Assimba.org has issued the following press release in Amharic regarding comments by Ato Dawey Ibrahim, former chairman of the Ethiopian Workers Confederaiton. (Amharic font can be downloaded here).
አቶ ዳዊ ኢብራሂም በአሲምባ የውይይት መድረክ ላይ ለሰነዘሩት አስተያየት የተሰጠ ምላሽ
በስደት የሚኖሩ ወገኖች ከመካከላቸው አንዱ የማይመስል ሲያወራ “ስደት ለወሬ ያመቻል” ይላሉ። እንዲያም ሲል ተንኮል የተሞላበት ፈጠራን ሲገነዘቡ “ጅብ ከማያቁት ሀገር ሄዶ ቆርበት አንጥፉልኝ አለ” ይላሉ። ከጥቂት ቀናት በፊት “የኢሕአፓና ትርምሰ ዑደትና የኢትዮጵያ ሠራተኞች” በሚል ርዕስ በአቶ ዳዊ ኢብራሂም ተጽፎ በአንዳድ ድረ-ገጾች ከተበተነ በኋላ በአንዳንድ የፓልቶክ መድረኮች ይህን ጽሁፍና ያአሲምባ ድረ-ገጽንና ሌሎችን በሚመለከት በኛ ግምት ኃላፊነት የጎደለውና ከዕውነት የራቀ ተራ ወሬ ሲነዛ በመክረሙ በጣም አዝነናል። በተለይም አቶ ዳዊ ከሦሥት ወራት በፊት በአሲምባ የውይይት መድረክ የዓለም አቀፍ የሠራተኞች ቀንን አንተርሶ የአቀረብናቸውን በስደት የሚገኙ የቀድሞ ሠራተኞች መሪዎችን አስመልክቶና የአሲምባ የውይይት መድረክን ተልዕኮ አጣመው የራሳቸውን ትርጉም በዘፈቀደ ለማቅረብ በመሞከራቸው ይህንን መግለጫ እንድናወጣ ተገደናል። ከዚህም በላይ የሳቸውን ጽሁፍና በዕለቱ ከእንግዶቻችን ጋራ ያደረግነውን ቀለ-መጠየይቅ እንዳለ እቅርበን ፍርዱን ለአንባብያን እንተወዋለን።በመጀመሪያ የአሲምባ ውይይት መድረክ እንዴትና ለምን ተመሠረተ?
አቶ ዳዊ እንደጻፉት የአሲምባ የውይይት መድረክ የኢሕአፓ ተለጣፊ አይደለም። በጥቂት ሀገር ወዳዶች የሚንቀሳቀስ ከማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ ነጻ የሆነ ፤ ዘለቅ ብሎ የተገለጸውን ዓላማ ይዞ የሚንቀሳቀስ መሆኑን እንዲገነዘቡልን እንወዳለን። ይህንንም ስንል ግን ኢሕአፓ የኢትዮጵያ የቁርጥዬ ቀን ጀግኖች በደም አጥንታቸው የገነቡት ዕውነተኛ ሕዝባዊና ኢትዮጵያዊ ድርጅት መሆኑን ላንዴም አንጠራጠርም። ኢትዮጵያዊነቱን ለሚጠይቁ በድረ-ገጻችን በየቀኑ እያደገ ያለውን የሰማዕታት ስም ዝርዝርና አጠር ያለ ታሪክ ላስተዋለ ፣ በስማቸው ብቻ በኢትዮጵያ ያሉትን ብሔሮች፣ ሃይማኖቶችና የሥራ ዘርፎችን እንደሚያንጸባርቁ መረዳት ይችላሉ። ይህም ራሱ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሞላ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሶ በደሙ የጻፈው ዕውነተኛ ታሪኩ ነውና ዛሬ የትግራይ ተወላጅ ብቻ ለትግራይ ሕዝብ ወይም የኦሮሞ ተወላጅ ብቻ ለኦሮሞ ሕዝብ ወዘተ,,ሃሳቢና ተቆርቋሪ እንደነበሩ አድርገው ሊያስተምሩን የሚዳዳቸውን ሁሉ ከሚያስፋፉት ጥላቻና ድንቁርና ጋር እርቃናቸውን ያስቀረዋል።
መድረኩም ሆነ ድረ-ገጹ በተመሠረቱበት ወቅት የወያኔ መንግሥት በዘጠና ሰባቱ ምርጫ ማግስት ያታልልበት የነበረውን የዲሞክራሲ ሽርጥ አውልቆ ጥሎ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ድሮውንም ግልጽ የነበረውን ፋሻሽታዊ ገጽታውን ይዞ በዓለም መድረክ ላይ ብቅ ያለበት የቀውጢ ጊዜ ነበር። ይህም ሁኔታ አዲሱ ትውልድ ለሚጠብቀው መራራ ትግል፤ ሊመረምረውና ሊማርበት የሚገባ፤ በዛሬዪቱ ኢትዮጲያችን የተንሠራፋው የዘረኞች፤ የጎጠኞችና፤ የሆዳሞች መንጋ አቶ ዳዊ እያደረጉት እንዳሉት ሁሉ የሚከላልሰውን፤ በጀግንነት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ባላቸው ፍቅር፤ ለፍትኅና ለዲሞክራሲ፤ በውድ ሕይወታቸው ምስወዕትነት ያዳበሩትን የዚያን ትውልድ ጅግኖች የትግል ታሪክ፤ ሳይቀነስ፤ ሳይበረዝና ሳይደለዝ፤ አሁንም በሕይወታቸው ከሚኖሩ የትግል ጓዶቻቸው፤ የሥራ ባልደረቦቻቸው፤ ወዳጆቻቸውና ቤተ-ዘመዶቻቸው ተሰባስቦ፤ ዕውነቱ በትክክል እንዲቀርብ ለማድረግ የጀመርነው ውጥን ወይም ፕሮጀክት ነው።
ከዚህም ሌላ ይህ መድረክ ባለፉት አርባ ዓመታት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍትኃዊ ነፃነት ሲታገሉ ለወደቁ፤ በደርግ ፋሺሽታዊ ሥርዓት በቀይ ሽብር ሠለባ ለሆኑ፤ ለሕዝባችን ነፃነት እንታገላለን በሚሉ ጠባብ ብሔረትኞች ለተጨፈጨፉ፤ በፅናታቸው፤ በኢትዮጵያዊነታቸው ተግዘው ለማቀቁና አሁንም በየጉድባው አሣራቸውን ለሚቆጥሩ፤ ከምድረ-ገጽ ደብዛቸው ለጠፉ የቁርጥዬ ቀን የኢትዮጵያ ጀግኖችና በዓለም ዙሪያ ካለውዴታቸው ተሰደውና በሀገር ቤትም አንገታቸውን ደፍተው ለሚኖሩ ታጋዮች መተሰቢያ እንዲሆን አስበን የመሠረትነው እንጂ አቶ ዳዊ እንደለጠፉብን ሴረኞች አይደለንም። ሥራችንም ሃላፊነት የተሞላው ለመሆኑ በግልጽ በውይይት መድረኩም ሆነ በድረ-ገጹ የሚንጸባረቅ ስለሆነ በተዘዋዋሪም መንገድ ጸረ-ቅንጅት አድርገው ሊቀቡን የሚሞክሩትን ሁሉ አንቀበላቸውም።
እንግዲህ ይህንን ግልጽ ካደረግን በኋላ በአቶ ዳዊ ጽሁፍ ላይ በጥቅሉ የተገነዘብነው ነገር ቢኖር የደርግ ፋሺሽቶችና ግብረ-አበሮቻቸው ያፈሰሱትን ደም ከጃቸው ያነጹ እየመሰላቸው በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሏቸውን፤ ያረዷቸውን፣ በዘይት የቀቀሏቸውን ኸረ ስንቱን ይገባቸዋል ብለው የሚያቅራሩትን ያክል በሚያሳዝን ሁኔታ እኚህም ሰው በዚህ ጽሁፋቸው በአጠቃላይ የፋሺሽቶች ሰለባ የሆኑትን ወገኖቻችንን የሙት ወቃሽ መሆናቸውን ነው። በአሲምባ ደግሞ ይህን ዓይነት የተንሸዋረረ ታሪክ የሚያቀርቡትን ለማስተካከል ስለቆምን እንዳለፉት ሃያና ዓመታት ተድበስብሶ የሚቀር የለምና እንግዲህ አረፍ ይበሉና እስኪ ከላልሰው ካቀረቡት የሰማዕታት ታሪክ መካከል ጥቂቱን እንስተን በጥሞና እንወያይ። ከዚያ በፊት ግን እንዲያውቁልን የምንሻው ኢህአፓ በዓለም ዙሪያ ሕጋዊ ጽ/ቤቶች ፣ የራዲዮ ጣቢያዎች ፣ የራሱ ድረ-ገጽና “ዲሞክራሲያ” ልሣኑ ያለው ድርጅት ስለሆነ በድርጅቱ ያቀረቡትን ክስ መልስ እንደማይነፍገዎ እንተማመናለን።
በመድረካችን ባሉት ቀን ቀርበው ውርጅብኝ ያወረዱባቸው እንግዶቻችንም እንዲሁ መልስ የሰጥዎታል ብለን እንገምታለን። ከዚህ ጽሁፍም ጋር አባሪ አድርገን ዝግጅቱን ያቀረብን ዕለት ውይይት ቅጂ እንደሚያመለክተው የእርስዎ ስም በመጥፎ አልተነሳም፣ ቅጂውን እንዲያዳምጡም እንጋብዞታለን። አንባቢያንም የአቶ ዳዊ ኢብራሂምን ጽሁፍ የኛን መልስ እንዲሁም የውይይቱን ቅጂ በማድመጥ በዕለቱ የውይይቱ መንፈስ ምን እንደነበር ያራሳችሁን ግንዛቤ እንደምትወስዱ አንጠራጠርም።
የምንተችባቸው ጽንሰ ሃሳቦች
1. በእርስዎ የደበዘዘ መነጽር ተመልክተው ደርግ በ1968 ዓ/ም ዲሞክራሲያዊ እንደ ነበር ሁሉ በዚያን ሜይ ዴይ የፈጸመውን እልቂት በኢህአፓ ተንኳሽነት እንደሆነ አድርገው ለማቅረብ መሞከርዎ የታሪክ ክለሳ ነው። ከጻፉት ለመጥቀስ “…በ1968 ዓ/ም ሜይ ዴይ በሚከበርበት ዕለት በዓብዮት አደባባይ ሠራተኞችን የማስመታትና ከሠራተኞች መሞት ስለደርግ ጨካኝነት ማስረጃ ለመፈልቀቅ የፈጸመችው መሠሪ ተግባር… ሠራተኛው ሕንፃ ላይ ለተጠመዱ መትሪየሶች የእሳት ዕራት እንዲሆን አደረገች…” ብለው የዚያን ትውልድ ሰማዕታት ወቃሽ ሆነው ተሰልፈዋል።
ዛሬ ሀገራችን እንደ ሀገር የምትቀጥልበትን ሁናታ በጥያቄ ውስጥ ያስገባውን ወያኔን አስወግደን በምትኩ ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለመመሥረት ኢትዮጵያዊ ኃይሎችን ወደ አንድ ወገን እንዴት ማምጣት የቻላል ብለው ሀገር ወዳዶች ከሊቅ እስከ ደቂቅ በሚጨነቁበት ወቅት እርስዎ ታሪክን የሚያውገረግር ተራ ወሬ የአሲምባንም ሚና ያጣመመ አጀንዳ ሲያሲዙን ማንን እየጠቀሙ መሰለዎት? ከፍተኛ መስዋዕትነት እየተገበረበት ያለን ሕዝባዊ የዲሞክራሲ ትግል እየጠቀሙ መሰለዎት? ኢሕአፓ የወያኔን ጠባብነት አውቆ ታጋዮቹን የገበረው ዛሬ አይደለም። ገና ከመነሻቸው ከደርግ ጊዜ ጀምሮ ነውና ያም ጥፋቱ ነው ብለው ያስተምሩን ይሆን? ከ1991 ዓ/ም ወያኔዎች ደብዛቸውን ላጠፏቸው አባላቱ፣ በአደባባይም ለገደሏቸው ታጋዮቹ ጥፋቱ የኢሕአፓ ነው ይሉን ይሆን?
ለማንኛውም ከላይ ከጽሁፎ ለጠቀስነው ዕውነታውን እንመልከትና በዚያን ቀን ማለትም ሜይ ዴይ 1968 ዓ/ም ልክ በ1997 ዓ/ም የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን ምንነት አንቀርቅቦ እንዳወቀ ሁሉ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሠራተኛውንም ጨምሮ የደርግን ምንነት በግብሩ የተረዳ ስለነበር በዚያን ዕለት ሠራተኛው “ጊዜያዊ ሕዝባዊ መንግሥት አሁኑኑ!” የሚሉ መፈክሮችን አንግቦ መውጣቱ፤ ብሎም በጊዜው የሕዝቡን ዋይታ ያንጸባርቅ የነበረውና ሕዝቡንም አደራጅቶ ያታግል የነበረ የሕዝቡ ፓርቲ ኢህአፓ ብቻ ስለነበር፤ “ኢህአፓ ፓርቲያችን ነው!” በሎ መፈክሩን በአደባባይ የዞ መውጣቱ ያስቆጣቸው የደርግ ባለሥልጣናት የፈጸሙት ይቅርታ የሌለው ጭፍጨፋ ነው።
ለመሆኑ እርስዎ በጽሁፎ ኢህአፓ ያንን ቀን የደርግን ፋሺሽትነት ለማስመስከር ተጠቀመበት የሚሉን ከዚያ በፊት ደርግ በሥልጣን ከወጣ ጀምሮ በግልጽ ያስመሰከረውን ካለፍርድ ሲሻው በአዋጅ የፍየል ወጠጤ በራዲዮ እያዘመረ ይገድል እንደነበር ፤ አለያም የደርግ አባላትና ተጠሪዎቹ በደረሱበት ቦታ ተቃዋሚ ተብለው የሚጠረጠሩትን የሠራተኞች ተሟጋቾችንም ጨምሮ ማለት ነው ይረሽኑ ያሰቃዩ እንደነበር እረስተውት ነው? ወይስ ዛሬ ለፖለቲካ ሥልጣን ራስን ለማመቻቸት ኢሰፓዎችን ማሞካሸት ይሻላል ብለው ገመቱ? ወይስ ተልኮዎ ረቀቅ ያለ ኢትዮጵያዊው ኃይል ወዳንድ እንዳይመጣ የመከፋፈያ መርዝ መርጨትዎ?
እንግዲህ ታሪክን እንደ ታሪክነቱ እንዲከለስ መፍቀድ ለወደፊት ለምናደርገው ትግል ጥራትን ከማሳጣቱም ሌላ ስህተቶች እዲደገሙ መሠረት ስለሚሆኑ በኛ በኩል እንዲህ ያለውን የውሸት ዘመቻ እየሰማን ዝም ማለቱ ጉዳቱ እንጂ ጥቅሙ ስላልታየንና የርስዎንም የመዋሸት ችሎታ ህዝቡ እዲረዳ በማድረግ በመድረካችን የተካሄደውን ውይይት ቅጂ እንዳለ በማቅረብ እንዴት ሊያጣምሙት እንደሚሞክሩ አሳይተን የርስዎና የመሳሰሉትን የተዛቡ አስተያየቶችን እንደዕውነታ ወስደን የተሳሳተ ግምት ውስጥ ከመግባት በፊት ሁሉም ወገን የሚያቀርበውን ተመልክቶ ትክክለኛው የትኛው እንደሆነ ከድምዳሜ መድረስ እንደሚቻል ለማሳየት ነው።
የአቶ ዳዋን የ1968ቱን የሜይ ዴይ ታሪክ እንኳ ይሁን ብለን ብንቀበል ፣ በዛሬዎቹ የጎጠኞች መንግሥት ከ1997 ዓ/ም በኋላ የሕዝብ ድምፅ ይከበር ብለው ሰላማዊ ሠልፍ ሰለወጡ ብቻ ለተጨፈጨፉ ወገኖች ተጠያቂዎቹ ታሥረው የነበሩ የቅንጅት መሪዎች ናቸው የሚሉንን ልንሰማ ነው ማለት ነው።
ከታሪክ ያልተማሩ ታሪክን ይደግማሉና በ1968 የተፈጸመን በደል ትክክለኛ ምንጩንና በጊዜው የነበረውን ሁኔታ በትክክል እንዳይጤን አውቀውም ሆነ ሳያውቁት ያ ትውልድ ከልቡ አምኖ ለወገኖቹ በቅንነት መሥዋዕትነት የከፈለበትን ታሪክ መከላለስ አዳጋው የዛሬው ትውልድ የአለፈውን ትውልድ ድክመቱን ሳይደግም ግን ከጠንካራ ጎኑ በተለይም ለሀገርና ወገን ያለውን ፍቅር እዲሁም በራስ መተማመንና ጀግንነትን ሰንቆ ለኢትዮጵያችን ያለናት እንደ አባቶቻችን እናቶቻችን እኛው በኢትዮጵያ የምንኮራ ሀገር ወዳዶች ብቻ መሆናችንን በቶሎ ተገንዝቦ እንዳይታገል ነገሮች እየተምታቱበት ፈራ ተባ እያለ እንዲጃጃልና ሀገሩን እንዲነጠቅ ማድረግ መሆኑን ልናስገነዝብ እንወዳለን።
ይህ ደግሞ ኢህአፓ ነበርን፤ ታሪኩን ከኛ የበለጠ የሚያውቅ ላሳር ነው እያሉ የዚያን ትውልድ ሰማዕትነት እያደባዩ ድርሳነ ክህደት የሚያነበንቡትንም ስለሚመለከት ፤ ሁሉም አንድ እንዲረዱልን የምንፈልገው ነገር ቢኖር፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጊዜና ሁኔታዎች ሲመቻቹለት የኢህአፓንና የዚያን ትውልድ መስዋዕትነት ዕውነተኛውን ታሪክ እንደሚናገር በፍጹም አንደማንጠራጠር ነው።
2. የዚህ ምላሽ ዋና ዓላማ አቶ ዳዋ ኢብራሂም የጻፉትን 6 ገጽ የታሪክ ክለሳ መስመር በመስመር ልንተችበት ሳይሆን ቢያንስ አንድ ሁለቱን አንስተን የቀዳዳውን ስፋት በህዝብ መነጽር እንዲታይ በማድረግ የዚያ ትውልድ ታሪክ በብዙ ሊመረመርና ሊጠና የሚገባው፤ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በአብዛኛው የምናየው ታሪክን የሚያንቋሽሽ ወሬና አሉባልታ እንዴት ወደ ሕዝቡ ዓዕምሮ ሰርፆ እንዲገባ እየተቀረገ እደሆነ ለማሳየት ብቻ ስለሆነ በዚህ ክፍል አንድ ነጥብ አንስትን እንተችበትና ወደ ማጠቃለያችን እንሄዳለን።
አቶ ዳዊ ኢብራሂም ሲጽፉ “…ከ1967 እስከ 1969 ዓ/ም ድረስ ኢህአፓ በኢትጵያ ሠራተኞችና ማህበሮቻቸው ያደረሰችው ጉዳት ይቅር የማይባል ዘግናኝና አሳዛኝ እንደነበር…” ይሉና ቀጠል አድርገውም “…ሥዩም ከበደ የኢህአፓ የትጥቅ ትግል (እነሱ እንደሚሉት የጥቃት መከላከያ) ዋና መሪ ስለነበር የሠራተኛውን ብሔራዊ ጽ/ቤት የግድያ ዕቅድ ማውጫ፤ …የመቺ ቡድን መጠለያና መሸሸጊያ፤ …የማህበሩ ሕንፃ ከመሬት በታች ምድር ቤት ስለነበረው የጦር መሳሪያ መደበቂያ ምቹ ሥፍራ አድርጋ ቆየች…” ብለው ይቀጥላሉ። ምናለ የሚመስል እንኳ ቢያወሩልን። ሥዩም ከበደና ኢህአፓ ያበዱና ሞትን ያሸተቱ ካልሆነ በቀር፣ በጊዜው ደርግ የሠራተኛውን ድርጅታዊ ነፃነት በራሱ ታማኝ መሪዎች ለመተካት እየታገለና እያስፈራራ እርስዎም ያልካዱት ደጋፊ ነን የሚሉ ውሁዳን መሪዎች እንደ ጣዕም ያለው እሸቴ አይነቱ ነገር አቀባዮች በሚርመሰመሱበት ጽ/ብት ውስጥና፤ ከሁሉም በላይ የደርግ የስለላ መረብ 24 ሰዓት በዓይነ ቁራኛ የሚጠበቀውን ህንፃ ወደ ምሽግነት ኢህአፓ ቀየረችው በሎ እንደ ታሪክ ማውራት የሚያሳፍር ቅጥፈት ነው። ለርስዎ አፈርንልዎ።
ሌላው ደግሞ ያኔ ደርግ ኢህአፓዎችን እያደነ ሲገድል “ሥርዓተ-አልበኞች” እያለ እኒያን ሰማዕታት ሰብአዊ ገጽታ እንዳይኖራቸው ግን ግዑዝ ከም አርዮስ መልክ በመቀባት፤ ቢገደሉም ምንም አይደለም አይነት ነገር በሕዝቡ እዕምሮ ይቀርፅበት የነበረውን የጭካኔ ቋንቋ ከሠላሣ ዓመት በኋላ ይዘው ብቅ ሲሉ ዛሬም እንደ ትላንቱ የሚኮንኑት መሠረታዊ የስብአዊ መብቶችን ፤ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ካለገደብ መጠየቅን፣ የመሰብሰብ፣ የመጻፍ፣ የመናገር፣ በነፃ የመደራጀት መብቶች መረጋገጥን፤ ባጠቃላይ የህግ የበላይነት የሚረጋገጠባት ለሁሉም ኢትዮጲያዊ እኩል የሆነች ሕዝባዊ ሥርዓት የተመሠረተባትን አንድ ኢትዮጵያን እንደሆነ ይገንዘቡልን።
ሊነግሩን የፈለጉት በዚያን ጨለማ ዘመን ካለፍርድ በነፃ እርምጃ በቀይ ሽብር የታጨዱትን ሰማዕታት ይገባቸዋል ነው። ይህንንም ዓይነት የተንሻዋረረ አመለካከት እንደርስዎ ያለ ስለሚያስፋፋው ዛሬም ስለፖለቲካ እስረኞች እንኳ አንዳንድ መሪዎች ነን የሚሉ ሲያወሩ ከ1991 ዓ/ም ጀምሮ ካለአግባብ ታሥረው ደብዛቸው የጠፉ በአብዛኛው ኢህኢፓዎች የት አሉ እንኳ ብሎ ለመጠየቅ ያልቻሉ የተዳነዙ ሰዎች ስለሕግ የበላይነት ሊደሰኩሩብን ሲያምራቸው እያነን ነው። በኛ አመለካከት የህግ የበላይነት ሲባል እንኳንስ በጸረ-ወያኔነት የታገለና ያታገለ በመደዳው ሕዝብ የጨረሰው መንግሥቱ ኃ/ማርያም እራሱ እንኳ ካለህዝባዊ ፍርድ መነካት የለብትም ባዮች ነን። ለዚህም የርስዎን ጽሁፍ አንተርሰውም ሆነ በሌላ ጊዜ የአሲምባ የውይይት መድረክ ስለቅንጅት መሪዎች እንደማናስብ አድርጎ ለማሳየት ቢነዘብንም ትግላችን አሁንም ወደፊትም በሃገራችን ዳግም ቀይ ሽብር እንዳይመጣ በሁሉም መሪዎች ነን በሚሉ ጭንቅላት ውስጥ ለዘለዓለም እንዲደውል የምንፈልገውም ለዚህ ነው። የማንም ይሁን የማን ድርጅት ወይም አማለካከት ደጋፊ ተብሎ ወደ እሥር የማይወረወርበት፣ የማይገደልበት ሀገር መመሥረት እድንችል የርስዎን ዓይነት ድንቁርና ማጥፋት አለብን በለን አበክረን እናምናለን። ምክንያቱም ለሌላ ማዓት ያዘጋጀናልና።
በአንድ ቦታ ኢህአፓ “…የሠራተኛውን የማህበራት መንፈስ እስከወዲሁ ድረስ እንዲደበዝዝ ከፍተኛ ወንጀል…” ብለዋል። የሠራተኛውን የማህበራት መንፈስ ያደበዘዘው ኢህአፓ ሳይሆን የሠራተኛውን በነፃ የመደራጀት መብት በመፃረር ሥልጣንና ኃይልን በመጠቀም የሠራተናውን ማህበራት በራሳቸው ምስል ሊቀርጹ የተነሱ የዚያን ጊዜ የደርግ ኢሠፓዎችና የዛሬዎቹ በክልልና በዘር የሚያናክሱት ወያኔዎች መሆናቸውን መረዳት የማይፈልግ ራሱን ያመመው ብቻ ነው።
ለማጠቃለል፥
እኛ የአሲምባ የውይይት መድረክ መሥራቾች ባለፉት 30 ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ትንንቅ ያለፉና ሚና የነበራቸው ግለ ሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ከተሠሩ ስህተቶች አንዳቸውም ነፃ ነን ብለው እጃቸውን እንደጲላጦስ መታጠብ እንደማይችሉ እናምናለን። በዓፄው ዘመነ-መንግሥት ፤ በደርግ ፋሻሽታዊ ሥርዓትና በዛሬዎቹ ጠባብ ብሔረተኞች ጊዜ፤ በምንግሥት ደረጃ ጥቂት ቡድኖች ራሳቸውን በሥልጣን ተክለው ለዘላዓለም ለመኖር ሲፍጨረጨሩ የፈጸሙትን ጥፋት፣ በሕዝብ ያደረሱትን በድልና ግፍ ከሕዝቡ ለመከላከል ሲውተረተሩ እንደ ኢህአፓ ያሉ ሕዝባዊ ድርጅቶች የፈጸሙትን ስህተቶችና ከሚደርስባቸው ምት የተነሳ ያሳዩትን መዝረክረክና ግድፈት በማንኛውም ዓይነት መሥፈሪያ ለማነፃፀር መሞከር ራሱን የቻለ ስህተት ነው በለን እናምናለን።
ሌላው ደግሞ ልንገነዘበው የሚገባ ነገር ቢኖር ከ30 ዓምታት በፊት ሲውተረተር ራሱን ገምግሞ አነሰም በዛም የሰራቸውን ስህተቶች ለማረም የሞከረና አቅጣጫውን በይፋ የቀየረ በጊዜው ከነበሩ ኃይሎች በድርጅትም ሆነ በግለ-ሰብ ኢህኢፓ ብቻ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህንን ሁሉ ካልን በኋላ የአቶ ደዋ በኢህአፓ ላይ እጣታቸውን መቀሠር በአሁኑ ወቅት ጠቀሜታውና ዓላማው ምን ይሆን ብለን ስንጠይቅ ያገኘነው መልስ ምንም ነው። ሀገራችን እንድትፈርስ እየተመቻቸች፣ የህዝባችን ውስጣዊ ቅራኔው ተጋግሞ እርስ በእርስ ተፋጦ ወደማይሆን አቅጣጫ እየተገፋ እያለና ከመቼውም የበለጠ ሀገር ወዳዶች ወደአንድ ወገን መሰባሰብና ሀገራችንን ከጥፋት ለማዳን ልንረባረብ በሚገባን በአሁኑ ጊዜ ፤ በመካከላችን መተማመንን የሚያደርቅ ላለፉት 30 ዓመታት ልንተማመንባቸው ያልቻልንባቸውንና የሚያፋጥጡንን ደጋግሞ ማንሳት ሁላችንንም የትም አያደርሰንም። በዚህም ከቀጠልን በጥቂት ጊዜ ውስጥ የምንከራከርበትና የምንኮራረፍብት ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አትኖርም።
ምጀመሪያ የመቀመጪያዬን እንዳለች ሁሉ ዝንጀሮ፤ ሀገራችንን የምንወድ ወገኖች ሁሉ ትላንት ያልተስማማንባቸውን ነገሮች ሁሉ ከጠረጴዛው አንስተን፤ ተከባብረን እየተዳማመጥን የምንከራከርብት ህዝባዊ ሥርዓት እስከምንመሠርት ጌዜ በይደር አቆይተን፤ ሀገር የማዳኑና ፍትኃዊ ሥርዓት መምጣትን የምናምን ፤ ከሁሉም በላይ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የማንደራደር ተሰባስበን ኃይላችንን አፈርጥመን በአንድ አቅጣጫ እንቅስቃሴ መጀመሩን ዋነኛ ተግባራችን እናድርገው።
በዚህ ሀገር አድን እንቅስቃሴ ደፍረን መሳተፍ ስንጀምር ካለጥርጥር ወደድንም ጠላንም መተማመንን በትግሉ ውስጥ ቀስ በቀስ እንገነባለን። ይቅር መባባሉንም እንደገና “ሀ” ብለን እንጀምራለን። ስህቶቻችንም ለመጠፋፊያ ሳይሆን የምንማማርባቸው መሠረቶች አድርገን አባቶቻችን ከሁሉ ጋር ተናጭተው በጥሩ የባህል ምግባር መሠረት አዋቅረው ያስረከቡንን ኢትዮጵያዊነትን መልሰን እናገኛታለን። ህዝባዊ ሥርዓትን ምሥርተን የህግ የበላይነት በሚረጋገጥባት ሀገር ምህረት አድራጊውም ከሳሹም ህዝብ ነው። ለዚህም ነው ዛሬ ያልተስማማንባቸውን ለህዝቡ ፍርዱንም እንተውለት የምንለው። ዛሬ በምንጫወተው ሚና በምናሳየው ምግባር ያለጥርጥር ህዝባችን ለሁላችንም ምስጋናውን እኩል ይሰጠናል። ምህረቱንም እንዲሁ። በህዝባችን እንተማመን። ዛሬ እኮ የሚገፋውን ያክል ኢትዮጵያን ይዞ ካለመሪ ከወያኔ ጋር ተፋጦ ያለ ህዝቡ መሆኑን አንርሳ።
ኢትዮጵያዊነት ያለጥርጥር ያቸንፋል!
ፍትኃዊ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት በጋራ እንነሳ!
የአሲምባ የውውይይት መድረክ

10 thoughts on “Assimba.org responds to Dawey Ibrahim”
Hi EPRPs
I don’t know if you realize you are in the 21st century where every single comment, speech, or article is documented or observed by someone somewhere in this “small” world of ours. I am a living witness of what you did after the “abyot of 1974” in Ethiopia. You confused the youth alienated whoever didn’t follow you and at the end you were instrumental for the death of millions of Ethiopians by the Derg and now still without admitting your guilt and without learning from your past mistakes you are trying to sound like a democratic entity. Please be realistic and if you truely think about the wellness of the Ethiopian poor stop bashing Kinijit and other genuine patriots who are working tirelessly to save Ethiopia. As I said above I was a high school student at that time and I have seen every thing you were doing at that time. May God help you to come to your senses
አሲምባዎች:-
ቆንጆ ጽሁፍ ነው:: መልዕክቱም ግልጽና ቁምነገሮች ያዘለ ነው:: አንዳንድ ሰዎች የቅንጅት ደጋፊነታቸውን የሚያረጋግጡት ኢህአፓን በመሳደብ ይመስላቸዋል መሰለኝ:: በተገላቢጦሽም አንዳንዶች ኢህአፓነታቸውን የሚያረጋግጡት ቅንጅትን በመሳደብ የሚመስላቸው አሉ:: ለእኔ ሁለቱም ስህተት ነው:: ስህተት ብቻ ሳይሆን አላዋቂነት ነው:: በአሁኑ ሰዓት የሚያስፈልገን ልዩነቶቻችንን ማጥበብና ወደ አብሮ መስራት መምጣት ነው:: የጥላቻ ፖለቲካ ማቆም አለበት:: ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ይህንን ሀቅ ነው መገንዘብ ያቃታቸው የሚመስለኝ:: የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈልገው የፓርቲዎችን መናቆር አይደለም:: በ1968 ማን ስህተት ሰራ በ1997ስ ማን አጠፋ አይደለም የኢትዮጵያ ህዝብ አንገብጋቢው ጥያቄ:: ምክንያቱም የኢትዮጵያ ህዝብ በየቀኑ እየተበደለና እየተሰቃየ ስለሆነ 1968ም ሆነ 1997 ከሌላው ቀናት የተለዩ ሆነው የሚታዩት አይመስለኝም:: የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈልገው የፖለቲከኞች መናቆር ቀንሶ “ቅንጅትን ደገፍክ”, “ኦነግን ደግፍክ” ወዘተ ወዘት እየተባለ በየእስር ቤቱ እንዳይታጎር ነው:: ስለዚህ መናቆሩ ይቁም!!!! እያንዳንዱ የፖለቲካ ድርጅት ኃላፊነት ያለው ስራ ይሰራ!!!!
ወይ ጉድ
Dawey: CHOSE TO STEAL A PAGE OUT OF ABRAHAM YAYEHE’S PLAY BOOK
Thank you very much for your input and making things clear. If any questions or doubts remain about this case, it would cast a permanent cloud over truth, diminishing accountbly and transparency. People, like Dawey should be unmasked and brought to justice.
As we are witnessing, Dawey has followed the foot prints of ABRAHAM YAYEH, cheating us, until his mask was removed, preaching empty pile of words which he has never made it practical, crowning only himself like NAPOLEON, by ignoring collective leadership and transparency. His deceitful move is “JIB YEMAYAKUT HAGER HEDO KURBET ANTIFULIGNE YILAL” style.
Dawey, a person currently working with anti-Ethiopian forces for his come back to get a place with the Woyane thugs and criminals is accusing pro-unity forces and individuals unreservedly contributing to our struggle for democracy and peace. For Dawey the number one enemy in the list are EPRP and trade unionist who stood by his side on those difficult days and contributed a lot. What a betrayl!
That is his present to WOYANE on silver plate, but he is making a grave mistake.
It is long ago that he made the trade union a one man show, marginalaizing others to fulfill his hidden agenda, instead of making it to represent thousands and working collectively to promote the cause of workers.
“Ashes fly back into the faces of him who throws them” as Dawey did by stealing a page from the play book of ABRAHAM YAYEHE,and no matter how long the night, the day is sure to come. Eventually he will be exposed for all his crimes ranging from abusing our sisters to pocketing thousands dollars in the name of Ethiopian workers and those who are beating the drum with him will be ashamed to hear his story and what he has been doing in Amsterdam. Just before, FNV kicked him out, Dawey was spending thousands of dollars collected in the name of victim,Ethiopian workers like there was no tomorrow.
Truth will prevail!!!!!!!
Dawit Yohannes
አቶ ዳዊ እንደጻፉት የአሲምባ የውይይት መድረክ የኢሕአፓ ተለጣፊ አይደለም። በጥቂት ሀገር ወዳዶች የሚንቀሳቀስ ከማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ ነጻ የሆነ ፤ ዘለቅ ብሎ የተገለጸውን ዓላማ ይዞ የሚንቀሳቀስ መሆኑን እንዲገነዘቡልን እንወዳለን። ይህንንም ስንል ግን ኢሕአፓ የኢትዮጵያ የቁርጥዬ ቀን ጀግኖች በደም አጥንታቸው የገነቡት ዕውነተኛ ሕዝባዊና ኢትዮጵያዊ ድርጅት መሆኑን ላንዴም አንጠራጠርም።
ተለጣፊም ነጻም አይደላችሁም ኢህአፓ ናችሁ እንጂ
God bless his soul.
EPRP WHY DON’T YOU GIVE UP? yOU HAD A CHANCE, BUT YOU SCREWED UP. ETHIOPIANS RATHER BETTER OFF WITH ANY GROUP OTHER THAN EPRP.
Hi! EPRP(The Ethiopian People Retarded Party)
You just want to be in power to scam the people like Woyanne. Not a chance. So give it up.
Belay
There is a big different between accepting EPRP as a good party and having been a member of EPRP. As I understand from that room, they are former members of EPRP/EPRA trying to contribute and involve in this new movement. I don’t think anything wrong with that. We suppose to give them some encouragement instead of oh ya you are EPRP. I also don’t think there is anything wrong if they are EPRPs.
Is it important to comment on the issue what happened 30 years ago? As far as I am concerned, the comment that Ato Dawi made is very irrelevant. For the simple reason that, time has changed. The condition at that time maybe permits to infiltreat any civic organizations, labor union, student union, women organization etc… So what is the use of the article? Unless we are attacking some group/party in organized manner for some unseen gain. If that is the reason the only thing we have to do is wait and see. I think we will see some thing very soon. Probably a new party a new way of approaching Woyane, time will tell.
Dear EPRPs,
Are you still not changed? Don’t remember what you have done to our people? Are you not the cause of the death of 100,000 people? What have Ato Dawey Ibrahim done to you? Yes, he revealed your underground work. Do you think that what are you doing is not known to the people of Ethiopia? Your history of killling thousands of innocent people will never repeated. One day you will be brought to justice. Don’t think that your file was closed.