Ethiopian eminent scholar and theologian Aleqa Ayalew Tamiru was buried on Thursday at Tekle Haimanot Church in Addis Ababa in the presence of over 15,000 people. Read the full report below in Amharic by an Ethiopian Review correspondent in Addis Ababa:
የአለቃ አያሌው የቀብር ስነ ስርዓት በተክለ ኃይማኖት ቤ/ክርስቲያን ተከናወነ፡፡
የአቡነ ጳውሎስን ስርዓት ከእምነትነቱ ይልቅ የካድሬ ስራ የሚሰራበት ነው በማለት በተቃውሞ ሰማዕት ሆነው የኖሩት አለቃ አያሌው ሕይወት ካለፈ በኋላ ሐሙስ ነሐሴ 17 ቀን 1999 ዓ.ም በአቡነ ተክለ ኃይማኖት በተከናወነው የቀብር ስነ ስርዓታቸው ላይ ቁጥሩ ከ15 ሺህ በላይ የሚገመት ሕዝብ ቢገኝም ካህናቱና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በዝማሬ አስክሬናቸውን ሳያጅቡ ቀሩ፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ማጉያ እንኳን ሳያወጡ የቤተ መቅደሱን በር ዘጋግተው ጠፉ፡፡
የአለቃ አያሌው የቀብር ስነ ስርዓት በደብረሊባኖስ ገዳም ይፈፀማል ተብሎ የነበረ ሲሆን አዲስ አበባ በሚገኘው ተክለ ኃይማኖት ቤ/ክርስቲያን እንደሚፈፀም ከተሰማ በኋላ ቤተሰቦቻቸው፣ ተከታዮቻቸውና ኃዘን የተሰማቸው በሙሉ በስፍራው ተገኙ፡፡
እንኳን ለአለቃ አያሌው ይቅርና አቅሙ የጎለበተ ባለኃብት ሲሞት በቤተክስቲያኑ የሚገኙ ካህናትና ወጣቶች ልብሳቸውን ለብሰው አስክሬን ሲያጅቡና ፍታት ሲፈቱ ይስተዋል የነበረ ሲሆን በእለቱ ግን የአለቃ አያሌው የቅርብ ወዳጆች የሆኑ ካህናት ብቻ በቤታቸው ፍታት አድርገውለላቸዋል፡፡
በቀብሩ ቦታ የነበሩ አንዳንድ የእምነቱ ተከታዮች እንደተናገሩት “ምድረ የቤተ ክህነት ሰራተኛ ዛሬ ካድሬነቱ ታወቀ፡፡ የአለቃ አያሌው አስክሬን መሸኘት ያለበት በዚህ መንገድ ነበር? ምንም አይደለም ለሁሉም አንድ ቀን ያስተዛዝባል” ሲሉ ተሰምተው ነበር፡፡
የአለቃ አያሌው የበኩር ልጅ ወ/ሮ ስምረት አያሌው ስለሁኔታው ሲናገሩ “አባታችን አሁን ባለው የአባ ገ/መድህን (አቡነ ጳውሎስ) አስተዳደር ስር ያሉ ካህናት ፍትኃት እንዳያደርጉልኝ በማለታቸው ከልክለናል፡፡ ይህን ያደረግነው የአባታችንን ቃለ ውግዘት ለመጠበቅ ስንል ነው፡፡ ያስተላለፈውን ቃለ ውግዘት የሚያከብሩና የሚፈፅሙ በርካታ ምዕመናን አሉ፡፡ የቀብር ስርዓቱ በነሱ ይፈፀማል፡፡” በሚል ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡
የዳግሚት ደብረሊባኖስ ደብረአሚን ፃድቁ አቡነ ተ/ኃይማኖት ምክኃ ድንግል ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በበኩላቸው የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ካህናቱም ልብሰ ተክህኖአቸውን አድርገው አለቃ አያሌው መኖሪያ ቤት መሄዳቸውንና ቤተሰቦቻቸው ቃለውግዘታቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ፍታት አታደርጉም ብለው እንደመለሷቸው ተናግረዋል፡፡ አንዳንዶቹም “እኛ ቃለ ውግዘታቸው ይጠበቅ ብለን እንጂ ከፓትሪያርኩ ጋር አብረን አይደለም አስክሬኑን ያላጀብነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የአለቃ አያሌው ደጋፊዎች ግን በዚህ አይስማሙም፡፡ ምንም እንኳን ቤተሰብ ቃለውግዘታቸውን ለመጠበቅ ቢከለክል ካህናቱም ሆነ ወጣቶች ልብሳቸውን እንደለሰቡ የቀብር ስርዓቱ ላይ መገኘት ይችሉ እንደነበር፤ እነሱ ግን ከዚህ ይልቅ ቤተ መቅደሱን ጠርቅመው መሄዳቸው ከኃይማኖት አስተማሪነታቸው ካድሬነታቸው እንደሚብስ ነው ያሳዩት ብለዋል፡፡
በቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት እንደታዘቡት ቤተ መቅደሱ ተጠርቅሞ ተዘግቷል፡፡ ለአለቃ አያሌው ቅኔ የሚቀኙ ወዳጆቻቸው የድምፅ ማጉያ አጥተው በቀበሌ ስብሰባ መጥሪያ ማይክራፎን ሲቀኙ ተስተውሏል፡፡
በዕለቱ በርካቶች በለቅሶ ኃዘናቸውን ይገልፃሉ፡፡ ከቤተክርስቲያኑ አናት በሚገኘው ጉልሏት አጠገብ ባለው መስታወት አንድ ሰው መጋረጃውን ገልጦ ወደህዝቡ ሲመለከት ታየ፡፡
ማን ይሆን? በሚል ይህን የተመለከትን ስንነጋገር የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እንደሆኑ የተገመቱ ሰው መሆናቸው ታወቀ፡፡ በኋላም በተደረገው ማጣራት ካህናቱ ህሊናቸው እያወቀ የአለቃ አያሌው የቀብር ስርዓት ከውጭ እየተፈፀመ እነሱ ከውስጥ ሆነው የቤተመቅደሱን በር ጠርቅመው ቁጭ ብለዋል፡፡
ሊቀ ኅሩያን በላይ መኮንን በርካታ ቅኔ ለአለቃ አያሌው የተቀኙላቸው ሲሆን ከቅኔው መካከልም
የሦስት ሺህ ዓመት ታሪክሽን
እንደ ጁሊያን ቆጥሮ
በባህር ሀሳብ አትቶ በአቡሻ ክር ተምሮ
ታሪክ ከታሪክ አጣቅሶ
መፅሐፍ አመሳክሮ
ሳያስረዳን ወግ ባህልሽን አበጥሮ
ጥንተ ታሪክሽን አንጠርጥሮ
የተላቁ ሊቅ ያ አንደበቱ ታስሮ
በአምዓትሽ ዋዜማ
በሚሌኒየም ከተማ
አራት አይናውን አያሌውን ካጣነውማ
ምኑን ባተልን እማማ?
ሲሉ ተቀኝተውላቸዋል፡፡
በመጨረሻም ለወ/ሮ ስምረት በተሰጣቸው እድል “አለቃ አያሌው የተበላሸውን የቤተክህነት ስርዓት እየታገሉ ያለምንም ደም ሰማዕት እየከፈሉ እዚህ አድርሰዋል፡፡ አሁንም ይሄን ተጋድሎ የሚመራና ለውጤት የሚያበቃ እንዲሰጠን እግዚአብሔር ልንለምነው ይገባል” ብለዋል፡፡
በአለቃ አያሌው ቀብር የእሳቸው ዘመድና ጓደኛ ከሆኑ አንድ ካህን በስተቀር አንድም የጠቅላይ ቤተክህነት መንበረ ፓትሪያርክ ሰራተኛ አለመገኘቱን ለመታዘብ ችለናል፡፡
ONLF Statement On UN Fact Finding Mission To Ogaden
The Ogaden National Liberation Front (ONLF) welcomes the decision of the United Nations to send a fact finding mission to the Ogaden. This represents a positive first step by the United Nations in addressing the man made humanitarian catastrophe unfolding in Ogaden.
We call on the United Nations not to limit the scope of this mission to a humanitarian assessment but to include an preliminary investigation of war crimes being committed against our people by the current Tigray Peoples Liberation Front (TPLF) led regime. We further urge the United Nations to allow international journalists, who are currently banned from entering Ogaden, to travel with the mission.
The ONLF is prepared to provide all necessary assistance to this mission and members of the international media who may join them in gaining access to all areas of Ogaden.
————————————-
Ogaden National Liberation Front (ONLF)
Assimba.org has issued the following press release in Amharic regarding comments by Ato Dawey Ibrahim, former chairman of the Ethiopian Workers Confederaiton. (Amharic font can be downloaded here).
አቶ ዳዊ ኢብራሂም በአሲምባ የውይይት መድረክ ላይ ለሰነዘሩት አስተያየት የተሰጠ ምላሽ
በስደት የሚኖሩ ወገኖች ከመካከላቸው አንዱ የማይመስል ሲያወራ “ስደት ለወሬ ያመቻል” ይላሉ። እንዲያም ሲል ተንኮል የተሞላበት ፈጠራን ሲገነዘቡ “ጅብ ከማያቁት ሀገር ሄዶ ቆርበት አንጥፉልኝ አለ” ይላሉ። ከጥቂት ቀናት በፊት “የኢሕአፓና ትርምሰ ዑደትና የኢትዮጵያ ሠራተኞች” በሚል ርዕስ በአቶ ዳዊ ኢብራሂም ተጽፎ በአንዳድ ድረ-ገጾች ከተበተነ በኋላ በአንዳንድ የፓልቶክ መድረኮች ይህን ጽሁፍና ያአሲምባ ድረ-ገጽንና ሌሎችን በሚመለከት በኛ ግምት ኃላፊነት የጎደለውና ከዕውነት የራቀ ተራ ወሬ ሲነዛ በመክረሙ በጣም አዝነናል። በተለይም አቶ ዳዊ ከሦሥት ወራት በፊት በአሲምባ የውይይት መድረክ የዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀንን አንተርሶ የአቀረብናቸውን በስደት የሚገኙ የቀድሞ ሠራተኞች መሪዎችን አስመልክቶና የአሲምባ የውይይት መድረክን ተልዕኮ አጣመው የራሳቸውን ትርጉም በዘፈቀደ ለማቅረብ በመሞከራቸው ይህንን መግለጫ እንድናወጣ ተገደናል። ከዚህም በላይ የሳቸውን ጽሁፍና በዕለቱ ከእንግዶቻችን ጋራ ያደረግነውን ቀለ-መጠየይቅ እንዳለ እቅርበን ፍርዱን ለአንባብያን እንተወዋለን።በመጀመሪያ የአሲምባ ውይይት መድረክ እንዴትና ለምን ተመሠረተ?
አቶ ዳዊ እንደጻፉት የአሲምባ የውይይት መድረክ የኢሕአፓ ተለጣፊ አይደለም። በጥቂት ሀገር ወዳዶች የሚንቀሳቀስ ከማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ ነጻ የሆነ ፤ ዘለቅ ብሎ የተገለጸውን ዓላማ ይዞ የሚንቀሳቀስ መሆኑን እንዲገነዘቡልን እንወዳለን። ይህንንም ስንል ግን ኢሕአፓ የኢትዮጵያ የቁርጥዬ ቀን ጀግኖች በደም አጥንታቸው የገነቡት ዕውነተኛ ሕዝባዊና ኢትዮጵያዊ ድርጅት መሆኑን ላንዴም አንጠራጠርም። ኢትዮጵያዊነቱን ለሚጠይቁ በድረ-ገጻችን በየቀኑ እያደገ ያለውን የሰማዕታት ስም ዝርዝርና አጠር ያለ ታሪክ ላስተዋለ ፣ በስማቸው ብቻ በኢትዮጵያ ያሉትን ብሔሮች፣ ሃይማኖቶችና የሥራ ዘርፎችን እንደሚያንጸባርቁ መረዳት ይችላሉ። ይህም ራሱ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሞላ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሶ በደሙ የጻፈው ዕውነተኛ ታሪኩ ነውና ዛሬ የትግራይ ተወላጅ ብቻ ለትግራይ ሕዝብ ወይም የኦሮሞ ተወላጅ ብቻ ለኦሮሞ ሕዝብ ወዘተ,,ሃሳቢና ተቆርቋሪ እንደነበሩ አድርገው ሊያስተምሩን የሚዳዳቸውን ሁሉ ከሚያስፋፉት ጥላቻና ድንቁርና ጋር እርቃናቸውን ያስቀረዋል።
መድረኩም ሆነ ድረ-ገጹ በተመሠረቱበት ወቅት የወያኔ መንግሥት በዘጠና ሰባቱ ምርጫ ማግስት ያታልልበት የነበረውን የዲሞክራሲ ሽርጥ አውልቆ ጥሎ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ድሮውንም ግልጽ የነበረውን ፋሻሽታዊ ገጽታውን ይዞ በዓለም መድረክ ላይ ብቅ ያለበት የቀውጢ ጊዜ ነበር። ይህም ሁኔታ አዲሱ ትውልድ ለሚጠብቀው መራራ ትግል፤ ሊመረምረውና ሊማርበት የሚገባ፤ በዛሬዪቱ ኢትዮጲያችን የተንሠራፋው የዘረኞች፤ የጎጠኞችና፤ የሆዳሞች መንጋ አቶ ዳዊ እያደረጉት እንዳሉት ሁሉ የሚከላልሰውን፤ በጀግንነት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ባላቸው ፍቅር፤ ለፍትኅና ለዲሞክራሲ፤ በውድ ሕይወታቸው ምስወዕትነት ያዳበሩትን የዚያን ትውልድ ጅግኖች የትግል ታሪክ፤ ሳይቀነስ፤ ሳይበረዝና ሳይደለዝ፤ አሁንም በሕይወታቸው ከሚኖሩ የትግል ጓዶቻቸው፤ የሥራ ባልደረቦቻቸው፤ ወዳጆቻቸውና ቤተ-ዘመዶቻቸው ተሰባስቦ፤ ዕውነቱ በትክክል እንዲቀርብ ለማድረግ የጀመርነው ውጥን ወይም ፕሮጀክት ነው።
ከዚህም ሌላ ይህ መድረክ ባለፉት አርባ ዓመታት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍትኃዊ ነፃነት ሲታገሉ ለወደቁ፤ በደርግ ፋሺሽታዊ ሥርዓት በቀይ ሽብር ሠለባ ለሆኑ፤ ለሕዝባችን ነፃነት እንታገላለን በሚሉ ጠባብ ብሔረትኞች ለተጨፈጨፉ፤ በፅናታቸው፤ በኢትዮጵያዊነታቸው ተግዘው ለማቀቁና አሁንም በየጉድባው አሣራቸውን ለሚቆጥሩ፤ ከምድረ-ገጽ ደብዛቸው ለጠፉ የቁርጥዬ ቀን የኢትዮጵያ ጀግኖችና በዓለም ዙሪያ ካለውዴታቸው ተሰደውና በሀገር ቤትም አንገታቸውን ደፍተው ለሚኖሩ ታጋዮች መተሰቢያ እንዲሆን አስበን የመሠረትነው እንጂ አቶ ዳዊ እንደለጠፉብን ሴረኞች አይደለንም። ሥራችንም ሃላፊነት የተሞላው ለመሆኑ በግልጽ በውይይት መድረኩም ሆነ በድረ-ገጹ የሚንጸባረቅ ስለሆነ በተዘዋዋሪም መንገድ ጸረ-ቅንጅት አድርገው ሊቀቡን የሚሞክሩትን ሁሉ አንቀበላቸውም።
እንግዲህ ይህንን ግልጽ ካደረግን በኋላ በአቶ ዳዊ ጽሁፍ ላይ በጥቅሉ የተገነዘብነው ነገር ቢኖር የደርግ ፋሺሽቶችና ግብረ-አበሮቻቸው ያፈሰሱትን ደም ከጃቸው ያነጹ እየመሰላቸው በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሏቸውን፤ ያረዷቸውን፣ በዘይት የቀቀሏቸውን ኸረ ስንቱን ይገባቸዋል ብለው የሚያቅራሩትን ያክል በሚያሳዝን ሁኔታ እኚህም ሰው በዚህ ጽሁፋቸው በአጠቃላይ የፋሺሽቶች ሰለባ የሆኑትን ወገኖቻችንን የሙት ወቃሽ መሆናቸውን ነው። በአሲምባ ደግሞ ይህን ዓይነት የተንሸዋረረ ታሪክ የሚያቀርቡትን ለማስተካከል ስለቆምን እንዳለፉት ሃያና ዓመታት ተድበስብሶ የሚቀር የለምና እንግዲህ አረፍ ይበሉና እስኪ ከላልሰው ካቀረቡት የሰማዕታት ታሪክ መካከል ጥቂቱን እንስተን በጥሞና እንወያይ። ከዚያ በፊት ግን እንዲያውቁልን የምንሻው ኢህአፓ በዓለም ዙሪያ ሕጋዊ ጽ/ቤቶች ፣ የራዲዮ ጣቢያዎች ፣ የራሱ ድረ-ገጽና “ዲሞክራሲያ” ልሣኑ ያለው ድርጅት ስለሆነ በድርጅቱ ያቀረቡትን ክስ መልስ እንደማይነፍገዎ እንተማመናለን።
በመድረካችን ባሉት ቀን ቀርበው ውርጅብኝ ያወረዱባቸው እንግዶቻችንም እንዲሁ መልስ የሰጥዎታል ብለን እንገምታለን። ከዚህ ጽሁፍም ጋር አባሪ አድርገን ዝግጅቱን ያቀረብን ዕለት ውይይት ቅጂ እንደሚያመለክተው የእርስዎ ስም በመጥፎ አልተነሳም፣ ቅጂውን እንዲያዳምጡም እንጋብዞታለን። አንባቢያንም የአቶ ዳዊ ኢብራሂምን ጽሁፍ የኛን መልስ እንዲሁም የውይይቱን ቅጂ በማድመጥ በዕለቱ የውይይቱ መንፈስ ምን እንደነበር ያራሳችሁን ግንዛቤ እንደምትወስዱ አንጠራጠርም።
የምንተችባቸው ጽንሰ ሃሳቦች
1. በእርስዎ የደበዘዘ መነጽር ተመልክተው ደርግ በ1968 ዓ/ም ዲሞክራሲያዊ እንደ ነበር ሁሉ በዚያን ሜይ ዴይ የፈጸመውን እልቂት በኢህአፓ ተንኳሽነት እንደሆነ አድርገው ለማቅረብ መሞከርዎ የታሪክ ክለሳ ነው። ከጻፉት ለመጥቀስ “…በ1968 ዓ/ም ሜይ ዴይ በሚከበርበት ዕለት በዓብዮት አደባባይ ሠራተኞችን የማስመታትና ከሠራተኞች መሞት ስለደርግ ጨካኝነት ማስረጃ ለመፈልቀቅ የፈጸመችው መሠሪ ተግባር… ሠራተኛው ሕንፃ ላይ ለተጠመዱ መትሪየሶች የእሳት ዕራት እንዲሆን አደረገች…” ብለው የዚያን ትውልድ ሰማዕታት ወቃሽ ሆነው ተሰልፈዋል።
ዛሬ ሀገራችን እንደ ሀገር የምትቀጥልበትን ሁናታ በጥያቄ ውስጥ ያስገባውን ወያኔን አስወግደን በምትኩ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመሥረት ኢትዮጵያዊ ኃይሎችን ወደ አንድ ወገን እንዴት ማምጣት የቻላል ብለው ሀገር ወዳዶች ከሊቅ እስከ ደቂቅ በሚጨነቁበት ወቅት እርስዎ ታሪክን የሚያውገረግር ተራ ወሬ የአሲምባንም ሚና ያጣመመ አጀንዳ ሲያሲዙን ማንን እየጠቀሙ መሰለዎት? ከፍተኛ መስዋዕትነት እየተገበረበት ያለን ሕዝባዊ የዲሞክራሲ ትግል እየጠቀሙ መሰለዎት? ኢሕአፓ የወያኔን ጠባብነት አውቆ ታጋዮቹን የገበረው ዛሬ አይደለም። ገና ከመነሻቸው ከደርግ ጊዜ ጀምሮ ነውና ያም ጥፋቱ ነው ብለው ያስተምሩን ይሆን? ከ1991 ዓ/ም ወያኔዎች ደብዛቸውን ላጠፏቸው አባላቱ፣ በአደባባይም ለገደሏቸው ታጋዮቹ ጥፋቱ የኢሕአፓ ነው ይሉን ይሆን?
ለማንኛውም ከላይ ከጽሁፎ ለጠቀስነው ዕውነታውን እንመልከትና በዚያን ቀን ማለትም ሜይ ዴይ 1968 ዓ/ም ልክ በ1997 ዓ/ም የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን ምንነት አንቀርቅቦ እንዳወቀ ሁሉ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሠራተኛውንም ጨምሮ የደርግን ምንነት በግብሩ የተረዳ ስለነበር በዚያን ዕለት ሠራተኛው “ጊዜያዊ ሕዝባዊ መንግሥት አሁኑኑ!” የሚሉ መፈክሮችን አንግቦ መውጣቱ፤ ብሎም በጊዜው የሕዝቡን ዋይታ ያንጸባርቅ የነበረውና ሕዝቡንም አደራጅቶ ያታግል የነበረ የሕዝቡ ፓርቲ ኢህአፓ ብቻ ስለነበር፤ “ኢህአፓ ፓርቲያችን ነው!” በሎ መፈክሩን በአደባባይ የዞ መውጣቱ ያስቆጣቸው የደርግ ባለሥልጣናት የፈጸሙት ይቅርታ የሌለው ጭፍጨፋ ነው።
ለመሆኑ እርስዎ በጽሁፎ ኢህአፓ ያንን ቀን የደርግን ፋሺሽትነት ለማስመስከር ተጠቀመበት የሚሉን ከዚያ በፊት ደርግ በሥልጣን ከወጣ ጀምሮ በግልጽ ያስመሰከረውን ካለፍርድ ሲሻው በአዋጅ የፍየል ወጠጤ በራዲዮ እያዘመረ ይገድል እንደነበር ፤ አለያም የደርግ አባላትና ተጠሪዎቹ በደረሱበት ቦታ ተቃዋሚ ተብለው የሚጠረጠሩትን የሠራተኞች ተሟጋቾችንም ጨምሮ ማለት ነው ይረሽኑ ያሰቃዩ እንደነበር እረስተውት ነው? ወይስ ዛሬ ለፖለቲካ ሥልጣን ራስን ለማመቻቸት ኢሰፓዎችን ማሞካሸት ይሻላል ብለው ገመቱ? ወይስ ተልኮዎ ረቀቅ ያለ ኢትዮጵያዊው ኃይል ወዳንድ እንዳይመጣ የመከፋፈያ መርዝ መርጨትዎ?
እንግዲህ ታሪክን እንደ ታሪክነቱ እንዲከለስ መፍቀድ ለወደፊት ለምናደርገው ትግል ጥራትን ከማሳጣቱም ሌላ ስህተቶች እዲደገሙ መሠረት ስለሚሆኑ በኛ በኩል እንዲህ ያለውን የውሸት ዘመቻ እየሰማን ዝም ማለቱ ጉዳቱ እንጂ ጥቅሙ ስላልታየንና የርስዎንም የመዋሸት ችሎታ ህዝቡ እዲረዳ በማድረግ በመድረካችን የተካሄደውን ውይይት ቅጂ እንዳለ በማቅረብ እንዴት ሊያጣምሙት እንደሚሞክሩ አሳይተን የርስዎና የመሳሰሉትን የተዛቡ አስተያየቶችን እንደዕውነታ ወስደን የተሳሳተ ግምት ውስጥ ከመግባት በፊት ሁሉም ወገን የሚያቀርበውን ተመልክቶ ትክክለኛው የትኛው እንደሆነ ከድምዳሜ መድረስ እንደሚቻል ለማሳየት ነው።
የአቶ ዳዋን የ1968ቱን የሜይ ዴይ ታሪክ እንኳ ይሁን ብለን ብንቀበል ፣ በዛሬዎቹ የጎጠኞች መንግሥት ከ1997 ዓ/ም በኋላ የሕዝብ ድምፅ ይከበር ብለው ሰላማዊ ሠልፍ ሰለወጡ ብቻ ለተጨፈጨፉ ወገኖች ተጠያቂዎቹ ታሥረው የነበሩ የቅንጅት መሪዎች ናቸው የሚሉንን ልንሰማ ነው ማለት ነው።
ከታሪክ ያልተማሩ ታሪክን ይደግማሉና በ1968 የተፈጸመን በደል ትክክለኛ ምንጩንና በጊዜው የነበረውን ሁኔታ በትክክል እንዳይጤን አውቀውም ሆነ ሳያውቁት ያ ትውልድ ከልቡ አምኖ ለወገኖቹ በቅንነት መሥዋዕትነት የከፈለበትን ታሪክ መከላለስ አዳጋው የዛሬው ትውልድ የአለፈውን ትውልድ ድክመቱን ሳይደግም ግን ከጠንካራ ጎኑ በተለይም ለሀገርና ወገን ያለውን ፍቅር እዲሁም በራስ መተማመንና ጀግንነትን ሰንቆ ለኢትዮጵያችን ያለናት እንደ አባቶቻችን እናቶቻችን እኛው በኢትዮጵያ የምንኮራ ሀገር ወዳዶች ብቻ መሆናችንን በቶሎ ተገንዝቦ እንዳይታገል ነገሮች እየተምታቱበት ፈራ ተባ እያለ እንዲጃጃልና ሀገሩን እንዲነጠቅ ማድረግ መሆኑን ልናስገነዝብ እንወዳለን።
ይህ ደግሞ ኢህአፓ ነበርን፤ ታሪኩን ከኛ የበለጠ የሚያውቅ ላሳር ነው እያሉ የዚያን ትውልድ ሰማዕትነት እያደባዩ ድርሳነ ክህደት የሚያነበንቡትንም ስለሚመለከት ፤ ሁሉም አንድ እንዲረዱልን የምንፈልገው ነገር ቢኖር፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጊዜና ሁኔታዎች ሲመቻቹለት የኢህአፓንና የዚያን ትውልድ መስዋዕትነት ዕውነተኛውን ታሪክ እንደሚናገር በፍጹም አንደማንጠራጠር ነው።
2. የዚህ ምላሽ ዋና ዓላማ አቶ ዳዋ ኢብራሂም የጻፉትን 6 ገጽ የታሪክ ክለሳ መስመር በመስመር ልንተችበት ሳይሆን ቢያንስ አንድ ሁለቱን አንስተን የቀዳዳውን ስፋት በህዝብ መነጽር እንዲታይ በማድረግ የዚያ ትውልድ ታሪክ በብዙ ሊመረመርና ሊጠና የሚገባው፤ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የምናየው ታሪክን የሚያንቋሽሽ ወሬና አሉባልታ እንዴት ወደ ሕዝቡ ዓዕምሮ ሰርፆ እንዲገባ እየተቀረገ እደሆነ ለማሳየት ብቻ ስለሆነ በዚህ ክፍል አንድ ነጥብ አንስትን እንተችበትና ወደ ማጠቃለያችን እንሄዳለን።
አቶ ዳዊ ኢብራሂም ሲጽፉ “…ከ1967 እስከ 1969 ዓ/ም ድረስ ኢህአፓ በኢትጵያ ሠራተኞችና ማህበሮቻቸው ያደረሰችው ጉዳት ይቅር የማይባል ዘግናኝና አሳዛኝ እንደነበር…” ይሉና ቀጠል አድርገውም “…ሥዩም ከበደ የኢህአፓ የትጥቅ ትግል (እነሱ እንደሚሉት የጥቃት መከላከያ) ዋና መሪ ስለነበር የሠራተኛውን ብሔራዊ ጽ/ቤት የግድያ ዕቅድ ማውጫ፤ …የመቺ ቡድን መጠለያና መሸሸጊያ፤ …የማህበሩ ሕንፃ ከመሬት በታች ምድር ቤት ስለነበረው የጦር መሳሪያ መደበቂያ ምቹ ሥፍራ አድርጋ ቆየች…” ብለው ይቀጥላሉ። ምናለ የሚመስል እንኳ ቢያወሩልን። ሥዩም ከበደና ኢህአፓ ያበዱና ሞትን ያሸተቱ ካልሆነ በቀር፣ በጊዜው ደርግ የሠራተኛውን ድርጅታዊ ነፃነት በራሱ ታማኝ መሪዎች ለመተካት እየታገለና እያስፈራራ እርስዎም ያልካዱት ደጋፊ ነን የሚሉ ውሁዳን መሪዎች እንደ ጣዕም ያለው እሸቴ አይነቱ ነገር አቀባዮች በሚርመሰመሱበት ጽ/ብት ውስጥና፤ ከሁሉም በላይ የደርግ የስለላ መረብ 24 ሰዓት በዓይነ ቁራኛ የሚጠበቀውን ህንፃ ወደ ምሽግነት ኢህአፓ ቀየረችው በሎ እንደ ታሪክ ማውራት የሚያሳፍር ቅጥፈት ነው። ለርስዎ አፈርንልዎ።
ሌላው ደግሞ ያኔ ደርግ ኢህአፓዎችን እያደነ ሲገድል “ሥርዓተ-አልበኞች” እያለ እኒያን ሰማዕታት ሰብአዊ ገጽታ እንዳይኖራቸው ግን ግዑዝ ከም አርዮስ መልክ በመቀባት፤ ቢገደሉም ምንም አይደለም አይነት ነገር በሕዝቡ እዕምሮ ይቀርፅበት የነበረውን የጭካኔ ቋንቋ ከሠላሣ ዓመት በኋላ ይዘው ብቅ ሲሉ ዛሬም እንደ ትላንቱ የሚኮንኑት መሠረታዊ የስብአዊ መብቶችን ፤ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ካለገደብ መጠየቅን፣ የመሰብሰብ፣ የመጻፍ፣ የመናገር፣ በነፃ የመደራጀት መብቶች መረጋገጥን፤ ባጠቃላይ የህግ የበላይነት የሚረጋገጠባት ለሁሉም ኢትዮጲያዊ እኩል የሆነች ሕዝባዊ ሥርዓት የተመሠረተባትን አንድ ኢትዮጵያን እንደሆነ ይገንዘቡልን።
ሊነግሩን የፈለጉት በዚያን ጨለማ ዘመን ካለፍርድ በነፃ እርምጃ በቀይ ሽብር የታጨዱትን ሰማዕታት ይገባቸዋል ነው። ይህንንም ዓይነት የተንሻዋረረ አመለካከት እንደርስዎ ያለ ስለሚያስፋፋው ዛሬም ስለፖለቲካ እስረኞች እንኳ አንዳንድ መሪዎች ነን የሚሉ ሲያወሩ ከ1991 ዓ/ም ጀምሮ ካለአግባብ ታሥረው ደብዛቸው የጠፉ በአብዛኛው ኢህኢፓዎች የት አሉ እንኳ ብሎ ለመጠየቅ ያልቻሉ የተዳነዙ ሰዎች ስለሕግ የበላይነት ሊደሰኩሩብን ሲያምራቸው እያነን ነው። በኛ አመለካከት የህግ የበላይነት ሲባል እንኳንስ በጸረ-ወያኔነት የታገለና ያታገለ በመደዳው ሕዝብ የጨረሰው መንግሥቱ ኃ/ማርያም እራሱ እንኳ ካለህዝባዊ ፍርድ መነካት የለብትም ባዮች ነን። ለዚህም የርስዎን ጽሁፍ አንተርሰውም ሆነ በሌላ ጊዜ የአሲምባ የውይይት መድረክ ስለቅንጅት መሪዎች እንደማናስብ አድርጎ ለማሳየት ቢነዘብንም ትግላችን አሁንም ወደፊትም በሃገራችን ዳግም ቀይ ሽብር እንዳይመጣ በሁሉም መሪዎች ነን በሚሉ ጭንቅላት ውስጥ ለዘለዓለም እንዲደውል የምንፈልገውም ለዚህ ነው። የማንም ይሁን የማን ድርጅት ወይም አማለካከት ደጋፊ ተብሎ ወደ እሥር የማይወረወርበት፣ የማይገደልበት ሀገር መመሥረት እድንችል የርስዎን ዓይነት ድንቁርና ማጥፋት አለብን በለን አበክረን እናምናለን። ምክንያቱም ለሌላ ማዓት ያዘጋጀናልና።
በአንድ ቦታ ኢህአፓ “…የሠራተኛውን የማህበራት መንፈስ እስከወዲሁ ድረስ እንዲደበዝዝ ከፍተኛ ወንጀል…” ብለዋል። የሠራተኛውን የማህበራት መንፈስ ያደበዘዘው ኢህአፓ ሳይሆን የሠራተኛውን በነፃ የመደራጀት መብት በመፃረር ሥልጣንና ኃይልን በመጠቀም የሠራተናውን ማህበራት በራሳቸው ምስል ሊቀርጹ የተነሱ የዚያን ጊዜ የደርግ ኢሠፓዎችና የዛሬዎቹ በክልልና በዘር የሚያናክሱት ወያኔዎች መሆናቸውን መረዳት የማይፈልግ ራሱን ያመመው ብቻ ነው።
ለማጠቃለል፥
እኛ የአሲምባ የውይይት መድረክ መሥራቾች ባለፉት 30 ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትንንቅ ያለፉና ሚና የነበራቸው ግለ ሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ከተሠሩ ስህተቶች አንዳቸውም ነፃ ነን ብለው እጃቸውን እንደጲላጦስ መታጠብ እንደማይችሉ እናምናለን። በዓፄው ዘመነ-መንግሥት ፤ በደርግ ፋሻሽታዊ ሥርዓትና በዛሬዎቹ ጠባብ ብሔረተኞች ጊዜ፤ በምንግሥት ደረጃ ጥቂት ቡድኖች ራሳቸውን በሥልጣን ተክለው ለዘላዓለም ለመኖር ሲፍጨረጨሩ የፈጸሙትን ጥፋት፣ በሕዝብ ያደረሱትን በድልና ግፍ ከሕዝቡ ለመከላከል ሲውተረተሩ እንደ ኢህአፓ ያሉ ሕዝባዊ ድርጅቶች የፈጸሙትን ስህተቶችና ከሚደርስባቸው ምት የተነሳ ያሳዩትን መዝረክረክና ግድፈት በማንኛውም ዓይነት መሥፈሪያ ለማነፃፀር መሞከር ራሱን የቻለ ስህተት ነው በለን እናምናለን።
ሌላው ደግሞ ልንገነዘበው የሚገባ ነገር ቢኖር ከ30 ዓምታት በፊት ሲውተረተር ራሱን ገምግሞ አነሰም በዛም የሰራቸውን ስህተቶች ለማረም የሞከረና አቅጣጫውን በይፋ የቀየረ በጊዜው ከነበሩ ኃይሎች በድርጅትም ሆነ በግለ-ሰብ ኢህኢፓ ብቻ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህንን ሁሉ ካልን በኋላ የአቶ ደዋ በኢህአፓ ላይ እጣታቸውን መቀሠር በአሁኑ ወቅት ጠቀሜታውና ዓላማው ምን ይሆን ብለን ስንጠይቅ ያገኘነው መልስ ምንም ነው። ሀገራችን እንድትፈርስ እየተመቻቸች፣ የህዝባችን ውስጣዊ ቅራኔው ተጋግሞ እርስ በእርስ ተፋጦ ወደማይሆን አቅጣጫ እየተገፋ እያለና ከመቼውም የበለጠ ሀገር ወዳዶች ወደአንድ ወገን መሰባሰብና ሀገራችንን ከጥፋት ለማዳን ልንረባረብ በሚገባን በአሁኑ ጊዜ ፤ በመካከላችን መተማመንን የሚያደርቅ ላለፉት 30 ዓመታት ልንተማመንባቸው ያልቻልንባቸውንና የሚያፋጥጡንን ደጋግሞ ማንሳት ሁላችንንም የትም አያደርሰንም። በዚህም ከቀጠልን በጥቂት ጊዜ ውስጥ የምንከራከርበትና የምንኮራረፍብት ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አትኖርም።
ምጀመሪያ የመቀመጪያዬን እንዳለች ሁሉ ዝንጀሮ፤ ሀገራችንን የምንወድ ወገኖች ሁሉ ትላንት ያልተስማማንባቸውን ነገሮች ሁሉ ከጠረጴዛው አንስተን፤ ተከባብረን እየተዳማመጥን የምንከራከርብት ህዝባዊ ሥርዓት እስከምንመሠርት ጌዜ በይደር አቆይተን፤ ሀገር የማዳኑና ፍትኃዊ ሥርዓት መምጣትን የምናምን ፤ ከሁሉም በላይ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የማንደራደር ተሰባስበን ኃይላችንን አፈርጥመን በአንድ አቅጣጫ እንቅስቃሴ መጀመሩን ዋነኛ ተግባራችን እናድርገው።
በዚህ ሀገር አድን እንቅስቃሴ ደፍረን መሳተፍ ስንጀምር ካለጥርጥር ወደድንም ጠላንም መተማመንን በትግሉ ውስጥ ቀስ በቀስ እንገነባለን። ይቅር መባባሉንም እንደገና “ሀ” ብለን እንጀምራለን። ስህቶቻችንም ለመጠፋፊያ ሳይሆን የምንማማርባቸው መሠረቶች አድርገን አባቶቻችን ከሁሉ ጋር ተናጭተው በጥሩ የባህል ምግባር መሠረት አዋቅረው ያስረከቡንን ኢትዮጵያዊነትን መልሰን እናገኛታለን። ህዝባዊ ሥርዓትን ምሥርተን የህግ የበላይነት በሚረጋገጥባት ሀገር ምህረት አድራጊውም ከሳሹም ህዝብ ነው። ለዚህም ነው ዛሬ ያልተስማማንባቸውን ለህዝቡ ፍርዱንም እንተውለት የምንለው። ዛሬ በምንጫወተው ሚና በምናሳየው ምግባር ያለጥርጥር ህዝባችን ለሁላችንም ምስጋናውን እኩል ይሰጠናል። ምህረቱንም እንዲሁ። በህዝባችን እንተማመን። ዛሬ እኮ የሚገፋውን ያክል ኢትዮጵያን ይዞ ካለመሪ ከወያኔ ጋር ተፋጦ ያለ ህዝቡ መሆኑን አንርሳ።
ኢትዮጵያዊነት ያለጥርጥር ያቸንፋል!
ፍትኃዊ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንነሳ!
የአሲምባ የውውይይት መድረክ
አመቱን ሙሉ ሲዘፈንለትና ሲነገርለት በነበረው የኢትዮጵያውያን ሚሌኒየም በዓል ላይ ቢያንስ ሕዝብን ሊያሳትፉ ይችላሉ ተብለው የታሰቡት የመስቀል አደባባይ ዝግጅቶች ከፀጥታ ጋር በተያያዘ ችግር ሊፈጠር ይችላል በሚል የስጋት ሰበብ ተሰረዘ፡፡ የበዓሉን ዝግጅት ያዘጋጃል በሚል ተቋቁሞ የነበረው የሚሌኒየም በዓል አከባበር ምክር ቤትም በመጨረሻ ከአንድ የዋዜማ ዝግጅት በስተቀር ሌላውን አመቱን ሙሉ ነው የምሰራው ሲል አስታውቋል፡፡
ከአቶ መለስ አንደበት ከ500 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ይገባሉ ተብሎ መነገሩ በነዋሪዎቹ ላይ የኑሮ ውድነት ከመጫኑ ውጪ ምንም የታየ በርካታ እንግዳ የለም፡፡
በመስቀል አደባባይ ለስምንት ቀናት መንደር በመገንባት ዝግጅት ለማዘጋጀት ከአዲስ አበባ ሚሌኒየም ጽ/ቤት ፍቃድ አግኝቶ የነበረው “ቴስት ኦፍ አዲስ” የተባለ ድርጅት ዝግጅቱን ማድረግ እንደማይችል በደብዳቤ ተገልፆለታል፡፡
በመስቀል አደባባይ ሚሌኒየሙን በማስመልከት ምንም አይነት ዝግጅት እንደማይደረግ በመንግስት በኩል የተገለፀ ሲሆን እንደምክንያት የተጠቀሰውም የኤርትራ መንግሥት የኢትዮጵያውያን ሚሌኒየም በዓል እንዲደናቀፍ በየቀኑ ከሽብርተኞች ጋር መልዕክት እየተለዋወጠ በመሆኑ ለደህንነት ሲባል ክፍት በሆኑ ቦታዎች ዝግጅት አይደረግም የሚል ነው፡፡
ሚሌኒምን በሚመለከት ካሁን በኋላ በኢትዮጵያ የሚደረጉ ዝግጅቶችም በዋዜማው በስታዲየም እና በጃን ሜዳ “ሕብር” በሚል የብሔር ብሔረሰቦች ጭፈራና ቀልድ ይታያል አዘጋጁም ብሔራዊ ሚሌኒየም ጽ/ቤት ከአዲስ አበባው ጋር በመተባበር በአርቲስቶች ተሳታፊነት ነው፡፡
በተጨማሪም በቦሌ በእነ አላሙዲን በተገነባ አዳራሽ የሙዚቃ ፌስቲቫል የሚዘጋጅ ሲሆን እስረኞቹ ካልተፈቱ ኮንሰርት አላዘጋጅም በሚል መግለጫ የሰጠው ቴዲ አፍሮም በሚቀጥለው ሳምንት የሙዚቃ ኮንሰርት ያዘጋጃል፡፡
ሚሌኒየምን በዓል ለማክበር በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ይገባሉ በሚል በተነገረው መሰረት አከራዮች ለእንግዶች እናከራያለን በሚል ተከራይን ለማስለቀቅ በሚያደርጉት ጥረትና ተከራይ ከምለቅ ኪራይ እጨምራለሁ በሚል ግብ ግብ የቤት ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ከመጨመሩ ውጪ ከሆቴል ተርፎ ቤት የሚከራይ እንግዳ መምጣቱን የተመለከተ አንድም ሰው የለ፡፡
በተጨማሪም የተለያዩ ምክንያቶች የሚሰጠው የኑሮ ውድነት ከሚሌኒየሙ በዓል ጋር ሊሆን እንደሚችል በሚገመቱ አንዳንድ ምክንያቶች ለምግብነት የሚያገለግሉ እቃዎች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ውድነት ታይቷል፡፡
ከዚህ በላይ ግን ከሰኔ ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ ይጎርፋል ተብሎ የተጠበቀው ትውልደ ኢትዮጵያዊ አልፎ አልፎ በአሉን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለማክበር ከሚመጡት በስተቀር እንደታሰበው እየመጣ ያለ እንግዳ የለም፡፡
የአቡነ ጳውሎስን ስርዓት ከእምነትነቱ ይልቅ የካድሬ ስራ የሚሰራበት ነው፤ በማለት በተቃውሞ ሰማዕት ሆነው የኖሩት አለቃ አያሌው ሕይወት ካለፈ በኋላ ሐሙስ ነሐሴ 17 ቀን 1999 ዓ.ም በአቡነ ተክለ ኃይማኖት በተከናወነው የቀብር ስነ ስርዓታቸው ላይ ቁጥሩ ከ15 ሺህ በላይ የሚገመት ሕዝብ ቢገኝም ካህናቱና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በዝማሬ አስክሬናቸውን ሳያጅቡ ቀሩ፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ማጉያ እንኳን ሳያወጡ የቤተ መቅደሱን በር ዘጋግተው ጠፉ፡፡
የአለቃ አያሌ የቀብር ስነ ስርዓት በደብረሊባኖስ ገዳም ይፈፀማል ተብሎ የነበረ ሲሆን አዲስ አበባ በሚገኘው ተክለ ኃይማኖት ቤ/ክርስቲያን እንደሚፈፀም ከተሰማ በኋላ ቤተሰቦቻቸው፣ ተከታዮቻቸውና ኃዘን የተሰማቸው በሙሉ በስፍራው ተገኙ፡፡
እንኳን ለአለቃ አያሌው ይቅርና አቅሙ የጎለበተ ባለኃብት ሲሞት በቤተክስቲያኑ የሚገኙ ካህናትና ወጣቶች ልብሳቸውን ለብሰው አስክሬን ሲያጅቡና ፍታት ሲፈቱ ይስተዋል የነበረ ሲሆን በእለቱ ግን የአለቃ አያሌው የቅርብ ወዳጆች የሆኑ ካህናት ብቻ በቤታቸው ፍታት አድርገውለላቸዋል፡፡
በቀብሩ ቦታ የነበሩ አንዳንድ የእምነቱ ተከታዮች እንደተናገሩት “ምድረ የቤተ ክህነት ሰራተኛ ዛሬ ካድሬነቱ ታወቀ የአለቃ አያሌው አስክሬን መሸኘት ያለበት በዚህ መንገድ ነበር? ምንም አይደለም ለሁሉም አንድ ቀን ያስተዛዝባል” ሲሉ ተሰምተው ነበር፡፡
የአለቃ አያሌው የበኩር ልጅ ወ/ሮ ስምረት አያሌው ስለሁኔታው ሲናገሩ “አባታችን አሁን ባለው የአቡነ ጳውሎስ አስተዳደር ስር ያሉ ካህናት ፍትኃት እንዳያደርጉልኝ በማለታቸው ከልክለናል፡፡ ይህን ያደረግነው የአባታችንን ቃለ ውግዘት ለመጠበቅ ስንል ነው፡፡ ያስተላለፈውን ቃለ ውግዘት የሚያከብሩና የሚፈፅሙ በርካታ ምዕመናን አሉ የቀብር ስርዓቱ በነሱ ይፈፀማል፡፡” በሚል ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡
የዳግሚት ደብረሊባኖስ ደብረአሚን ፃድቁ አቡነ ተ/ኃይማኖት ምክኃ ድንግል ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በበኩላቸው፤ የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ካህናቱም ልብሰ ተክህኖአቸውን አድርገው አለቃ አያሌው መኖሪያ ቤት መሄዳቸወንና ቤተሰቦቻቸው ቃለውግዘታቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ፍታት አታደርጉም ብለው እንደመለሷቸው ተናግረዋል፡፡ አንዳንዶቹም “እኛ ቃለ ውግዘታቸው ይጠበቅ ብለን እንጂ ከፓትሪያርኩ ጋር አብረን አይደለም አስክሬኑን ያላጀብነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የአለቃ አያሌ ደጋፊዎች ግን በዚህ አይስማሙም ምንም እንኳን ቤተሰብ ቃለውግዘታቸውን ለመጠበቅ ቢከለክል ካህናቱም ሆነ ወጣቶች ልብሳቸውን እንደለሰቡ የቀብር ስርዓቱ ላይ መገኘት ይችሉ እንደነበር፤ እነሱ ግን ከዚህ ይልቅ ቤተ መቅደሱን ጠርቅመው መሄዳቸው ከኃይማኖት አስተማሪነታቸው ካድሬነታቸው እንደሚብስ ነው ያሳዩት ብለዋል፡፡
በቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት እንደታዘቡት፤ ቤተ መቅደሱ ተጠርቅሞ ተዘግቷል፡፡ ለአለቃ አያሌው ቅኔ የሚቀኙ ወዳጆቻቸው የድምፅ ማጉያ አጥተው በቀበሌ ስብሰባ መጥሪያ ማይክራፎን ሲቀኙ ተስተውሏል፡፡
በዕለቱ በርካቶች በለቅሶ ኃዘናቸውን ይገልፃሉ ከቤተክርስቲያኑ አናት በሚገኘው ጉልሏት አጠገብ ባለው መስታወት አንድ ሰው መጋረጃውን ገልጦ ወደህዝቡ ሲመለከት ታየ፡፡
ማን ይሆን? በሚል ይህን የተመለከትን ስንነጋገር የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እንደሆኑ የተገመቱ ሰው መሆናቸው ታወቀ፡፡ በኋላም በተደረገው ማጣራት ካህናቱ ህሊናቸው እያወቀ የአለቃ አያሌው የቀብር ስርዓት ከውጭ እየተፈፀመ እነሱ ከውስጥ ሆነው የቤተመቅደሱን በር ጠርቅመው ቁጭ ብለዋል፡፡
ሊቀ ኅሩያን በላይ መኮንን በርካታ ቅኔ ለአለቃ አያሌው የተቀኙላቸው ሲሆን ከቅኔው መካከልም
የሦስት ሺህ ዓመት ታሪክሽን
እንደ ጁሊያን ቆጥሮ
በባህር ሀሳብ አትቶ በአቡሻ ክር ተምሮ
ታሪክ ከታሪክ አጣቅሶ
መፅሐፍ አመሳክሮ
ሳያስረዳን ወግ ባህልሽን አበጥሮ
ጥንተ ታሪክሽን አንጠርጥሮ
የተላቁ ሊቅ ያ አንደበቱ ታስሮ
በአምዓትሽ ዋዜማ
በሚሌኒየም ከተማ
አራት አይናውን አያሌውን ካጣነውማ
ምኑን ባተልን እማማ? ሲሉ ተቀኝተውላቸዋል፡፡
በመጨረሻም ለወ/ሮ ስምረት በተሰጣቸው እድል “አለቃ አያሌው የተበላሸውን የቤተክህነት ስርዓት እየታገሉ ያለምንም ደም ሰማዕት እየከፈሉ እዚህ አድርሰዋል፡፡ አሁንም ይሄን ተጋድሎ የሚመራና ለውጤት የሚያበቃ እንዲሰጠን እግዚአብሔር ልንለምነው ይገባል” ብለዋል፡፡
በአለቃ አያሌው ቀብር የእሳቸው ዘመድና ጓደኛ ከሆኑ አንድ ካህን በስተቀር አንድም የጠቅላይ ቤተክህነት መንበረ ፓትሪያርክ ሰራተኛ አለመገኘቱን ለመታዘብ ችለናል፡፡
ወደ አሜሪካና አውሮፓ ጉዞ የሚያደርጉት የቅንጅት አመራሮች ቪዛ አላገኙም
ወደ አሜሪካን አገር ጉዞ ለማድረግ በዝግጅት ላይ የነበሩት አምስት የቅንጅት አመራሮች ኢትዮጵያ ከሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ የመውጫ ቪዛ ባለማግኘታቸው ጉዞአቸው ሳይዘገይ እንደማይቀር ተገምቷል፡፡ ወደ አውሮፓ የሚጓዙት ሌሎቹ አምስት አመራሮችም እስካሁን ቪዛ እንዳላገኙ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡
ባለፈው እረቡ የግብዣ ወረቀታቸውን በመያዝ ኢትዮጵያ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ያመሩት ኢ/ር ኃይሉ ሻውል፣ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ዶ/ር ኃይሉ አርአያ አቶ ብሩክ ከበደ እና ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው በአጠቃላይ አምስት የቅንጅት አመራሮች የአሜሪካ መንግሥት የመግቢያ ፍቃድ ስላላከልን እሱን ከላከልን እንሰጣችኋለን ሲሉ መልሰዋቸዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ የአሜሪካ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚፈለገውን ክሊራንስ ያልላከ ሲሆን እሱ ተልዕኮ ቪዛ እስኪሰጣቸው ድረስ እየጠበቁ መሆኑ ታውቋል፡፡
በሌላ በኩል ወደ አውሮፓ ጉዞ የሚያደርጉት አቶ ሙሉነህ ኢዩኤል፣ ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም፣ አቶ አባይነህ ብርሃኑ፣ አቶ አስቻለው ከተማና አቶ ክፍሌ ጥግነህ የግብዣ ወረቀት የደረሳቸው ባለፈው ሳምንት ሲሆን ትክክለኛውን ምላሽ የሚያውቁት የፊታችን ሰኞ መሆኑን ለማወቅ ችለናል፡፡