Skip to content

Author: EthiopianReview.com

በሚያዝያው ምርጫ ተቃዋሚዎች እያማረሩ ነው

በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ የመጨረሻው ዝቅተኛ ግምት በተሰጠው የሚያዝያው ምርጫ ላይ የህብረትና የኦፌዴን አመራሮች እጩዎቻቸው እየታሰሩባቸው መሆኑንና የተለያዩ ጫናዎች እንደሚደርሱባቸው በመግለጽ ላይ ሲሆኑ በማንም አእምሮ እንደተቃዋሚ የማይቆጠሩት የአቶ ልደቱና አየለ ጫሚሶ ቡድኖች ምርጫውን አስመልክቶ እንደሚጠበቀው አዎንታዊ መግለጫዎችን በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡

ለሚያዝያው ምርጫ ገዢው ፓርቲ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተወዳዳሪዎችን ያዘጋጀ ሲሆን በተለይ አዲስ አበባ ላይ በምርጫ 97 የደረሰበትን ክስረት ባለው እድል ሁሉ ተጠቅሞ ለማካካስና ከሁለት አመት በኋላ ለሚካሄደው 4ኛው አገር አቀፍ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ተጠምዷል፡፡ በዋና ከተማዋ ላይ ብቻ የመምረጥ መብት እንዳለው የሚገመተው ከአንድ ሚሊን በላይ ዜጋ ቢሆንም በምዝገባው የመጨረሻ ቀናት ላይ ‹ተመዘገበ› የተባለው አሃዝ ከግማሽ እንደማይበልጥ የመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ሳይቀሩ ይፋ አድርገውታል፡፡ በዚህ የ520 ሺህ አሃዝ ላይ ህዝቡ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዳለው ያነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች አልሸሸጉም፡፡

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ዴሞክራቲክ ንቅናቄ (ኦፌዴን) እና የህብረት እጩዎች ወደሚወዳደሩባቸው ክልሎች በመሄድ ህዝባቸውን ለማነጋገር ሲሞክሩ ፍጹም ኢ-ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ወደ እስር ቤቶች ተግዘዋል፡፡

በሰሜን ሸዋ ዞን የሰላሌ የወሰን ከተማ በሆነችው በጎሃጽዮን ህዝቡን በማነጋገር ላይ የነበሩ 27 የኦፌዴን ተወካዮች በሙሉ ወደ እስር ቤት መነዳታቸው ለዚህ ተጠቃሽ መሆኑን አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ገልጸዋል፡፡ በዚህ የተነሳም ፓርቲዎች የእጩዎቻቸውን ማንነት ምርጫው እስኪቀርብ ላለመግለጽ እንደሚገደዱ በማስታወቅ ላይ ይገኛሉ፡፡

የቅንጅትን የትግል አቅጣጫ የሚወስን የስምምነት ፊርማ ተፈጸመ

ለቀናት ሰፊ ውይይት ሲካሄድበት የቆየው ቅንጅትን የትግል አቅጣጫ ይወስናል ተብሎ የታመነበት ስምምነት ፊርማ በቅንጅት ስራ አስፈጻሚ እና ፓርቲውን ወክለው ፓርላማ በገቡት በእነ አቶ ተመስገን መካከል በዛሬው እለት ተፈጸመ፡፡

ዛሬ ከቀኑ በ8፡00 ሰአት ላይ የቅንጅት ስራ አስፈጻሚ ቡድን ባደረገው የአብላጫ ድምጽ ውሳኔ የእነ አቶ ተመስገን ዘውዴ ቡድን ያቀረበው የትግል አቅጣጫ ሃሳብና አመራሩ ያቀረበውን ከተናበቡ በኋላ ተግባራዊ እንዲሆን ተወስኗል፡፡

የስምምነቱ ዝርዝር ሃሳብ ፓርቲው ህጋዊ የሚሆንበት አማራጭ አስመልክቶ የተለያዩ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በቀጣይ ሂደት አዲስ ስያሜ ለመውሰድ ወደ ምርጫ ቦርድ የሚኬድበት አማራጭ፤ ይህንን ተከትሎም ፊርማ ማሰባሰብ፤ ከፊርማ ማሰባሰብ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤ መጥራትና የፓርቲው አመራር የሚመረጥበትን ዲሞክራሲያዊ አሰራር ያጠቃለለ መሆኑን አንድ የአመራር አባል ለዜና አገልግሎቱ ገልጸዋል፡፡

ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ በጦርነት እየታመሰች ነው

በደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ኦሮሚያ ዞን ቦረና ከሃገረ ማርያም 57 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በጉጂዎችና በኮሬ ብሄረሰብ መካከል በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ጦርነት እየተካሄደ መሆኑን ሪፖርተራችን ዘገበ፡፤

በአከባቢው በተለያዩ ጊዜያት በወሰንና አከባቢውን ሃብት በመጠቀም መንስኤ ግጭቶች ሲከሰቱ የቆዩ ቢሆንም የአሁኑ ከፍተኛ የሰውና የንብረት ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን ተጠቂዎቹን ያነጋገረው ሪፖርተራችን ዘገባ ያመለክታል፡፤

እስካሁን ሁለት የፌዴራል ፖሊስ አባላትና ሌሎች ሁለት የክልል ፖሊስ አባላት በግጭቱ ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡

የአካባቢው ነዋሪዎች ግጭቱን የቀሰቀሱት በአካባቢው የተሰማሩት የወያኔ/ኢህአዴግ ካድሬዎች ናቸው ሲሉ ይከሳሉ:: በሌላ በኩል የዞኑ ባለስልጣናት “ኦንግ የፈጠረው ብጥብጥ ነው” ይላሉ::

የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ አባዱላ ገመዳ በክልሉ ያሉ የኦነግ አባላትን ለማስወገድ በሚል ከክልሉ አስተዳዳሪ ጋር የነደፉት የአራት ሚሊዮን ብር ፕሮጀክት ከከሸፈ በኋላ ግጭቶች በከፍተኛ ደረጃ መጨመራቸውን ምንጮቻችን አመልክተዋል፡፡

Young Ethiopian duo to take on Australia's Mottram

IAAF – World Junior 5000m champion Tariku Bekele and fellow Ethiopian Abreham Cherkos Feleke will both contest the 5000m national title against Australia’s 2005 Worlkd Championship bronze medallist Craig Mottram at Melbourne’s Olympic Park, one of the feature events on the timetable at the IAAF World Athletic Tour meeting on Thursday 21 February.

Both Bekele and Feleke come to Australia boasting impressive credentials – the Ethiopians have run faster than Mottram over 5000m. Tariku Bekele, 21, the younger brother of Kenenisa Bekele, is the 2006 World Junior 5000m champion. Tariku Bekele and Mottram have had some epic battles on the track, in particular, last year’s two mile event at the Prefontaine Classic in Oregon, and at the Golden Spike meeting in Ostrava when he was out-sprinted by Mottram in the final stages.

Cherkos Feleke, at just 18, was the world’s second fastest junior over 5000m in 2007, with his season’s best of 13.05.83 set when finishing third behind Mottram and Bekele at the Golden Spike meeting.

The Ethiopians will be looking to gain a mental advantage over Mottram in this Olympic year by defeating him on his home soil.

“I’ve had some good battles against Bekele and I’m looking forward to racing against him again,” Mottram said. “I’m really pleased that he’ll be coming to Melbourne as it gives me yet another opportunity to race against world class opposition in front of a Melbourne crowd.

“It’s always a challenge racing against the Ethiopians anywhere in the world, but being in Melbourne, where I’ve had so much support in the past, just brings an extra edge to the competition for me and hopefully for the fans. I’d love to see Olympic Park packed out for the Ethiopians and we get another night similar to what we had in Melbourne at the Commonwealth Games when I ran against the Kenyans two years ago.”

Mottram has just completed another block of altitude training at Falls Creek, and will head to the United States tomorrow, where he will prepare to defend his 3000m title against Commonwealth Games champion Nick Willis at the Boston Indoor Games (January 26), and prevent reigning world 1500m and 5000m champion Bernard Lagat from collecting his sixth Wanamaker Mile victory at the 101st Millrose Games in New York (February 1).

“After my three good blocks of training at Falls Creek, I feel ready now for world class competition,” Mottram continued. “I really enjoyed racing in Boston and Millrose last year against some very good fields, so I’ve decided to go back there again this year.”

“After racing Lagat in New York, and then Bekele in Melbourne, I will get a very good indication as to where my preparations are at.”

በደቡብ ኢትዮጵያ የቅንጅት ተወካይ በደህንነቶች ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ በህዝብ ግፊት ተለቀዋል

በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል የጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ የቅንጅት ተወካይ የሆኑት አቶ እንድርያስ ኤሮ በዛሬው እለት የከተማዋ የፌዴራል የደህንነት ቢሮ ሃላፊ በሆኑት በአቶ ሚካኤል ዘሪሁንና የወያኔ/ኢህአዴግ ተወካይ በሆኑት በአቶ ታደለ ያዕቆብ ከቢሯቸው ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ በህዝብ ግፊት መለቀቃቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ሪፖርተራችን ዘገበ፡፡

በአከባቢው ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ያላቸው የቅንጅቱ ተወካይ ከቢሯቸው ታፍነው ወደ ከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ሲወሰዱ ህዝቡ ማዘጋጃ ቤቱን በመክበብ በፈጠረው ጫና አባሉ ሊለቀቁ ችለዋል፡፡

አቶ እንድርያስ በጽ/ቤቱ ውስጥ ለሰአታት የቆየ ምርመራ የተደረገባቸው ሲሆን ህገ ወጥ ስብሰባ እንዲካሄድ አስተባብረዋል፤ ህዝቡ ለቅንጅት ድጋፉን እንዲሰጥ ቀስቅሰዋል፤ ህጋዊ ላልሆነ አመራር ድጋፍ አሰባስበዋል፤ እንዲሁም ይህንኑ ሁኔታ በተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ ሜዲያዎች አስተዋውቀዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸው እንደነበር ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የቅንጅቱ ተወካይ ጽ/ቤቱ እንዲዘጋ የተሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ አስመልክቶ ትእዛዙ በጽሁፍ ይድረሰኝና ከህዝባችን ጋር እመክርበታለሁ ያሉ ሲሆን በአስቸኳይ ባይለቀቁ ኖሮ ማዘጋጃ ቤቱን ከቦ የነበረው ህዝብ ወዳልታሰበ የሃይል እርምጃ ሊገባ ይችላል ተብሎ ተሰግቶ እንደነበር ዘገባው ያመለክታል፡፡

ለጥምቀት የወጣው ህዝብ ለቅንጅት አመራር የማበረታቻ መልእክት አስተላልፈ

የጥምቀት በዐልን ለማክበር በቦሌ መድሃኔአለም የተገኙት የቅንጅት ለአንድነትና ዴሞክራሲ ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ግዛቸው ሽፈራው ለበዐሉ ካደመው በብዙ ሺህ የሚቆጠር ምእመን “በርቱ” የሚል የድጋፍ መልእክት ተላለፈላቸው::

አቶ ግዛቸው በስፍራው የተገኙት ከቤተሰባቸው ጋር በበዐሉ ለመካፍል ቢሆንም በቦታው መኖራቸው እንደታውቀ ብዙ ሺህ ህዝብ ከቧቸው አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን ሲሰነዝር የነበረ ሲሆን ህዝቡ የቅንጅት ምልክት የሆነውን ሁለት ጣት ማሳየት ሲጀምር በአካባቢው የነበሩ ፖሊሶች የመደናገጥና ግራ የመጋባት መልክ ይታይባቸው ነበር::

አቶ ግዛቸው በርካታ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን ካስተናገዱ በኋላ ቅንጅት የህዝብ ድርጅት በመሆኑ ጊዜያዊ ችግሮች ቢያጋጥሙትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው ወደቤታቸው ተመልሰዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ የነ አቶ አባይነህ ቡድን በመኢዐድ ስም መንቀሳቀስ በመጀመራቸው ምክንያት ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ እየደረሰባቸው በመሆኑ ስልት በመቀየር “ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ” በሚል ስያሜ የፓርቲ ፈቃድ ለማውጣት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል::