Skip to content

Month: August 2007

የቅንጅት ምክትል ፕሬዚደንት ብርቱካን ሚደቅሳ መኪና ተሸለሙ

በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ፈረንሳይ ለጋሲዮን እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች የአካባቢያቸው ልጅ ለሆነችው ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ መኪና በመሸለም ደስታቸውን ገለጹ፡፡ በተጨማሪም ከእስር ለተፈቱት የቅንጅት አመራሮች የምሳ ግብዣ አደረጉ፡፡ በግብዣው ላይ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም እና ወ/ት ብርቱካን ንግግር አድርገዋል፡፡ ከቀኑ አምስት ሰአት ጀምሮ ነበር ግብዣውን ያዘጋጁት የአካባቢው ነዋሪዎች ጉድ ጉድ ማለት የጀመሩት፡፡ እንግዶቹ በተጠሩበት 7፡00 ሰአት ሲመጡ ግን አካባቢው በጩኅት ተናወጠ፡፡ ሁሉም ደስታውን በጭብጨባ መግለጽ ጀመረ፡፡

ዝግጅቱ ወደተደረገበት የቀበሌ እድር አዳራሽ ሲገባ አዳራሹ ውስጥ የተሰበሰበው ህዝብ ደስታውን የሚገልጽበት ስሜት ምናልባትም ከምርጫው በሓላ የመጀመሪያው የህዝብ ስሜት ሊባል የሚችል ነበር፡፡ ሁሉም ታዳሚ የቅንጅት አርማ የሆነውን የጣት ምልክት በማውጣት በፉጨት ደስታውን ይገልጻል፡፡
አዘጋጆቹ ንግግር ካደረጉ በሓላ የምሳው ግብዣ ሥነስርአት የተከናወነ ሲሆን ኣቶ ኃይሉ ሻውል ባለመገኘታቸው የተዘጋጀላቸውን ስጦታ በልጃቸው አማካኝነት ተሰተቸዋል፡፡

በተጨማሪም ለፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም ስጦታ የተሰጠ ሲሆን ይህ ለሁለቱም የተሰጠው ስጦታ የቅንጅት አርማ የሆነው የጣት ምልክት የተቀረጸበት ዱላ ሲሆን ‹‹በትረ መንግስት›› ሲሉም ሰይመውላቸዋል፡፡

ለአቶ ሙሉነህ ኢዩኤል እና አቶ አለማየሁ ለተባለ የአካባቢቸው ወጣት ተጨማሪ ሥጦታን ከሰጡ በኋላ ለወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ሽልማት እንዳላቸው ተናገሩ፡፡ ህዝቡ ሽልማቱን ለማወቅ በከፍተኛ ጉጉት የጠበቀ ሲሆን ‹‹ጀግና›› ላለት የአካባቢያቸው ልጅ የመኪና ቁልፍ አስረከቡ፡፡ ህዝቡ ደስታውን በጭብጨባ ገለጸ፡፡

ወ/ት ብርቱካን ምን እንደምትናገር የጠፋት በሚመስል ስሜት በሁለት እጆችዋ አርማውን እያሳየች ከወገቧ በመጎንበስ ምስጋናዋን ገልጻለች፡፡ ወደ መኪናዋም በመሄድ የተሸፈነችበትን ጨርቅ ገልጣ ተረክባለች፡፡

አዘጋጆቹም ሽልማታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ‹‹አቅማችን ፈቅዶ ሁላችሁንም ብንሸልም ደሰ ባለን ነበር… ግን ለሁላችሁም የሚሆን አንድ ስጦታ አለን እሱም ልባችን ነው›› ብለዋል፡፡

ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳና ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማሪያም ረዘም ያለ ንግግር አድርገው ፕሮግራሙ ተፈጽሟል፡፡

Tirunesh Dibaba wins thrilling 10,000m in Osaka

(AFP) Ethiopia’s Tirunesh Dibaba has come from the back of the field to retain her world 10,000 metres title in a thrilling race in Osaka overnight.

Dibaba trailed by some 50 metres with three-quarters of the race run but recovered to power past Turkey’s Elvan Abeylegesse on the bell and finish in 31 minutes 55.41 seconds.

Abeylegesse claimed silver ahead of third-placed American Kara Goucher as Dibaba, who has not run the distance since her 2005 win in Helsinki, remained on course for her second consecutive 10,000m-5,000m world double.

The victory looked impossible as Dibaba, who later revealed she was suffering from severe stomach pains, stumbled over tumbling compatriot Mestawat Tufa to drop to the back of the field.

But in scenes reminiscent of the 1982 hit ‘Chariots of Fire,’ the Ethiopian shrugged off her pain and the sweltering conditions to surge back into contention.

“That was the toughest race I’ve ever run,” Dibaba said. “I’ve won a lot of races but I’ve never been challenged so much because of this stomach problem.

“If it hadn’t been a matter of representing my country, I would have dropped out.”

Tufa, who holds the fastest time this year, was forced out by her fall and Japan’s Megumi Kinakawa threatened briefly despite having to stop to adjust a loose running shoe.

Dibaba’s elder sister Ejegayehu faded after a strong performance to finish seventh in an eventful race which brought the first day of competition to a close.

It was Ethiopia’s fifth consecutive gold medal in the event stretching back to 1999.

In 2005, Dibaba became the first woman to hold both the 5,000m and 10,000m world crowns at the same time.

But this was her first 10km event since then and she has been hampered by a leg injury this season, running against coaches’ advice in Paris to get into shape for her twin title defence.

Dibaba, 22, has a fierce rivalry over 5,000m with compatriot Meseret Defar, the Olympic champion and world record-holder, whom she will also face here.

The 10,000m world record is held by China’s Wang Junxia, coached by the doping-tainted Ma Junren, who ran 29:31.78 in 1993.

Indian company eyes Ethiopia to grow tea

Commodity Online

In a giant move, the Kanan Devan Hills Plantations (KDHP) company of India has decided to invest Rs 375 crore in Ethiopia to develop 10,000 hectares of tea plantation.

KDHP officials said while the new project would have a 70:30 debt equity ratio, some foreign private equity companies have shown interest to participate in the venture.

The participation of Tata Tea, which already holds 20 per cent equity in KDHP, would also be sought.

The debt component would be raised from Ethiopian banks which have shown interest in the project.

The project was initiated after Ethiopian ambassador visited the tea plantations of KDHP in Munnar, which are among the largest participatory management projects in the world, and asked company officials to explore the possibilities of setting up a similar project in Ethiopia, a traditional coffee country.

A team from KDHP surveyed several potential sites before identifying 10,000 hectares of land in the South Western Oromiya district of Ethiopia for the project.

The aerial survey of the land had been completed and reached KDHP just couple of days back, along with queries on the employment and economic generation potential of the project.

According to KDHP officials, the project would create direct employment for close to 10,000 people and accelerate export and economic development of the region.

The land, which is given on 90-year lease, will command a very nominal rent.

With the nominal rent and low cost of labour, the project should be able to produce 25 million kg of high quality CTC and orthodox teas in 10 years.

Since the country has no history of tea plantations, workers from India will train Ethiopian workers. The suitability of the land is testified by the proximity to Kenya and Tanzania, which are traditional tea growing countries.

The company is in the process of preparing a detailed project report.

Pakistan appoints new envoy to Ethiopia

Pakistan Times Wire Service

ISLAMABAD: Pakistan Friday appointed Khalid Hussain its new ambassador to Ethiopia, presently serving as ambassador to Sudan since July 2004, says a press release of Foreign Office.

Khalid Hussain holds a bachelor degree of LLB and Masters Degrees in Economics and Political Science.

He joined foreign service of Pakistan on March 21, 1977 and held various diplomatic assignments in Pakistan Missions abroad.

He served in Doha (1981-1983), Jeddah (1985-1988), Mexico (1988-1991), Abu Dhabi (1994-1997) and Tripoli (1997-2001).

Khalid Hussain served at headquarters as Section Officer (1978-1981 & 1983-1985), Director (1991-1994) and Director General (2002-2004).

Ethiopian Electric Power Corp. signs power supply contracts with Chinese firms

The state-owned Ethiopian Electric Power Corporation (EEPCo) on Friday signed six contracts with three Chinese companies, providing for expanding electricity supply services to rural towns and villages.

The contracts amount to more than 124 million U.S. dollars, said EEPCo General Manager Mihret Debebe.

The construction of a 400 kv Bahir Dar-Debremarkos-Addis Ababa, a 230 kv Tekeze-Endaselassie-Humera, a 230 kv Bedele-Mettu and a 230 kv Fincha’a-Gedo-Gefersa transmission stations and line installations are among the projects, Mihret said after a signing ceremony.

He said 85 percent of the funds have been secured from the Chinese government in loan, adding that the balance will come from government coffers.

Mihret said the projects should be implemented according to timetable and then contribute significantly to the country’s development endeavors.

The projects are due to complete within 18 months, he said.

Source: Xinhua

Over 15,000 people attended Aleqa Ayalew's funeral

Ethiopian eminent scholar and theologian Aleqa Ayalew Tamiru was buried on Thursday at Tekle Haimanot Church in Addis Ababa in the presence of over 15,000 people. Read the full report below in Amharic by an Ethiopian Review correspondent in Addis Ababa:


የአለቃ አያሌው የቀብር ስነ ስርዓት በተክለ ኃይማኖት ቤ/ክርስቲያን ተከናወነ፡፡


የአቡነ ጳውሎስን ስርዓት ከእምነትነቱ ይልቅ የካድሬ ስራ የሚሰራበት ነው በማለት በተቃውሞ ሰማዕት ሆነው የኖሩት አለቃ አያሌው ሕይወት ካለፈ በኋላ ሐሙስ ነሐሴ 17 ቀን 1999 ዓ.ም በአቡነ ተክለ ኃይማኖት በተከናወነው የቀብር ስነ ስርዓታቸው ላይ ቁጥሩ ከ15 ሺህ በላይ የሚገመት ሕዝብ ቢገኝም ካህናቱና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በዝማሬ አስክሬናቸውን ሳያጅቡ ቀሩ፡፡ በተጨማሪም የድምፅ ማጉያ እንኳን ሳያወጡ የቤተ መቅደሱን በር ዘጋግተው ጠፉ፡፡

የአለቃ አያሌው የቀብር ስነ ስርዓት በደብረሊባኖስ ገዳም ይፈፀማል ተብሎ የነበረ ሲሆን አዲስ አበባ በሚገኘው ተክለ ኃይማኖት ቤ/ክርስቲያን እንደሚፈፀም ከተሰማ በኋላ ቤተሰቦቻቸው፣ ተከታዮቻቸውና ኃዘን የተሰማቸው በሙሉ በስፍራው ተገኙ፡፡

እንኳን ለአለቃ አያሌው ይቅርና አቅሙ የጎለበተ ባለኃብት ሲሞት በቤተክስቲያኑ የሚገኙ ካህናትና ወጣቶች ልብሳቸውን ለብሰው አስክሬን ሲያጅቡና ፍታት ሲፈቱ ይስተዋል የነበረ ሲሆን በእለቱ ግን የአለቃ አያሌው የቅርብ ወዳጆች የሆኑ ካህናት ብቻ በቤታቸው ፍታት አድርገውለላቸዋል፡፡

በቀብሩ ቦታ የነበሩ አንዳንድ የእምነቱ ተከታዮች እንደተናገሩት “ምድረ የቤተ ክህነት ሰራተኛ ዛሬ ካድሬነቱ ታወቀ፡፡ የአለቃ አያሌው አስክሬን መሸኘት ያለበት በዚህ መንገድ ነበር? ምንም አይደለም ለሁሉም አንድ ቀን ያስተዛዝባል” ሲሉ ተሰምተው ነበር፡፡

የአለቃ አያሌው የበኩር ልጅ ወ/ሮ ስምረት አያሌው ስለሁኔታው ሲናገሩ “አባታችን አሁን ባለው የአባ ገ/መድህን (አቡነ ጳውሎስ) አስተዳደር ስር ያሉ ካህናት ፍትኃት እንዳያደርጉልኝ በማለታቸው ከልክለናል፡፡ ይህን ያደረግነው የአባታችንን ቃለ ውግዘት ለመጠበቅ ስንል ነው፡፡ ያስተላለፈውን ቃለ ውግዘት የሚያከብሩና የሚፈፅሙ በርካታ ምዕመናን አሉ፡፡ የቀብር ስርዓቱ በነሱ ይፈፀማል፡፡” በሚል ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡

የዳግሚት ደብረሊባኖስ ደብረአሚን ፃድቁ አቡነ ተ/ኃይማኖት ምክኃ ድንግል ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች በበኩላቸው የደንብ ልብሳቸውን ለብሰው ካህናቱም ልብሰ ተክህኖአቸውን አድርገው አለቃ አያሌው መኖሪያ ቤት መሄዳቸውንና ቤተሰቦቻቸው ቃለውግዘታቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ፍታት አታደርጉም ብለው እንደመለሷቸው ተናግረዋል፡፡ አንዳንዶቹም “እኛ ቃለ ውግዘታቸው ይጠበቅ ብለን እንጂ ከፓትሪያርኩ ጋር አብረን አይደለም አስክሬኑን ያላጀብነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የአለቃ አያሌው ደጋፊዎች ግን በዚህ አይስማሙም፡፡ ምንም እንኳን ቤተሰብ ቃለውግዘታቸውን ለመጠበቅ ቢከለክል ካህናቱም ሆነ ወጣቶች ልብሳቸውን እንደለሰቡ የቀብር ስርዓቱ ላይ መገኘት ይችሉ እንደነበር፤ እነሱ ግን ከዚህ ይልቅ ቤተ መቅደሱን ጠርቅመው መሄዳቸው ከኃይማኖት አስተማሪነታቸው ካድሬነታቸው እንደሚብስ ነው ያሳዩት ብለዋል፡፡

በቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት እንደታዘቡት ቤተ መቅደሱ ተጠርቅሞ ተዘግቷል፡፡ ለአለቃ አያሌው ቅኔ የሚቀኙ ወዳጆቻቸው የድምፅ ማጉያ አጥተው በቀበሌ ስብሰባ መጥሪያ ማይክራፎን ሲቀኙ ተስተውሏል፡፡

በዕለቱ በርካቶች በለቅሶ ኃዘናቸውን ይገልፃሉ፡፡ ከቤተክርስቲያኑ አናት በሚገኘው ጉልሏት አጠገብ ባለው መስታወት አንድ ሰው መጋረጃውን ገልጦ ወደህዝቡ ሲመለከት ታየ፡፡

ማን ይሆን? በሚል ይህን የተመለከትን ስንነጋገር የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ እንደሆኑ የተገመቱ ሰው መሆናቸው ታወቀ፡፡ በኋላም በተደረገው ማጣራት ካህናቱ ህሊናቸው እያወቀ የአለቃ አያሌው የቀብር ስርዓት ከውጭ እየተፈፀመ እነሱ ከውስጥ ሆነው የቤተመቅደሱን በር ጠርቅመው ቁጭ ብለዋል፡፡

ሊቀ ኅሩያን በላይ መኮንን በርካታ ቅኔ ለአለቃ አያሌው የተቀኙላቸው ሲሆን ከቅኔው መካከልም

የሦስት ሺህ ዓመት ታሪክሽን
እንደ ጁሊያን ቆጥሮ
በባህር ሀሳብ አትቶ በአቡሻ ክር ተምሮ
ታሪክ ከታሪክ አጣቅሶ
መፅሐፍ አመሳክሮ
ሳያስረዳን ወግ ባህልሽን አበጥሮ
ጥንተ ታሪክሽን አንጠርጥሮ
የተላቁ ሊቅ ያ አንደበቱ ታስሮ
በአምዓትሽ ዋዜማ
በሚሌኒየም ከተማ
አራት አይናውን አያሌውን ካጣነውማ
ምኑን ባተልን እማማ?

ሲሉ ተቀኝተውላቸዋል፡፡

በመጨረሻም ለወ/ሮ ስምረት በተሰጣቸው እድል “አለቃ አያሌው የተበላሸውን የቤተክህነት ስርዓት እየታገሉ ያለምንም ደም ሰማዕት እየከፈሉ እዚህ አድርሰዋል፡፡ አሁንም ይሄን ተጋድሎ የሚመራና ለውጤት የሚያበቃ እንዲሰጠን እግዚአብሔር ልንለምነው ይገባል” ብለዋል፡፡

በአለቃ አያሌው ቀብር የእሳቸው ዘመድና ጓደኛ ከሆኑ አንድ ካህን በስተቀር አንድም የጠቅላይ ቤተክህነት መንበረ ፓትሪያርክ ሰራተኛ አለመገኘቱን ለመታዘብ ችለናል፡፡