Skip to content

Ethiopia

ኢትዮጵያ፤ የመዳኛ ወቅትና፤ የዕረቀሰላምጊዜ

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ

የረፖርተር ድሕረ ገፅ ሲዘግብ:

‹‹በጎሳ ላይ የተመሰረተ ግጭት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሃል በመጸዳጃ ቤቶች፤ በቤተመጻህፍትና በመኝታ ቤት  ግድግዳ ላይ፤የተጻፉ አስፀያፊ ክብረነክ ጸሁፎች ከስድስት በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ለከፍተኛ የመቁሰል አደጋ ተጠቂ ዳርጓቸዋል:: በርካታዎችንም ለእስር አብቅቷል፡፡ ለላለፉት አሰርት ዓመታት፤በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሃል ግጭቶችን ሲያስነሱ ከርመዋል፡፡ ይህም መሰረታዊ ችግሩና መንስኤው አስተዳደራዊ ድክመት ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተመሳሳይ ባለፈው በእለተ ዕረቡ ጃንዋሪ 2 2013 የተቀሰቀሰው ግጭትም በተለይ በሁለት ጎሳዎች በኦሮሞና በትግራይ ተማሪዎች መሃል የተከሰተ ነበር፡፡ ምስክሮች እንደሚሉት፤ግጭቱ የተቀሰቀሰው የትግራይ ተወላጅ የሆነው ተማሪ፤ በመጸዳጃ ቤት፤ በቤተመጻህፍትና በተማሪዎች መኝታ ቤቶች  ግድግዳዎች ላይ የጎሳን ክብር የሚነካ ጽሁፍ በመጻፉ ነበር፡፡››

እንደ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባለስልጣን አባባል ‹‹ግጭቱ የተቀሰቀሰው ያንን የጎሣ ክብር የሚነካ ክብረነክ ጽሁፍ በተመለከቱት ተማሪዎች  መሆኑን ነው::›› በዚህም የተነሳ 20 ተማሪዎች መቁሰላችውንና 3ቱ የጠናባቸው ወደ ሆስፒታ፤ል መወሰዳቸውን በተጨማሪ ሁለቱ የቀዶ ጥገና እንደተደረገላቸው ታውቋል፡፡ ሌሎች 20ዎችም በፖሊስ ባልለየለት ውንጀላ ለእስር ተዳርገዋል፡፡

ስለኢትዮጵያ ‹‹የብልሆች መፍለቂያ ከነበረው ዩኒቨርሲቲ›› ይህን ሁኔታ ሳነበው ያደረብኝ ግብታዊ አስተያየት፤ ማመን እስኪያቅተኝ ነበር፡፡ ሳስበዉም ‹‹ይህ ፈጽሞ ሊታመን የሚችል ጉዳይ አይደልም፡፡ ይህ ከኢትዮጵያ አነሮች ትውልድ (ወጣቱ ትውልድ) በዚህ ፈሪነትና የማያስፈራራ አስከፊ ሁኔታ ውስጥ መግባት ተግባራቸው አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዚህ ቆሻሻ እና እጣቢ አተላ የጎሳ ፖለቲካ ውስጥ ከመንደፋደፍ የተሸለና የበለጠ ተግባር ማከናውን ይችላሉ›› አልኩኝ :: ይህን የመሰለ የረከሰ የጥላቻ ምግባር፤የወዲፊቶቹ ኢትዮጵያዊያን ምሁራን፤የቀጣዩ ትውልድ መምህራን፤ ሳይንቲስቶች፤ እና የፈጠራ ሰዎች ምግባር እንዳልሆነ ነበር እራሴን ማሳመን የሞከርኩት፡፡

ነገሩን የበለጠ ሳጤነው አምአሮ የሚነካና የሚአስቀፍፍ ሆኖ አገኘሁት፡፡ እራሴንም ጠየቅሁ፡፡ ምናልባትስ ይህ የጎሳ ክብር የሚነካ ጽሁፍ በሌሎች የአ አ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች  የተፈጠረ ቢሆንስ? ይህን የመሰለው ዝቃጭ፤ወኔቢስ፤ባለጌ ተግባር ስለነዚህ ተማሪዎች ምን ይላል? ስለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችስ? ስለአጠቃላዮቹ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችስ? ስለ መላው የኢትዮጵያ ወጣቶችስ?

ከዚህ ጥየቄ ጋር በመታገል ላይ እንዳለሁ፤ ሊገታ የማይችል ሃፍረትና ውርደት ሰሜት ወረረኝ፡፡ እራሴን ደጋግሜ መረመርኩት፡፡ ‹‹የኢትዮጵያ ምርጥና ብሩህ አእምሮ ያለቸው ተማሪዎች—- የኢዮጵያ አነሮች —- ይህን በመሰል ኋላ ቀር፤ አረመኔያዊ፤ ጨካኝና አሰቃቂ፤ ተናካሽ፤ ተንኮል የተመላበት፤ተግባር አንዴት ሊሰሩ ይችላሉ?  በምን መንስኤ ነው፤ አንድ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ስብስብ ሌላውን ወገን ስብእና ለመድፈር፤ የጋኔን ተግባር ለመፈጸም፤ ዝቅ አድርጎ ለመመልከት፤ አውሬ በማስመሰል፤ አካሄድና ተግባር የሚሰማሩት? ለምን? እኮ ለምን? ለነዚህ ጥያቄዎች አንዳችም ምክንያታዊ ምላሽ ላገኝ አልቻልኩም፡፡

ይህ የ ጎሳ  ጥላቻ ወንጀል የተፈጸመው ባለፈው ሳምንት ሰለ አትዮጴያ ወጣቶች ክብርና ወደፊት ላገራቸው ሰለምተበቀባቸው ግዴታ በመፅፈበት ወቅት ነበር :: ሆነ በተባለው የጎሳ ጥላቻ ወንጀል የበለጠ ግራ እየተጋባሁ ሄድኩ፡፡ ይህን አስጠያፊና አስፈሪ፤ ቀፋፊ ሁኔታ በምክንያታዊነት በጥልቀት ለመረዳትና በዚህ አስገራሚ ትርኢት ውስጥ አንዳንድ የኢትዮጵያ አነሮች እንደ ጉማሬዎቹ በመንቀሳቀስ እንደጅቦቹ ለመሆን መከጀላቸው አስገረመኝ፡፡ አሳፈረኝ፡፡ አሳዘነኝ፡፡

ያን ግልብ ስሜቴን ወደ ጎን አልኩና ረጋ ብዬ ማሰብ ጀመርኩ:: ከምር ጠንክሬ አሰብኩ፡፡ ይህ በዩኒቨርሲቲው የተከናወነው ‹‹በጎሳ ላይ የተመሰረተውን አልመግባባት›› ድርጊት ከጥሩ እምነት ካላቸው ሁነኛ መደበኛ ተማሪዎች ተጠንስሶ በስራ ላይ የዋለ ነው  ለማለት ምን ማስረጃ ሊቀርብ ይችላል? በእውነትስ  የተባለውና በዚህ በየግድግዳው ላይ የሰፈሩትን ክብረ ነክ ጽሁፎች የጻፈው ‹‹ተማሪ›› ማነው?  በዚህ ዩኒቨርሲቲ የሙዚቃ ሸክላ አጫዋች መሰል የህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ተቀምሞ የተበተነውን መሸንገያ አባባል ማመን አለብን? እንዴት ነው የዩኒቨርሲቲ አስተዳዳሪዎች  ‹‹ለአሰርት ዓመታት በዩኒቨርሲቲዎች ሲከናወኑ የነበሩትን የጎሳ ግጭቶች” ያሳለፏቸውና አሁንም ሲቀጥሉ  አጃቸዉን አጣጥፈው  መመልከት የቻሉት? በዩኒቨርሲቲውስ ውስጥ ምራቃቸውን የዋጡና የበሰሉ፤ችግሮችን ለማክሸፍና ለማግባባት ፈቃደኛ የሆኑ አመራሮች የሉም?

ጥርጣሬ ቀስ እያለ፤ድንጋጤዬንና ሃፍረቴ  መተካት ስለጀመረ፤ የዚህ ‹‹በጎሳ ላይ የተመሰረተ ብጥብጥ›› በገዢው መንግስት ጀብደኛ ባለማዕረግ የተዋቀረና፤ የተተለመ እንደሆነስ የሚለው ጥያቄ አያፈጠጠ ያየኝ ጀመር፡፡ በኋላም የወንጀል መመርመርያ ማስረጃ ማፈላለጊያ “መነጽሬን” ሳደርገው፤ እንደገና በመሹለክለክ ድምጽዋን አጥፍታ ጨለማና ወቅትን መከለያ በማድረግ አንዲት መናጢና ቆሻሻ አይጥ ተንኮሏን ከፈጸመችና ተልእኮዋን ከፈጸመች በኋላ ሳትታይ ጥላው  የሄደችውን የእጇንና የእግሯን አሸራ በግድገዳ ላይ ከተጻፈው አስጠያፊ ጥሁፍ አግርጌ ታትሞ አየሁት፡፡

በሜይ 2010 ጃዋር ሲራጅ ሞሃመድ ወጣቱ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ሐተታ ሰጪ እንዲሁም የኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪ እንደዘገበው  በዩኒ ቨርሲቲው ግቢ ውስጥ ከተማሪዎች ጋር በርካታ ውይይት ካካሄደ በኋላ እንዲሁም በሁለት ክፍል በሃራማያና፤በአዳማ  ዩኒ ቨርሲቲ በ2006 የተከናወነውን ድርጊት  ሰበቡን የአካዳሚክ ነጻነት ማጣትና በኢትዮጵያ የደህንነት ሚስጥራዊ ተቀጣሪዎች ተማሪ በመምሰል ሰርገው በመግባት የግጭቱ መሰሪ ጠንሳሾች መሆናቸውን ለማመን በቅቷል፡፡

ደግሞም በሴፕቴምበር 2011 ላይ በይፋ የዎጣው ማስረጃ አንዳሳየው በሴፕቴምበር 16 2006 “ የኢትዮጵያ የደህንነት ሃይሎች በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ 3 ፈንጂዎች መቅበራቸውንና በመፈንዳቱና፤ በወቅቱም የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ የሚካሄድበት ስለነበረ ከረር ያለ ጥያቄ ያስነሳውን  ፍንዳታም ኤርትራንና የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባርን ተጠያቂ እንዳደረጉ ነበር::” በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካን መንግስት ኤምባሲ ባካሄደው ‹‹የሚስጢር ዘገባ›› በጉዳዩ ላይ የመርማሪዎቹ ጣት  ወደ ኢትዮጵያ ገዢ መንግስት የደህንነት አባላትን በመጠቆም ለዚህ የወንጀል ድርጊት ተጠያቂ አድርጓቸዋል፡፡

በሌላም በኩል በ2006 የተገኘው ሚስጥራዊው ባለ 52 ገጽ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተዘጋጀው ሰነድ፤ የዲያስፖራው ዳይሬክቶሬት በዲያስፖራው ያሉትን የተቃዋሚ ሃይላትና አባሎቻቸውን የሚነዘንዝ፤ በሃይማኖት፤ በዘር፤ በፖለቲካ ጥላቻ የሚከፋፍልና ማንኛቸውንም ገዢውን ፓርቲ የሚቃወሙትን ለመከፋፈልና በመሃላቸው መግባባት እንዲጠፋ ያደረገው ጥረትና ዝግጅት ተጋልጦ ነበር ፡፡ ስለ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አጋጣሚ በይበልጥ ባሰብኩ ቁጥር፤የገዢው መንግስት ተቃዋሚዎችን ለማስጠላት ለመከፋፈል ለመበታተን ለማክሸፍ ብሎ የሚዘራውን ቆሻሻና የብልግና ባህሪ ያጋልጡት ጀምረዋል፡፡

በተጨባጭ ምርምሬ አንደተርዳሁት ‹‹በጎሳ ላይ ለተመሰረተው ግጭት›› ወንጀል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ተጠያቂው ማን እንደሆነ ግልጽ የሆነው ማስረጃ  የሚጠቆመው ወደ ተለመዱት ወንጀል ፈጻሚ የገዢው መንገስት ወንጀለኞች ነው፡፡

ሊታለፍ የማይችለው መደምደሚያም፤ (ሌላ ተቃራኒ  ማስረጃ  እስካልቀረበ ድረስ) በጃንዋሪ 2 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለተፈጸመው ወንጀላዊ  ተግባር ተጠያቂዎቹ፤ በግቢው ውስጥ በድብቅ የተቀመጡት መዘዝ ፈጣሪዎችና ምግባረ ብልሹ ሕሊና ቢስ  ወኪል ተንኳሾችና ደባ ፈጻሚዎች እንጂ ጨርሶ ለጥሩ ዕምነት የተፈጠሩት ወጣት አቦሸማኔዎቹ የነገ የሃገር አለኝተ ዎች ሊሆኑ አይችሉም፡፡

የማጠቃለያው ግምገማም ይህንን መደምደሚያ የማያጠያይቅ ማስረጃ በመሆን ያረጋግጠዋል፡፡ ያለዉን ማስረጃ በጥቂቱ ብንመለከተው: በመጀመርያ እንድ ብቸኛ “ተማሪ”ብቻ ነው ድርጊቱን በመተንኮሱ  የተወነጀለው፡፡ ይህ ደግሞ ተማሪዎች በአንድ ጎሳ ስር ተቧድነው ለዚህ ድርጊት መንቀሳቀሳቸውንና በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ሰላም ለማጥፋት ወንጀል ለመፈጸም፤ መደራጀታቸውን ተአማኒነት ያሳጣዋል፡፡  ይህን እንቅሳቃሴ ለመጀመርና መነሻ ሆነ የተባለውም ብቸኛ “ተማሪ” የየት ጎሳ አባል እንደሆነ በግልጽ አልተረጋገጠም፡፡ የዩኒቨርሲቲው ባለስልጣናት: ስምና መለያው ያልታወቀ፤ አንድ ተማሪ በማለት ወንጀለኛ ብለውታል፡፡ ይሁንና ይህ ‹‹ተማሪ›› ዓላማ ያለው እርገግጠኛ  መደበኛ “ተማሪስ” ነው? ወይስ ተቀጣሪ ነገር ቆስቋሽ የስለላ ድርጅት ወኪል ግን እንደተማሪ ተመሳስሎ ተወሻቂ አባል (የቀበሮ መንኩሴ በግ መሃል ይጸለያል አንደሚባለው ሁሉ ) ነው? ይህስ ተማሪ በዘር ላይ የተመሰረተ የጥላቻ ባሕሪ ግለ ታሪክስ ያለው ነው?

ሶስተኛ፤ በሶስት ቦታዎች ማለትም በላይብረሪ፤ በመጻሕፍት ቤትና በተማሪ  መኝታ ቤት ይህን መሰሉን የጎሳን ክብር የሚያዋርድና የሚያንቋሽሽ ጽሁፍ ለመጻፉ ምንም የተጠቀሰ ማስረጃ የለም፡፡ በጥላቻ ወንጀል ድርጊት፤ እንዲህ መሰሎች የጥላቻና የማዋረድ ተግባር ያለባቸው ጽሁፎች ሲጻፉ ዓላማቸው አንድን የጎሳ አባል የሚመለከቱ ሲሆኑ፤ ኢላማ የተደረጉት ግለሰብም ይሁን ቡድኖች ሊደርሱበትና ሊያዩት በሚችሉት ስፍራ ይሆናል እንጂ የግል ጥላቻውንና ብሶት ጣውን  ከተለያዩ ብዙ ጎሳዎች የመጡ በሚገኙበት ግቢ ውስጥ የማይመለከታቸውም እንዲመለከቱት ለምን ይደረጋል?

አራተኛ፤ ከዚህ አስቀያሚ  የግድግዳ ጽሁፍ ሌላ ማስረጃ ሊሆን የሚችል አንዳችም ነገር ከዚህ የችግሩ ጠንሳሽ በተባለው ‹‹ተማሪ›› ላይ አልተገኘም፡፡

አምስተኛ፤ በጃንዋሪ 2 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተፈጸመው ደባ የተለየ ሁኔታ ሆኖ ሊታይ አይችልም፡፡ ላለፉት በርካታ አሰርት ዓመታት ይህን መሰል በጎሳ ላይ ተመሰረተ አምባጓሮ ይነሳ እንደነበር የማያጠያይቅ ነው፡፡ ለምንስ የዩኒቨርሲቲው ባለስልጣናት ጉዳዩ ሲያቆጠቁጥ አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ ለዚህ ከመብቃቱ ቀደም ብለው አላከሸፉትም፡፡ ድርጊቱ በአስከፊና ሊቀለበስ ወደማይችልበት ሁኔታ ከደረሰና አዳገው ሁሉ ከተከናወነም በኋላ በሌሎች ተማሪዎች ላይ አመጹ ተስፋፍቶ እንዳይቀጥልም ባለስላጣናቱ የወሰዱት እርምጃ የለም፡፡

ስድስተኛ፤ በነጻ አካላት ጉዳዩ ሙሉ በሙሉ ከመጣራቱስ አስቀድመው የዩኒቨርሲቲው ባለስልጣናት “አመጹ የተጀመረው በግድግዳዎች ላይ የተጻፈውን ምግባረ ብልሹና ጎሳን የሚያንኳስስ ጥሁፍ ያዩት ተማሪዎች ነው በማለት ለምነስ መግለጫ አወጡ? ጉዳዩን ከመሰረቱ አንስተው የሚያጣሩ ገለልተኛ ወገኖች በማዋቀርና በመመርመር ለወዲቱ ይህን መሰል ድርጊት በድጋሚ እንዳይከሰት ማድረግ የሚቻልበትን ዘዴ ለምን አልቀያሱም? የዩኒቬርሲቲው ባለስልጣናት ጉዳዩን እራሳቸውን ከተጠያቂነትና ከሃላፊነት በማግለል ለፖሊስ ሙሉ በሙሉ ለምን አስረከቡት? ምናልባት በዩኒቨርሲቲው የሚከሰተውን የጎሳ ጥላቻ ወንጀል ቸል ያሉት አይታችሁ እንዳላየ ሁኑ የሚል መመርያ ስለተሰጣቸው ይሆን?

ሰባተኛ፤ የዚህ የጥላቻ ብጥብጥ ወንጀል ተጠቂ የሆኑትስ በፖሊስ ለመደብደብ ለመያዝና ለመታሰር ለጉዳት ለምን ተዳረጉ?

በአጭሩ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተፈጸመው የጥላቻ ወንጀል የቀረበው ሁኔታና ማስረጃ ጨርሶ ወደ ተከሳሾቹ ተማሪዎች ጣት አያመላክትም፡፡ ይልቁንስ ያአመልካች ጣት በወንጀለከኝነት የሚጠቁመው ወደ ከሳሾቹ ነው፡፡ የዚህን የጥላቻ ወንጀል ፈጻሚዎች ለማጣራትና ለመያዝ የሚያስፈልገው፤ ያንን የግድግዳ ላይ ጽሁፍ የከተቡትን የማይታዩ ጣቶች ብቻ ሳይሆን  እነዚያን ተማሪዎቹን እስኪጠወልጉ ድረስ የቀጠቀጡና ያሰቃዩ፤ ከዚያም በረጩት የአመጽ ነዳጅ ላይ እንዳይጠፋና የበለጥ እንዲቀጣጠል ንዳድ የረጩበትንና የጎሳ ግጭቱን ያቀጣጠሉትን፤በተማሪዎች መሃል ጥላቻ  ንትረክና ዉዝግብ አንድፈጠር የሚዶልቱ ወንጀል ጠንሳሶች ነው፡፡

ያም እንዳለ ሆኖ፤አሁን ወቅቱ ነው፤ አስፈላጊው ወቅት ነው፤ትክክለኛው ጊዜ ……..

የማገገሚያጊዜ፤የመቀበያውየመተቃቀፊያ  የእርቀሠላምጊዜ አሁን ነው

በክዱስ ጽሁፍ እንደሰፈረው፤ ‹‹ለማንኛውም ሁኔታ ወቅት አለው፤ከሰማይ በታች ላሉት ነገሮች ሁሉ  ለየምክንያቱ ጊዜ አለው::›› ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለሃዘንም ወቅት አለው፤ ድንጋይ ለመወርወርም ጊዜ አለው፡፡ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፡፡ እንዲሁም ለመተቃቀፍም ጊዜ አለው ለሠላምና ለማገገምም ጊዜ አለው፡፡ ለእርቀሰላምም  የራሱ ጊዜ አለው፡፡

አሁን ነው ጊዜው፤ — ትክለኛው ጊዜ– ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች በትምህርት ቤቶች፤ በዩኒቬርስቲዎች፤ በስራ ቦታዎች፤ በአጎራባች መንደሮችና በመንገድም ላይ  የማገገሚያው ወቅት፡፡ ጊዜው—– ትክክለኛው ጊዜ—- የኢትዮጵያ ወጣቶች በወንድማማችነት በአህትማማችነት ስሜት መተቃቀፍ  መተሳሰብ እጅ ለእጅ በመያያዝና አንድ በመሆን ብዛታቸውን  ለቅድመአያቶቻቸው ክብርና ለታሪካቸው መከበርያ ማድረግ የሚገባቸው፡፡

ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች የጎሳ ጥላቻን  የብጥብጥን አዙሪት የመበጠሻ ጊዜው አሁንነው:: አላስፈላጊውን የቅሬታ ልምድ የማክተሚያ፤ የፍርሃትን ባህል፤ ጥላቻን፤ አውልቆ የመጣያው ትክክለኛው ጊዜው አሁን ነው፡፡

ለኢትዮጵያውያን ወጣቶች ጣቶቻቸውን በማቆላለፍ እጅ ለእጅ በመያያዝ የፍርሃትን እከክ ማራገፊያቸው፤ ጥላቻን፤ግጭትን፤ከልባቸው ፤ ከሕሊናቸው፤ ከመንፈሳቸው አውጥተው መጣያ ጊዜያቸው አሁን ነው፡፡ ጓደኞቻቸውንና የትምህርት ባልደረቦቻቸውን እንደጠላትና  ባላጋራ መመልከትን ማቆሚያቸው ጊዜ አሁን ነው፡፡

ሰላም ፈጥረው እርስ በርሳቸው እንደወንድምና እህት የሚተቃቀፉበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብልህና ምርጦች አንድ ላይ በመስራትና በመተጋገዝ የተሸለን ነገ ለመፍጠር የሚችሉበት፤በረጋና ጠንካራ በሆነ የሕግ የበላይነት ላይ፤ ሰብአዊ መብትና ዴሞክራሲ የተከበሩበት አማራጭ ሂደቶች ያሉበት መትለሚያው ጊዜ አሁን ነው፡፡ ኔልሰን ማንዴላ እንዳስተማሩት ‹‹ከጠላት ጋር ሠላምን መፍጠር ካስፈለገህ፤ከጠላትህ ጋር ተጓድነህ መስራት አለብህ፤ ያን ጊዜ ጠላትህ ወዳጅህ ይሆናል::›› እነዚያን ጠላት የምንላቸውን ወንድምና አህት አብሮ ተማሪዎች  ና ወዳጅ ማድረጊያ ጊዜው አሁን ነው፡፡

በዩኒቨርሲቲ ግቢያችን ውስጥና ከግቢያችንም ውጪ ጥላቻንና የጥላቻ ወንጀልን ለማጥፋት መተባበርያው ጊዜ አሁን ነው፡፡

ከሕሊናችንና ከመንፈሳችን ውስጥ የጥላቻ ቋጠሯችንን ማጥፊያው፤ የፍርሃትን ሰንሰለትና ካቴና መበጠሸውጊዜ አሁን ነው፡፡ የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች ካለፈው ጫና እራሳቸውን ለማላቀቅና ነጻ ለማድረግ ጊዜው አሁን ነው፡፡

ለሁሉም ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ቆንጨራውን በመቅበር ለአንድዬና ለመጨረሻው ጊዜ ‹‹አሻፈረን! አንዳችን ሌላውን የዚህ ወይም የዚያ ጎሳ ስለሆንን ለመጠላላት አሻፈረን፤ እምቢ! መባያችን ጊዜው አሁን ነው፡፡ አሻፈረን! ምክንያቱም ሁላችንም በተለያየ ስም በምንጠራው የጋራችን በሆነው አምላክ ስር አለያም የሁላችን በሆነችው ሀጋራችን የተለያየ ማእዘን ነዋሪዎች ነንና፡፡ እምቢ! በምንም መልኩ ለመጠቀሚያነትና እንደ አሻንጉሊትነት ሆነን በሚጠቀሙብን ለጥላቻ ለእርስ በርስ መቆራቆስ መጠቀሚያ አንሆንም፤ እምቢኝ! የሠለጠንን ነንና ለጥላቻ አንሰለፍም፡፡ አዳኝ እንደሚያሳድደው የሚታደን አውሬ ለመሆን እምቢኝ!

ከአንድጉማሬጥቂትቃላትለበርካታዎቹአቦሸማኔዎች

በርካታ አቦሸማኔዎች ምናልባትም ጉማሬውን ትውልድ ማዳመጡ ያስገርማቸው ይሆናል፡፡

እኛ ጉማሬዎች ‹‹በዕውቀት የተጋረድን›› ‹‹ራዕይ የጎደለን››  ‹‹የራሳችን ምንጭ እስካልደረቀብን ድረስ ጠቅላላው ሃገር ቢደረማመስ ደንታ የሌለን ›› ነን ተበለን አነታወቃለን:: ያም ሆኖ ወጣቱን ትውልድ  በአክብሮት እባካችሁ ጆሯችሁን አውሱኝና ለመደመጥ እድል ስጡኝ እላለሁ፡፡

ጀግኑ!

የመጀመርያው የኢትዮጵያ ትውልድ በመሆን፤ እራሳችሁን ከሰንሰለቱ ነጻ በማድረግ ካለፈው የጫና ሰቆቃ እኛንም አራሳችህሁንም ለማላቀቅ ብቁ፡፡

የመጀመርያው የኢትዮጵያ ትውልድ በመሆን፤ ታሪካዊ ጥላቻን፤ ቅሬታን በማጥፋት፤ መግባባትንና መቻቻልን በማምጣት አዲስ እርቀሰላም በኢትዮጵያ ታሪክ ጀምሩ፡፡

የጥላቻን ቁስል ለማዳን የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን ለዘመናት ያመረቀዘውን በማጥፋት ለመጪው ትውልድ ያለፈው ትውልድ ስህተትና ጥፋት እስረኞች እንደማይሆኑ አረጋግጡላቸው፡፡

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን ሁላችንም በእኩልነት የሰው ዘር አባላት በመሆናችን ይህንንም በጎሰኝነት ለማቀደም ብለን አዘቅት አንውረድ ::

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን አንደኛችን ለሌላው ይቅርታን በመቸር ለአንድዬና ለመጨረሻ ጊዜ ቆንጨራውን በመቅበር፤ ጣቶቻችንም የጠመንጃ  ቃታና ምላጭ ለመሳብ፤ጣቶቻችን የጥላቻ መነሾ የሆኑ ቃላትን በየግድግዳው ላይ ለመለቅለቅ ሳይሆን እጆቻችን የሚዘረጉት የመግባባት የመተሳሰብ ሰላምታ ለመለዋወጥና ለችግርም ይሁን ለደስታ እጅ ለመዋዋስ ብቻ አንድሆን ማረግ ያሻል፡፡

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን የተለያዩት እምነቶቻችን መለኮታዊነታቸውን ማረጋገጥ እንቻል::

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን አሻፈረኝ! አምቢ! በማለት ውስጥ ውስጡን ከሚበላን የጎሳ የሃይሞነት የጻታ ልዩነት በተቃርኖ እንቁም::

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን በመኝታ ቤቶች፤ በቤተመጻህፍት፤በመጸዳጃ ቤቶችም ያሉትን አስነዋሪና በታታኝ፤ ጎሰኝነትን የሚያቅራሩ ቃላታን በእርቀሰላም፤ በመግባባት፤ በውህደት፤ በፍቅር አሰባሳቢ ቃላቶች እንሸፍናቸው፡፡

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን የወደፊቷ ሃገራችን መሪ ሻምበሎች እናንት ኩሩ አቦሸማኔዎችእንጂ፤ የደከሙት፤ሙሰኞቹ፤ ምግባረብልሹዎቹ፤ እራሳቸውን የሚያስተናግዱ ጉማሬዎች ሊሆኑ አይችሉም፡፡

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን  ለመሆን የምትመኘውን ሁሉ በመሆን፤ለመሆንም ለማሰብ ቀደምት አንሁን፡፡

የመጀመርያዎቹ ትውልዶች በመሆን  የትላንቱን የመረረ ስሜት በዛሬውና በነገው ጣፋጭ እርቀሰላም፤ መግባባት፤ አንድነት፤ መሰረት ላይ መልሳችሁ አዋቅሩት፡፡

የሃቅ ወቅቱ ደርሷል፡ አቦሸማኔዎቹ እራሳቸውን በማዳን ለእኛም መድህን ይሆኑን ይሆን ?

ለኢትዮጵያ ምርጡና ብሩሁ የሃቅ ወቅት ደርሷል!

የኢትዮጵያ ምርጥና ብሩህ አቦሸማኔዎች ካለፈው ጫናና መከራ እራሳቸውን በማዳንና የጎሳ መጎጃጃ፤ የሃይሞነት አክራሪነትን  የጨቋኝ ስጦታ በመጣል እራሳቸውን ማዳን ይችሉ ይሆን?

እነዚህ አቦሸማኔዎች ተጠራጣሪዎቹን፤ የመሸጉትን ምስኪን ጉማሬዎች ከራሳቸው ነጻ ያወጧቸው ይሆን?

ከጎሳ መቆራቆስ ወደ ጎሳ ፍቅር፤መቻቻል አንድነት፤ መግባባትን ያበቁን ይሆን?

አቦሸማኔዎቹ ስብእናችንን ከጎግፍ ማነቆና ከአውሬ አስተሳሰብ ያላቅቁን ይሆን?

አቦሸማኔዎች የእርቀ ሰላምን ጥበብ ያስተምሩን ይሆን? በእርቀሰላም ቋንቋ ያናግሩን ይሆን?

የኢትዮጵያ ብልህና ብሩሆች አንድ የወጣት ግብረሃይል በመሆን 2013ን የአቦሸማኔዎች ዓመት ያደርጉት ይሆን? አንድ ላይ በመቆም የጎሳ ጥላቻን ቆንጨራ በመስበር የወገንተኛነትን ጎራዴ በማቅለጥ የእርቀሰላምን ሙሉነት ያስመርቱን ይሆን?

የአላንዳች ጥርጥር አዎን ይቻላቸዋል!

ባለፈው ሳምንት 2013 የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች ዓመት ብዬ ስተነብይ፤  የኢትዮጵያን ወጣቶች ለማስተማር፤ ለማዳረስ፤ለማሳመን ቃል ገብቼ ነበር፡፡ አኛ ጉማሬዎች አቦሸማነዎችን አናስተመራለን የሚል አምነትም ነበረኝ:: ጉማሬዎችን አቦሸማኔዎችን ያስተምራሉ ብዬ አልገመትኩም ነበር::  ለዚህ ነው እኛ ጉማሬዎች ግራ የተጋባ ሸውራራ (የተዛባ አመለካከት) ቅርብ አዳሪነት፤ጠባብ አስተሳሰብ፤ የምያጠቃን::  ለአቦሸማኔዎች የማስተማርያ ወቅት ሊኖር ስለመቻሉ ጥርጣሬዬ የመጣው::

ስለዚህም የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎችና ጉማሬዎች በርካታ ግብግቦች የሚገጥሟቸው፡፡ የአቦሸማኔዎቹ ፈታና ጉማሬዎቹን የእርቀሰላምን ጥበብ ማስተማሩ ላይ ነው፡፡ የጉማሬዎቹ ፈተና ደግሞ ከአቦሸማኔዎች የእርቀሰላምን ጥበብ መማሩ ላይ ነው፡፡

አቦሸማኔዎች ታሪካዊ ገድል የመፈጸም እድል ቀርቦላቸዋል፡- ይሄዉም በምሳሌነት ማስተማር፡፡

በአዲስ አበባው ዩኒቨርሲቲ አጋጣሚ የተሳተፉትን፤ ወዳዳጆቻቸውንና ሌሎቹም ጭምር በግቢያቸው የተፈጸመውን አስጸያፊ የግጭት ሁኔታና ሁከት አስመልክቼ የማቀርበው ጥሪ ሁኔታውን ወደ ውብና ያማረ ፍቅርና ሰላም የሞላበት ፍሬያማ ውጤት ለማምጣት የአንድነት አውድማ ላይ እንዲሰባሰቡ ነው፡፡ እያንዳንዳቸው ወደ ሌላው በመቅረብ ይቅርታን እንዲጠይቁና እንዲቀባበሉ እጠይቃለሁ፡፡ አንዲት በጣም ትንሽ የሆነችውን ‹‹ይቅርታ›› የምትለውን ቃል ለመተንፈስ ወኔ ይጠይቃል፡፡

በራሳቸው ውህደት እንዲፈጥሩ እጠይቃለሁ—-አንድ ለአንድ፤ በትንሹና በበርካታው ስብስብ—–ልዩነታቸውን ይወያዩበት ይነጋገሩበት ይምከሩበት፡፡ አንደኛቸው የሌላው ጉዳትና ግፍ ይሰማው፡፡ አንዱ የሌላው ፍርሃትና ጥርጣሬ ይሰማው:: አንዱ ለሌላው እንባ ንቀት አይኑረው፡፡

 

በብሩህ ህሊና፤ በንጹህ ልቦና፤ አእምሮና መንፈስ ሊነጋገሩ ግድ ነውና ይህንንም እጠይቃለሁ፡፡

እያንዳንዳቸው የሌላውን ስሜትና ጥርጣሬ እንዲረዱ እጠይቃለሁ፡፡ በጓደኞቻቸው ጫማ ውስጥ ሆነው ለኪሎሜትር  እንዲራመዱ እጠይቃለሁ:: በመጫሚያም ይሁን በባዶ እግራቸው ፈገግ ሊያሰኛቸው የሚችል ሁኔታ ያጋጥማቸዋል፡፡

የኢትጵያ አቦሸማኔዎችን 2013ን የእርቀሰላምና የሰላም ዓመት እንዲያደርጉት እጠይቃለሁ፡፡

ጃንዋሪ 2 1013 በታሪክ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች  የጎሳ ጥላቻን ቆንጨራ፤የሃይሞነት ወገንተኝነት፤ የጾታ ልዩነት የተቀበሩበት ዕለት ሆኖ ዘወትር አንድታሰብ ይሁን፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተከሰተው አስጸያፊ ሁኔታ ለሕዝብ ማስተማሪያነት ያገልግል፡፡

ጥንካሬን ከችግር ወልዳችሁ፤ አንድነትን ከከፋፋይ ተምራችሁ፤ ከጓደኞቻችሁ ተማሪዎች ጋር ለመደማመጥና የመግባባትን፤ የመቻቻልን፤ የውህደትን ዘር ለማፈስ እንድትበቁ እማጸናችኋለሁ፡፡

የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች ጉማሬዎችን እንደመሩ እጠይቃለሁ፡፡ እኛን አትከተሉን፤መሄጃችንን አናውቀውምና፡፡እኛ የጠፋው የጉማሬ ትውልዶች ነን፡፡

ይህን ግብግብ በመቀበል፤ትክክለኛውን እንደትክክል፤ስህተቱንም ወደ ትክክለኛነት ካልለወጣችሁት፤ አቦሸማኔዎች በስልጠና ላይ ያሉ ደካማ ጉማሬዎች ናቸው የሚል ትችት ላይ መውደቅ ይመጣል::

ለሁሉም ጊዜ አለው::   ለኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች፤ ለማገገምና ለእርቀሰላም ሰዓቱ አሁን ነው፡፡

የኔ ጥያቄ ለእዮጵያ ወጣቶች  ይህ ነው:-  አሁን ስንት ሰአት ነው!?!

የተባበሩት የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች ፈጽሞ ለውድቀትና ለሽንፈት አይዳረጉም!

*የተቶረገመው ጽሁፍ (translated from):

http://open.salon.com/blog/almariam/2013/01/13/ethiopia_a_time_to_heal_a_time_to_reconcile

(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::) ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን  ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24

 

 

 

ENTC denounces assassination attempt on Abebe Gelaw

Posted on

It has been reported in the news that TPLF/EPRDF hatched plot had been foiled by the US FBI office and the suspects are under investigation. ENTC strongly denounces this shameful act. It is a recent memory that following the 2005 election, the fascist TPLF foreign ministry drafted and disseminated a 52 page document to all its embassies around the world. This document, aimed in targeting and weakening the opposition forces has been leaked to the public.

The regime has continued its terrorist acts of killing and kidnapping individuals from neighboring Sudan, Kenya, Djibouti, Uganda and other refugee camps and submit them to the inhumane tortures in the Ethiopian prisons. Now it has expanded its terrorist operations to the United States unashamed.

Not only this shows the true nature of this regime, but also the disregard and total disrespect for the laws of the United States, whose government is shedding billions of US tax payer’s dollars with the disguise of ‘fighting terrorism’. Nothing different is expected from a mafia group that has been recorded as terrorist in the US state department books for multiple killings and genocides from 1975 to 1991. Not much is expected from a regime that jails journalists, vilifies millions of Muslims fighting for their freedom as terrorists, commits genocides on its own people (Angwak, Oromo, Amhara), kills innocent civilians and children. We believe this blatant action of the TPLF/EPRDF should prompt the United States government to re-assess its relationships with the regime.

ENTC urges all opposition groups and country loving Ethiopians in the diaspora to exert continuous pressure in making sure that he United States government investigates and takes swift actions. We need to expose the TPLF agents and spies that are serving as the instruments of the terrorist regime to the proper authorities around the world.

We would like to express our respect and admiration to our hero Abebe Gelaw and clearly say to the junta government that we will be committed to create thousands of Abebes and eradicate this mercilessly brutal rule.

ENTC leadership

Read the Amharic Version

 

Ethiopia: A Time to Heal, A Time to Reconcile

aauLast week, The Reporter reported:

An ethnic-based conflict between Addis Ababa University (AAU) students following derogatory graffiti posted on toilet-walls and library walls has left half a dozen students with severe injuries while others had faced arrest. For decades, the clash between students at universities has witnessed many ethnic-based conflicts which many observers claim it to be the weakness of the administering body. Likewise, the Wednesday [January 2] conflict was particularly between those from the ethnic lines of Oromo and Tigre. Reports indicate that the conflict was instigated when member (sic) of the latter ethnic group scrawled derogatory remarks on the walls of toilets and the library and in his own dormitory as well.

An official of Addis Ababa University alleged the “conflict was instigated by students who found derogatory statements posted on the wall”. Some 20 students were reportedly injured in the incident and three hospitalized including two who underwent surgery. Police reportedly arrested 20 students on unspecified charges.

My initial reaction reading this report about Ethiopia’s “best and brightest” was sheer disbelief.  “This just can’t be true. It is beneath the dignity of Ethiopia’s Cheetah Generation (young people) to engage in such a cowardly and dastardly act. Ethiopia’s university students know better than to wrestle in the filth and sewage of ethnic politics.” I kept on reassuring myself that such wicked hatemongering could not possibly  be the work of Ethiopia’s budding intellectuals, future scholars, scientists and literary men and women.

My certitude slowly gave way to gnawing disquietude. I asked myself, “Supposing the inflammatory graffiti and “derogatory statements” were written by bona fide AAU students? What would such a vile, gutless and vulgar act say about these students? About the injured students who reacted with righteous indignation? About the AAU student body? About all Ethiopian university students? About all of Ethiopia’s young people?”

As I wrestled with these questions, I was overcome by an irrepressible feeling of shame and ignominy.  I kept interrogating myself, “How is it even possible for Ethiopia’s best and brightest — Ethiopia’s Cheetahs — to engage in such backward, barbaric, cruel, vicious and villainous act? Why would one group of young Ethiopian university students deliberately plan and scheme to dehumanize, demoralize, demonize, degrade and brutalize  another? Why? Why? I could not come up with a rational answer.

I became even more bewildered trying to answer these questions as I was drafting my “proclamation” to make  2013 the Year of the Ethiopian Cheetahs.  I could not logically fathom the occurrence of this disgusting and horrifying  drama in which some Ethiopian Cheetahs were acting like Hippos and behaving like hyenas.

I put aside my roiled emotions and paused to think, and think really hard. What evidence is there to factually establish the “ethnic-based conflict” was the work of a bona fide AAU “student”? Who really is the alleged “student” who put up the offensive “graffiti and derogatory statements”? Must we believe the story line about the incident concocted by a wily university public relations desk jokey?  How is it that Ethiopian “universities have witnessed many ethnic-based conflicts for decades” and continue to witness them with predictable regularity?  Are there no adults in charge at the universities ready, able and willing to take preemptive and preventive action?

Doubt slowly began to displace my disappointment, shock and shame as I pondered the real possibility of this so-called “ethnic-based conflict” being stage-managed by the invisible knights of the empire.

When I finally put on my forensic lenses, I could clearly see the fingerprints and footprints of a dirty rat lurking on campus once again undetected.

In May 2010, Jawar Siraj Mohammed, a young Ethiopian political commentator and graduate student at Columbia University reported, “After interviewing several students involved in these [campus] conflicts and witnessing two violent episodes in Haramaya and Adama universities in 2006, I have come to the conclusion that lack of academic freedom at the universities and infiltration by agents of Ethiopia’s secret police and security services are the major sources of conflict.”

It also dawned on me that in September 2011 we learned  “Ethiopian security forces (had) planted 3 bombs that went off in the Ethiopian capital Addis Ababa on September 16, 2006  and then blamed Eritrea and the Oromo resistance for the blasts in a case that raised serious questions about the claims made about the bombing attempt against the African Union summit earlier this year in Addis Ababa, Ethiopia.” It was the U.S. Embassy in Addis Ababa which conducted its own “clandestine reporting” and fingered “GoE (Government of Ethiopia) security forces” for this criminal act.

I also recalled a 2006 secret 52-page document written in Amharic and prepared by the so-called Directorate of the Diaspora of the Foreign Ministry in Addis Ababa detailing strategy and tactics to harass, persecute and smear critics and opponents of the ruling regime and spread ethnic strife in the Ethiopian Diaspora.  As I thought more about the AAU incident, the anecdotal evidence of regime dirty tricks used to undermine, neutralize and destroy opposition parties, harass and persecute dissidents and others kept popping out.

My preliminary analysis of the circumstantial evidence on who is responsible for the “ethnic-based conflict” at the AAU campus points exclusively at the usual suspects. The inescapable conclusion (until substantial counterfactual evidence is presented) is that the hate crime that took place on the AAU campus on January 2 is likely the work of anagent provocateur (s) (one or few individuals placed on campus to act as agitators and instigators) and not a bona fide student(s).

A summary review of the uncontroverted evidence supports this conclusion. First, a single “student” is officially blamed for causing the incident. This factually negates the existence of an organized hate group of students of one ethnic group engaged in the persecution of another and intent on causing ethnic strife, dissension and discord on campus.  Second, the identity, background and affiliation (ethnic and otherwise) of the “student” who is said to be responsible for the criminal act has not been factually established. University officials fingered an unidentified student as being responsible. But is this “student”  a bona fide student or a regime undercoveragent provocateur masquerading as a student? Does this “student” have a history of ethnic animus against students of other ethnic groups?

Third, no motive has been established for the “student” who put up the graffiti and derogatory statements in multiple locations including the “walls of toilets, the library and in his own dormitory as well.”  In hate crime situations, when derogatory graffiti are directed toward a group, they are usually displayed in locations likely to be seen by the target group and intended to spark random expressions of outrage. Why would the “student” fingered for this crime target all students of an entire ethnic group as the object of his personal fury?

Fourth, other than the graffiti depicting the offensive statements, no additional evidence of hate crime was found in the possession of the “student” who committed the hate crime.

Fifth, the January 2 hate crime incident on the AAU campus cannot be seen as an isolated incident. The fact that periodic and recurrent campus hate crimes have been occurring “for decades” on Ethiopian university campuses is  uncontro- verted.  Why haven’t university officials taken swift and decisive action to prevent campus hate crimes with full foreknowledge of the occurrence of such incidents? Is the lack of action and intervention by university officials evidence of official tolerance, complicity, indifference and/or gross incompetence in the investigation and prevention of the occurrence of campus hate crimes? The evidence further shows that in the aftermath of the hate crime, university officials took no decisive action or implemented no preventive measures to ensure the safety of other students who could be targets of ethnic harassment on campus from a potential flare up of violence.

Sixth, why did AAU officials publicly announce, without a full and independent fact finding investigation, that the “conflict was instigated by students who found derogatory statements posted on the wall”? Why haven’t AAU officials empaneled an internal and/or outside independent investigation to thoroughly examine  the causes and participants in the hate crime and make recommendations to prevent such incidents in the future? Why have university officials left this incident entirely to the police?  Could it be that university officials turn a blind eye to campus hate crimes because they are directed to do so?

Seventh, why are the victims of this hate crime also the targets of arrest and detention by police?

In short, the totality of the circumstantial evidence on the hate crime committed on the AAU campus does not point an accusatory finger at students. The evidence points an accusatory finger at an invisible hand. To identify and apprehend the perpetrators of this hate crime, one must look not only for the invisible fingers that wrote the graffiti and derogatory statements on library and dormitory walls but also the hands that beat up the students to a pulp and ceaselessly bellow blasts of  hot air to spread and ignite ethnic strife, fear, hate and loathing among university students.

Be that as it may, it is now time, high time, the right time…

A Time to Heal, A Time to Embrace and a Time to Reconcile

It is written that “To everything there is a season, and a time to every purpose under the heaven.” There is a time to weep, a time to mourn, a time to cast away stones. There is a time to build up and a time to speak up. Then there is a time to embrace, a time for peace and a time to heal. There is a time to reconcile.

This is the time — the right time — for Ethiopia’s young people to heal in the schools, universities, the work places, the neighborhoods and in the streets. This is the time — the right time — for Ethiopia’s young people to embrace each other in the spirit of brotherhood and sisterhood; to hold hands and celebrate their diversity and honor their common ancestry and history.

This is the right time for all of Ethiopia’s young people  to break the cycle of ethnic hatred and violence; the right time to end the futile tradition of grievance and victimhood; the right time to abandon the culture of fear, hatred and loathing.

This is the right time for Ethiopia’s youth to lock fingers and join hands to heal the open wounds of fear, loathing and antagonism in their hearts, minds and souls. This the right time to stop seeing fellow students as enemies and adversaries. It is the right time to make peace and embrace each other as brothers, sisters and partners. This is the time for Ethiopia’s  best and brightest to work together for a better future, to dream of  alternative futures built on a solid foundation of the rule of law, respect for human rights and democracy. As Nelson Mandela taught, “If you want to make peace with your enemy, you have to work with your enemy. Then he becomes your partner.”  It is time to make those we perceive to be enemies our partners.

This is the right time to unite against hate and hate crimes on and off campus. It is the right time to purge hatred from our minds and hearts; the right time to break the chains of fear that shackle and cripple young minds and hearts. It is time for Ethiopia’s Cheetahs to liberate themselves from the burdens of the past.

This is the right time for all of Ethiopia’s young people  to bury the hatchet, to declare once and for all, “No! We refuse to hate each other because we belong to one ethnic group or another. No! we refuse to hate each other  because we worship the same God by a different name or live in different corners of the land. No! We WILL NOT be manipulated or puppet-mastered to hate each other. We will not hate because we are civilized humans. We will not behave like predatory beasts who prey.”

This is also the right time not to do the wrong thing. This is the wrong time to engage in finger-pointing, teeth-gnashing, bellyaching or revenge planning. This is the wrong time to demonize and scapegoat one group of students as predatory beasts and disempower another group as helpless and hopeless prey. Both groups of students are the prey of those who write words of hate on library and dorm room walls.

A Word or Two from One Hippo to Many Cheetahs

Many young Cheetahs may find it amusing to listen to a member of the Hippo Generation. After all, we Hippos are known for being “intellectually astigmatic”, “lacking in vision”  and “not caring if the whole country collapses around us as long as our pond is secure.”  But I respectfully ask the youth to lend me your ears and hear me out.

Be courageous!

Be the first generation of Ethiopians to unchain yourselves and the rest of us from the burdens of the past.

Be the first generation to put an end to historic hatreds and resentments, sow the seeds of understanding and tolerance and open a new chapter of truth and reconciliation in Ethiopia’s history.

Be the first generation to close the wounds of hatred that have festered for generations and declare to future generations that they will not be prisoners of the mistakes and blunders of the past generations.

Be the first generation to accept the fact that we are all equal members of the human race and will not race to the bottom to affirm our ethnicity over our common humanity.

Be the first generation to make a peace offering to each other; to bury the hatchet once and for all; to use your fingers not to pull triggers and write hateful graffiti but stretch out your fingers to shake hands, to hold hands and to lend hands.

Be the first generation to affirm the divinity in our religious diversity.

Be the first generation to say No! to insidious ethnic, religious and gender divisions.

Be the first generation to cover the walls of the libraries, dorm rooms and even toilets with graffiti of  reconciliation, understanding, harmony and love.

Be the first generation to declare that you, the proud Cheetahs, are the captains of your country’s destiny and not the tired, corrupt, scheming, unprincipled and self-serving Hippos.

Be the first generation to be all you can be and to think what you will.

Be the first generation to win the war declared on our human dignity and common humanity, on our civility, morality, cordiality, integrity, and national unity by winning the struggle for the hearts and minds of your fellow youths.

Be the first generation to end the bitterness of yesterday and restore it with the sweetness of reconciliation today and tomorrow.

The Moment of Truth Has Arrived: Can the Cheetahs Save Themselves and Us? 

The moment of truth for Ethiopia’s best and brightest has arrived!

Can Ethiopia’s best and brightest Cheetahs rescue themselves from the burden of the past and the legacy of ethnic prejudice and religious bigotry?

Can these Cheetahs save the cynical, wretched and laggard Hippos from themselves?

Can they teach us to create ethnic harmony out of ethnic strife, understanding out of intolerance? Can they transform sectarian discord into spiritual concord for themselves and the people of Ethiopia?

Can the Cheetahs rescue our humanity from clutches of ethnic and sectarian inhumanity and bestiality?

Can Ethiopia’s Cheetah teach us the art of reconciliation? Can they enlighten us on the science of reconciliation?  Can they show us the path to reconciliation? Can they speak to us in words of reconciliation?

Can Ethiopia’s best and brightest come together as one Youth Force and make 2013 the Year of Ethiopian Cheetahs? Come together and bury the hatchet of ethnic strife and beat the swords of sectarianism into  ploughshares and harvest a plenitude of reconciliation?

Yes, indeed they can!

When I “proclaimed” 2013 as the Year of Ethiopia’s Cheetah Generation last week, I promised to reach, teach and preach to Ethiopia’s youth. Little did I think about the possibility of Cheetahs reaching, teaching and preaching to  me and my fellow Hippos. (That is why we Hippos are astigmatic (have distorted view) and myopic (near-sighted and narrow-minded; natural hazards of being a Hippo). Little did I think of a teachable moment coming for Cheetah’s and Hippos so soon.

So Ethiopia’s Cheetahs  and Hippos face an enormous challenge. The challenge for the Cheetah’s is they must now teach the Hippos the art of reconciliation. The challenge for the Hippos is that they must learn the art of reconciliation from the Cheetahs.

The Cheetahs now have a chance to play a historic role: Teach by example.

So I call upon the young men who were involved in the incident at Addis Ababa University and their friends and all of the other students to transform this ugly moment of conflict and strife on their campus into a beautiful moment of reconciliation. I ask them to reach out to each other and ask forgiveness. It takes great courage to say something as simple as, “I am sorry.”

I call on them to come together on their own —  one-on-one, in small and large groups — and discuss their  differences. Try to feel each other’s pain and anguish. Be sensitive to each other’s fears and never scorn each other’s tears.

I ask them to talk to each other with open minds, open hearts and open spirits. I ask them to listen to each other’s concerns, fears, hopes and despair. I ask them to walk a mile in the shoes of their fellow students. If their fellow students do not have shoes, I ask them to walk a mile bare feet and feel the sharp-edged rocks. I believe if  they walk hand in hand for a mile, with shoes or bare feet, they will have reasons to smile.

I ask Ethiopia’s Cheetahs to make 2013 the Year of Reconciliation and Peace.

Let January 2, 2013 be remembered in all history as the day Ethiopia’s university students  buried the hatchets of ethnic division, religious sectarianism and gender inequality.  Let the ugly incident at AAU serve as a teachable moment for the nation.

Take up the challenge to talk and listen to your fellow students and sow the seeds of understanding, tolerance and harmony.

I ask Ethiopia’s Cheetah Generation to lead the Hippo Generation. Do not follow us, for we know not where we are going. We are the Hippo Generation, the lost generation.

If you don’t accept the challenge and do what is right and right what is wrong, then you would have proved to the world that Ethiopia’s Cheetahs are only Hippos in training.

To everything there is a season, a time. This is the time for Ethiopia’s Cheetahs to heal and to reconcile.

Ethiopia’s Cheetahs! What time is it?

Ethiopia’s Cheetahs united can never be defeated!

 

Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.

Previous commentaries by the author are available at:

http://open.salon.com/blog/almariam/

www.huffingtonpost.com/alemayehu-g-mariam/ 

Amharic translations of recent commentaries by the author may be found at:

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24

 

ENTC requests diplomatic recognition from South Africa

Posted on

PRESS RELEASE
January 14, 2013

The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) has sent a communiqué to the South African Minister of International Relations and Cooperation, the Honorable Maite Nkoana-Mashabane, requesting a diplomatic recognition. The letter was submitted to the Ministry by Ato Israel Wondimu Negash, ENTC’s diplomatic representative in South Africa.

The letter explains ENTC’s mission, and discusses the worsening political, economic and security crises in Ethiopia, as well as the need for the South African government to help with a peaceful transition to democracy.

The Transitional Council was founded at a 3-day conference in Dallas, Texas, that was convened from July 1 – 3, 2012, with the participation of representatives from all over the world.

Diplomacy is one of the primary tasks that the ENTC general assembly assigned to the leadership at the July 2012 conference in Dallas.

For more info:
ENTC Foreign Relations Committee
85 S. Bragg St. Alexandria VA, 22312 USA
Tel: 202-735-4262
Email: [email protected]
Website: etntc.org

2013 የኢትዮጵያ የአቦሸማኔ ትውልድ ዓመት ይሁን!

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ

የአቦሸማኔዎች ዓመት

2013 የኢትዮጵያዊያን አቦሸማኔዎች (የወጣቱ ትውልድ) ዓመት መሆን አለበት፡፡

‹‹የአቦሸማኔው ዘመን የሚያመላክተው የአፍሪካን ጉዳይና ችግር በአዲስ መንገድና አመለካከት ማየት የሚችለውን አዲሱንና ቁጡውን ወጣት፤ አዲስ ተመራቂዎችንና ብቁ ባለሙያዎችን የሚመለከት ነው፡፡ ምናልባትም ‹‹ቁንጥንጥ ትውልድ›› ተብለው ሊጠቀሱ ይችላል:: ያም ሆኖ ግን የአፍሪካ አዲሶቹ ተስፋ ወጣቶቹ ናቸው፡፡ ግልጽነትን፤ ተጠያቂነትን፤ሰብአዊ መብትን፤ መልካም አስተዳደርን የቀለጠፈና ፈጣን አስተሳሰብን፤የሚረዱና ተግባራዊ እውነታንም የሚያስቀድሙ ናቸው›› የታወቀውና የተከበሩት ጋናዊው ኤኮኖሚስት ጆርጅ አይቴ አስረድተዋል:: ቀጥለዉም ሲናገሩ  ‹‹ አብዛኛዎቹ አሁን በአፍሪካ  በስልጣን ላይ ያሉት መሪዎቻቸው ከመጠን ባለፈ ምግባረ ብልሹ እንደሆኑና፤ የሚመሩትም መንገስት በስድብ የተካነ ግን በተግባራዊ መልካም ሀገርና ሕዝብን በሚጠቅም ጉዳይ እርባና ቢስ የሆኑ፤ ማለቂያ የሌለው የሰብአዊ መብት ድፍረትን የፈጸሙ መሆናቸውን ወጣቶቹ ጠንቅቀው ያውቃሉ››::

በኔ አመለካከት የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች ትውልድ፤የሚያካትተው ወጣት ተመራቂዎችንና ባለሙያዎችን፤ምርጥና ብቃት ያላቸው ምሁራንን ብቻ ሳይሆን፤ በነጻ ለማሰብ ለመወያየት፤ ለመመካከር ለመተንፈስ ፍላጎታቸው ያቆበቆበውንና በወገንተኝነት፤አድሎአዊነት፤በምግባረ ብልሹዎች  ቦታቸውና ሁለንተናቸው የተያዘባቸውን፤ፍርድ አልባ ለሆነ  ለእስርና እንግልት ስለሰብአዊ መብት መከበር በጮሁ  ቢያንስ አምናችሁ በስራ ላይ የዋለው  ሕገ መንግስት ተከብሮ ይተግበር ባሉና ለመከራና ስቃይ የተዳረጉትን የኢትዮጵያ ወጣቶችን በሙሉ ያካትትታል፡፡የኢትዮጵያ አቦ ሸማኔ ትውልድ የእስክንድር ነጋና የሰርካለም ፋሲል ትውልድ ነው፡፡ የአንዱዓለም አራጌ፤ውብሸት ታዬ፤ የርዕዮት ዓለሙ፤የበቀለ ገርባ፤ የኦልባና ሌሊሳ፤ እና የሌሎችም መሰሎቻቸው ትውልደ ዘመን ነው፡፡ የኢትዮጵያው አቦ ሸማኔ ትውልድ ብቻ ነው ኢትዮጵያን ከብረት ጥፍራሞች የግፍ አገዛዝ ቡጥጫና ከዲክታተር ሺፕ ማነቆ የሚያላቅቃት፡፡ ከእባብ ጥርስ፤ ከዕብድ ውሻ ክራንቻ፤ ከዋጣት የጨለማ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ፤ በማላቀቅ ወደ ብሔራዊ ዕርቀ ሰላም በማምጣት የበሰበሰና የአለቀለት ተስፋ ቢስ  በሃሰት መሰረት ላይ የተንሳፈፈውን ገዢ መንግስት በመለወጥ የሕዝብ አመኔታ ያለውና በሕዝቡ ፍላጎት ላይ በጠንካራ ሕዝባዊ መሰረት ላይ የተገነባ ስርዓት ለማቆም የሚችለው፡፡

አሁን ያለው ገዢ መንግስትና ከስሩ ኩስ ኩስ ባዮቹ የኢትዮጵያው የጉማሬ ትውልድ (ወይም አበው ነን ባይ ትውልድ) ወደ ጎን እልፍ በማለትና  በቃን በመቀበል ለአቦሸማኔዎቹ መንገዱን ማስተካከልና መልቀቅ አለበት፡፡ አይቴ እንዳለው ‹‹የጉማሬው ትውልድ ምሁራዊ አመለካከቱ ከዘመናት አገልግሎቱ የተነሳ ሞራ ሸፍኖታልና አስተሳሰቡ አሁንም በቅኝ ገዢዎች  መምህርነት ላይ እንደተጣበቀ ነው›› ጠጣር ድንጋይማ ከባድ  በመሆን የአሮጌው ኮሎኒያሊዝም ኢምፔሪያሊዝም አርአያን ከሃገር ሃይልና እምነት ጋር ጉማሬዎቹ አስተሳስረውታል፡፡ማንኛቸውንም የአፍሪካን ችግርና መከራ አገዛዙ ሊለውጠው ይገባል በሚል ባዶ ተስፋ ብቻ በመመኘት ራዕይ አልባ ሆነው፤ በምቹ መንበራቸው ላይ ተሰይመዋል፡፡ አገዛዙ ስልጣኑን የምያራዘመዉና የበለጠ ሥላጣንና ሃይል፤   የሚየዘው የበዛ የውጭ ዕርዳታና ችሮታ ሰለሚያገኝ ብቻ ነው፡፡ የጥቅም መፍሰሻ ቧንቧው እስካልደረቀ ድረስ፤ አገዛዙ ሃገሪቱ እንዳለች ብትጠፋ፤ ሕዝቡ ጨርሶ ቢያልቅ ደንታቸው አይደለም፡፡

የኢትዮጵያ ጉማሬ ትውልድ በተጠናበረ አመለካከት ኢላማውን የሳተ ብቻ ሳይሆን፤ ቅርብ አላሚና አስተሳሰበ ጥቂት፤ ለራሱ ብቻ እርባና ቢስ አጀንዳ የሚያወጣ ጭፍን ትውልድ ነው፡፡ በስልጣን ላይ ያለው የጉማሬ ገዢው መንግስት በረግረግ የሚሰጥም አሸዋ ላይ ባለ የከፋፋይ የዘር ፖለቲካና ክፉኛ በተጠናወተው ብቀላ ላይ ተጠምዷል፡፡ ምንም የማይሳነው ነው የሚሉት የግዛት መንግስታቸው ዐመጸኛ እንጂ  ሌላ ሊሆን የማይችል ነው፡፡ ከንፈሮቻቸው በተላቀቁ ቁጥር ምላሳቸው ለሆዳቸውና ለኪሳቸው መሙያ የሚገለገሉበትንና መመሪያችን በማለት በየአደባባዩ የሚያሞካሹትን ‹‹ኒዎሊቤራሊዝምን›› ለማውገዝና ለመንቀፍ ታጥቀው ተነስተዋል፡፡ ስልጣንም ላይ የሰመጠ መርከብ ላይ እንደሚጣበቁበት ሐዋሳት ሰፍረውበት ለመኖር ነው እቅዳቸው፡፡ ከውጭ መንሥታት የሚቸራቸውን ዳረጎት እንደከፍተኛ የእድገታቸው ግብ አድርገው ይቆጠሩታል ጉራቸዉንም ይነሰነሱበታል፡፡ ለነዚህ ጉማሬዎች ደግሞ ወጣቱ  ዋነኛ መገልገያ መሳርያቸው ነው፡፡ የአፍ ዳረጎት ይቸሩታል፡፡ መለስ ዜናዊ በዚያ ዝነኛው የ99.6 የምርጫ ሃፍረተ ድሉ ወቅት ባደረገው ዲስኩር፤ ወጣቱን በማይጨበጥ ባዶ ቃላት ሸረደደው፡፡ ‹‹በመካሄድ ላይ ባለው የሃገሪቱ ልማትና እድገት ላይ የሃገራችን ወጣት ትውልድ ተሳታፊ መሆን በመጀመሩና በተሰማራበትም (የኮብል ስቶን ባለሙያነት) መስክ ውጤታማ በመሆኑ ወጣቱን ላመሰግን እወዳለሁ፡፡ ወጣቱ ላሳየውና ላረጋገጠው ድጋፉ ለማይታጠፍ አቋሙ ምስጋናችን ይድረሰው፡፡›› በማለት ማሞካሻና በንብረትንት ማሰባሰቢያ ዲስኩር ነበር ያደረገው፡፡

ከስልጣን የገተገለሉትም ጉማሬዎች ወጣቱንና ሴቶችን በፓርቲያቸው መዋቅር ውስጥ አመራር ላይ ለማካተትና ተግባራዊ ተሳትፎ እንዲያደርግ  ለማሰባሰብ አልቻሉም፡፡ በዚህም ምክንያት እራሳቸውን  ባልተረጋጋ ፖለቲካ ሂደት ውስጥ በማስገባት ፖለቲካውንም አሽመድምደውታል፡፡ ስለዚህም እንደገና ለማንሰራራትና ለመታደስ፤ በአዲስ ሃይልና ዘዴ ለመደራጀትና ብቃትም ለማግኘት፤ ለማገገም ወጣቱ ያስፈልጋቸዋል፡፡ ወጣቱን ያላቀፈና ስልጣን የተነፈገው የጉማሬ ትውልድ፤ በስልጣን ላይ ላለው የጉማሬ ስብስብ መቀለጃ፤ መተረቻ መዘባበቻ መሆን ብቻ ነው ትርፋቸው፡፡

የታገተው አቦሸማኔ

አሳፋሪው አሉባልታ መሰል ባዶ ቃል ደግሞ ‹‹በመካሄድ ላይ ካለው ልማት ወጣቱ ትውልድ ተጠቃሚ ሆኗል›› መባሉ ነው፡፡ ሃቁ የሚያሳየው ደግሞ ፈጽሞ ከአባባሉ ጋር የማይገናኝ ተቃራኒ ነው፡፡ ከ18 ዓመት በታች የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብዛት 41 ሚሊዮን አለያም  ከአጠቃላይ የሕዝቡ ቁጥር ገሚስ ነው ተብሎ ቢገመትም፤ የ ዩኒሴፍ ዘገባ እንደሚያመለክተው ደግሞ፤  ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑት ሕጻነት በሞት መቀጠፍ ዋነኛ መንስኤው የተመጣጠነ የምግብ እጥረት መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ኢትዮጵያ በ5 ሚሊዮን የሚገመቱ ወላጅ አልባ ሕጻናት አሏት ወይም 15 በመቶ ይሆናሉ፡፡ ከኒህ ውስጥ 800,000 የሚሆኑት ለዚህ የተዳረጉት በኤይድስ ሳቢያ ነው፡፡ የገጠሩ ስራአጥ ቁጥር ሰባ በመቶ ደርሷል፡፡ በ2011 በተካሄደው የተባበሩት መንግስታት ካፒታል ዴቬሎፕመንት ፈንድ  ሪፖርት መሰረት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ካሉት ሃገራት ሁሉ አነስተኛው መጻፍና ማንበብ የሚችሉ ወጣቶች ያሉባት ሃገር ናት ብሎአል፡፡ በ15-24 የዕድሜ ክልል ውስጥ ያለው የትምህርት ሁኔታ በአሳፋሪ 43 በመቶ ነው:: በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ምዝገባው  ዘገምተኛ 30.9 በመቶ፤ ሲሆን: በሚያሳዝን መልኩ 77.8 በመቶው የኢትዮጵያ ወጣት ኑሮውን ከ2 የአሜሪካን ዶላር እጅግ ባነሰ ሂሳብ ነው የሚኖረው፡፡

ወጣት ኢትዮጵያውያን ሥራ ለማግኘት ሕልውናቸውን ለመሸጥ እየተገደዱ ነው፡፡ የአሜሪካን ስቴት ዲፓርትመነት የሰብአዊ መብት 2010 ዘገባ መሰረት፤ “ታማኝ ምንጮች እንዳስታወቁት፤ ስራ አጥ ወጣት ዜጎች የገዢው ፓርቲ አባል መሆናቸውን ካላረጋገጡ ፎርሙን ሞልተው ታማኝነታቸውን ካላረጋገጡ በስተቀር  የዜግነት መብታቸው የሆነውን የስራ ማፈላለጊያ የቀበሌ ማስረጃ ጨርሶ ማግኘት አይችሉም” ሲል አትቶዋል፡፡ በመንግስት መስሪያ ቤትም ለመቀጠር የገዢው ፓርቲ አባልነት ዋነኛው መሟላት ያለበት ግዴት ነው፡፡ የፖሊስ አስተዳደር ባለባት ሃገር ኢትዮጵያ ለመኖር ዋስትና፤ ለመማር ዋስትና፤ ለመቀጠር ዋስትናው የገዢው ፓርቲ አባልነት ብቻ ነው፡፡ የአሜሪካን ስቴት ዲፓርትመነት የሰብአዊ መብት 2010 ዘገባውን ሲያጠቃልል ብቸኛና ለስራ መቀጠርም ተቀባይነት ወዳለውና የውጭ ትምህርትም ለማግኘት ዋነኛ ማሟያ ነጥብ የሆነው የአዲስ አበባ ዩኒቬርሲቲም ገብቶ ትምህርት ለመከታተል የሚመኝ ወጣት በቅድሚያ የገዢው ፓርቲ አባል በመሆን ፎርሙን ሞልቶ፤ ቃለ መሃላ ፈጽሞ፤ ታማኝነቱን አረጋግጦ፤ በዩኒቨርሲቲው የሚታሰበውን አድማ ላለመሳተፍና ለማክሸፍም ለሚመለከተው በማሳበቅ ማገልገሎ እንዳለባቸው ቃል ገብተው ነው ተቀባይነት የሚያገኙት፡፡

ተስፋ በመቁረጥና እርካታ በማጣት፤በርካታ ወጣቶች ትምህርታቸውን በማቋረጥ በጣም አሳፋሪና ሕሊናን አድካሚ፤ ስብዕናን ገፋፊ  ወደ ሆኑ ተግባር በመሰማራት ወደ አደንዛዥ እጽ፤ መጠጥ፤ ትምባሆ፤  ሱሰኝነት እና እንዲሁም ወደ ወንጀልና ልቅ የግብረስጋ ግንኙነት በመሰማራት በወሲብ ለሚመጡ በሽታዎች፤ ኤይድስን ጭምር በሽተኞች በመሆን ላይ ናቸው፡፡ ችግረኞች የሆኑት ወጣቶች (ሰፊውን ቁጥር የሚይዙት ወጣቶች) ከትምህርትና ከስራ ማግኘት እድል የተነፈጉ ናቸውና በራሳቸውም በሃገራቸውም ላይ ተስፋ ቆርጠዋል፡፡ የተከበሩት የሙስሊሙ ሕብረተሰብ የሃይሞነት አባትና መሪ ሃጂ ሞሃመድ ሰኢድ ያነሱት ጥያቄ እንቅልፍ ነስቶ በሃሳብ ያዋዥቀኛል፡- ‹‹ለመሆኑ አሁን የተረፈ የኢትዮጵያ ትውልድ አለ? ወደ ዩኒቨርሲቲው የገቡት ወጣቶች እኮ ሕሊናቸው በጫት ሱስና በሲጋራ የተጠመደ ነው፤ ይሄ ገዢው ፓርቲ እኮ ትውልዱን አጥፍቶታል” ሲሉ አኝህ የተከበሩ  የሃይማኖት አባት ተናግረዋል ፡፡

አቦሸማኔዎቹን ፍታ

በርካታ የጦማሬ አንባቢዎች ለሃገራቸው ነጻነትና ለውጥ ስለሚናፍቁት ግን በገዢው ማነቆ ተጠፍረው ስላሉት  ወጣት ኢትዮጵያዊያን ግንዛቤ እንዳለቸው አማናለሁ፡፡ በተጨማሪም አንባቢዎቼ ለኩሩዎቹ አቦሸማኔዎች ለእስክንድር ነጋ፤ ሰርክዓለም ፋሲል፤ አንዱዓለም አራጌ፤ ውብሸት ታዬ፤ ርዕዮት ዓለሙ፤ በቀለ ገርባ፤ ኦልባና ሌሊሳና ለሌሎችም በርካታ ቆራጥና አልበገር ባይ አቦሸማኔዎች  ሕገመንግስታዊ መብታቸውንለማስጠበቅ፤ የስልጣንን እውነተኛ ገጽታና ምንነት ለገዢዎች በማሳወቃቸውና ድምጻቸውን በማሳማታቸው ለእስር ስለተዳረጉ አኔም የማያቋርጠውንና ወደፊትም የሚቀጥለዉም ጥብቅናዬን አይዘነጉትም፡፡ በዚህ በአቦሸማኔዎቹ ዓመት፤ ወሳኝና አጣዳፊ ለሆነው የኢትዮጵያ ወጣቶች ስለተጋፈጡት ከፍተኛና ወሳኝ ግጥሚያ ከፍተኛ የትኩረት ጥሪ እያደረግሁ እንዲሁም ለጉማሬዎቹ፤ በተለይም በዲያስፖራው ላሉት ምሁራን አቦሸማኔዎች  የስነምግባር አስተዋጽኦና ትብብር በማድረግና ከወጣቱ ጋር ውህደት በመፍጠር፤ የአመራር ድጋፍ፤ማነሳሳት ድጋፍ፤ ማበረታቻ ምክርና ድጋፍ በማድረግ ከወጣቱ ጋር አንድነት እንዲፈጥሩ ነው፡፡

በጁን 2010 ሊካዱ በማይችሉ እውነቶች ላይ ተመስርቼ ጥሪ አቅርቤ ነበር፡- ለማስታወስ ያህል ‹‹ወጣቱ እንደፈንጂ ቦምብ ነው›› በማለት አቅርቤው የነበረውን ጦማር መመልከት ይቻላል፡፡ በዚህ ጦማሬ ላይ ወጣቱ ስለተጫነበት መከራና እራሱን እንዳይሆን ስለሚሸረብበት ደባ በሰፊው አቅርቤያለሁ፡፡ የኢትዮጵያ ወጣት በመላው ዓለም ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ በችግር፤ በመከራ ሽሽት፤ ከገዢው የእስራት ማነቆ ለማምለጥ እንደተበተነም አሳሰቤያለሁ፡፡

በዚህ በኢትዮጵያዊያን የአቦሸማኔ ዓመት፤ እኛ በጉማሬ ትውልድ ሕሊና ውስጥ ያለነው፤ ለፈጠምነው ስህተትና ጥፋት ንስሃ በመግባት፤ከወጣቱ የአቦሸማኔ ትውልድ ጋር እርቅና መግባባት ማድረግ ይገባናል፡፡ ምንም እንኳን ትግበራው እስከዚህም ባይሆን፤ ፕሬዜዳንት ኦባማ በአፍሪካ ስለሚከሰተው መጥፎና አስቸጋሪ ሁኔታ ያላቸው ግምትና አስተሳሰብ ትክክል ነው፡፡ አንዳሉትም ‹‹ በአፍሪካ ለውጥ የሚያመጡት እንደ ንክሩማና ኬንያታ ያሉት ታላላቅ ግዙፎች እንዳልሆኑ ለመገንዘብ ችለናል፡፡ ባለፉት ትውልዶች ሳይታወቅ የቀረው፤ ይሀን ለውጥ በአፍሪካ ውስጥ እውን ለማድረግ ብቃቱ ችሎታውና እውቀቱ፤ ፈቃደኝነቱና የጸና አቋም ያላቸው ወጣተቶች ናቸው::›› እኛ  ጉማሬዎች የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ለሕልፈት በተዳረጉ ዲክታተሮች፤ በጣዕረሞታቸው አለያም በሙት መንፈስ አምላኪዎቻቸው የሚወሰን አለመሆኑን አጢነን ልንረዳው ይገባናል፡፡የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ሃገሪቱን እንደግል ንብረታቸው ለመያዝ በሚፍጨረጨሩት፤ የቁማር መጫወቻ ሜዳቸው ሊያደርጓት በሚያልሙት፤ ወይም በስልጣናቸው ላይ ለመቆየት የላቸውን ሊዛዊ ዘመን ለማራዘም በመዳክሩ፤ የጎሳ ልዩነት ፖለቲካ በሚረጩት፤ ፈጥሞ አይወሰንም፡፡ የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው ጠንካራና ጤናማ በሆነው የአቦሸማኔዎች ጥምረትና አንድነት በአንድ ድምጽ በመናገር፤በተጨበጠ መዳፍ ውስጥ እንዳሉ ጣቶች የተባበረና የተጣመረ አካሄድ፤በመመራት ለአንድ ወሳኝ ግብ በተሰለፉት አቦሸማኔዎች ብቻ ነው፡፡

ከስልጣን ውጪ ለሆኑት ጉማሬዎችና፤ በጎን ሆነው የሚሆነውን ለሚጠብቁት አንድ መልእክት አርቅቄያለሁ፡፡ በቃችሁ፤ ተነሱ፤ ንቁ፤ በትክከለኛው ጎዳና መራመድ በመጀመር  ቁጥራችሁን ከወጣቱ ጋር አስተካክሉ፡፡ ከተጣለብን የራሳችን የጥላቻ ጎሳ ፖለቲካ ሊያላቅቁንና በትክክለኛው መንገድ ሊያራምዱን የሚችሉት እነዚህ ወጣቶች ብቻ ናቸው፡፡ ከተጫነብን የሃይማኖት ወገንታዊነት፤ ሊያገላግሉን የሚችሉት እነዚህ ወጣቶች ብቻ ናቸው፡፡ ካደረብን የፖለቲካ ዘይቤ ግጭት ነጻ የሚያደርጉንም እነሱው ወጣቶቹ ናቸው፡፡ ከዲክታተርሺፕ ማነቆና ጫና፤ የሚያድንኑም እነዚሁ ወጣቶቹ ናቸው፡፡ ወደ አቦሸማኔዎቹ ወጣቶች በመቅረብ፤ ደግ ደጉን ማስተማር፤ ማሳሰብ፤ ማሳመንና ከሕሊና ባርነት ነጻ በማድረግ ፈጠራቸውን በስራ ላይ ለማዋል እንዲችሉ መንገዱን ልናጠራላቸውና ልንደግፋቸው ግዴታችን ነው፡፡

በየአቅጣጫው መደራረስ አለብን፡: አቦሸማኔዎቹ ባሉበት የዘመኑን ቴክኒዎሎጂ በመጠቀም፤ያለንን እውቀትና የስራ ልምዳችንን ሁሉ በሁሉም መስክ ማካፈል አለብን፡፡ ሊሉ የሚፈልጉትን ማዳመጥ አለብን፡፡ እነሱ በጉልህ የነደፉትን እቅድና አስፈላጊ ነው በማለት የሚያነሷቸውን ነጥቦች መቀበልና መርዳት አለብን፡፡ ለረጂም ጊዜ ወጣቱን ከጉዳዩ፤ ከውይየቱ፤ ከድርድሩ አግልለን አርቀን አቆይተነዋል፡: ማድረግ ያለባቸውን በድፍረትና በፍጥነት እየነገርናቸው፤ እነሱ ለሚሉት ግን ጆሮ ዳባ ልበስ ብለናል፡፡ ከችልታ መለስ ባልን ቁጥር ብቻ መግለጫ እንሰጣቸዋለን፡፡ የሚገባቸውን ከበሬታ የምንቸራቸው ግን አልፎ አልፎ ነው፡፡ የነሱን ብቃትና ችሎታ እያሳነስን የራሳችንን ችሎታ በማምጠቅ የራሳችንን ዓላማና እቅድ አስፈጣሚ እናደርጋቸዋለን፡፡ በአቦሸማኔዎቹ ዓመት ከጉማሬዎቹ ምሁራን መሰሎቼ ጋር ወጣቱን አቦሸማኔ እንድንቀርበውና እንድናውቀው እማጸናለሁ፡፡

ወጣቱን ማስተማር አለብን:: ለሁላችንም አስፈላጊ የሆነውን ሁሉ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፡፡ ሃጂ ሞሃመድ ሰኢድ አንደተናገሩት ከአንድነት ውጪ ምንም ሊኖረን አይችልም በማለት አስጠንቅቀውናል፡፡ ‹‹ሃገር ከሌለን ሃይማኖት አይኖረንም፤ ሃገር ሲኖረን ብቻ ነው ማንኛውም ነገር የሚኖረን::›› ለዚህም ነው ወጣቶቹ ሁሉ በአንድ ላይ የእማማ ኢትዮጵያ ልጆች በመሆን ሊተባበሩና ፤በዘር፤በሃይማኖት፤በጎሳ፤ በጾታና በሌላም ሰበብ የሚከፋፍላቸውን ማንኛውንም የፖለቲካ ዘይቤ በማራቅ ወደ ጎን በማለት፤ በመሰባሰብ ፤አንድ መሆን  የሚገባቸው፡፡ ዲክታተሮችና አምባገነኖች ምንም ከማያውቁት ወጣቶች ላይ መብታቸውን መስረቅ አያስቸግራቸውም፡፡ ‹‹ምንገዜም ያለማወቅ ለአምባገነኖችና ጨካኝ ገዢዎች ትልቁ የማሰመሰያና የማጭበርበሪያ የመሳርያ ፋብሪካቸው ነው::›› ኔልሰን ማንዴላ ሲያስተምሩን፤ ‹‹ዓለምን ለመለወጥ የምንጠቀምበት ታላቁ መሳርያ የምንገበየው እውቀት ነው›› ብለዋል፡፡ ከጨቋኞችና ከፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች የመከራ ጫና ለመላቀቅ ዋናው መሳሪያችን ወጣቱን በትምህርት በማነጽ እውቀትን ማስገብየት ነው፡፡  በአቦሸማኔዎቹ ዓመት፤ከጉማሬዎቹ ምሁራን መሰሎቼ ጋር አቦሸማኔዎቹን ማሃይምነትንና መሃይሞችህን እንዲዋጉ፤አላዋቂነትን በችሎታ፤ በማስረዳትና በበሰለና በዳበረ አእምሮ እንዲተኩት ማስተማር ይኖርብናል፡፡

ማሳመንም አለብን:፡ የሰላምን፤ የዴሞክራሲን፤የሰብአዊ መብትን፤ የሕግ የበላይነትን፤የተጠያቂነትንና የግልጽነትን መንገድ፤ ወጣቶቹን ማሳየት አለብን፡፡ ማንም ቢሆን እራሱን እንደሕግ ማድረግ አይችልም፡፡ ሰብአዊ መብትን የደፈሩና በዘር ማጥፋት ወንጀል የተሰማሩ ሊጠየቁ ይገባል፡፡በመንግስት ውስጥ መንግስት፤ በብሔር ውስጥ ብሔር፤ በሃገር ውስጥ ሃገር ሊኖር አይችልም፡፡ በዲያስፖራው ያሉትን ወጣቶች በዓላማ ሰንሰለት፤ በእጣ ፈንታ ሰንሰለት ከኢትዮጵያ ካለው ወጣት ጋር የምናስተሳስርበትን መንገድ መቀየስ አለብን፡፡ በከፊል እርግጥ የተሰራ ካርታ አለ፤ መደብ አለ፡፡ ያ መጥበብ አለበት፡፡ በኢትዮጵያ ያሉትም ወጣቶች ከሌሎች በኢትዮጵያ ካሉ ወጣቶች ጋር ሊገናኙ የሚችሉበትን እቅድ በመትለም፤ውጤታማ ውይይትና ምክክር በማካሄድ፤ ሃሳብ በመለዋወጥ፤ አብረው በመስራት ዴሞክራሲያዊ ተስፋን የሚያረጋግጡበትንና ተግባራዊ የሚያደርጉበትን እቅድ እንዲያወጡ ልንረዳቸው ይገባል፡፡ የኢትዮጵያን አቦሸማኔዎች ትውልድ የሚያጋጥሟቸው ፈተናዎች በርካታ ቢሆንም፤ የቻልነውን በማድረግ ወጣቱ የወደፊቱን የመሪነት ቦታ እንዲረከብ ማዘጋጀት አለብን፡፡ በርካታ ችግሮችን ሊፈታ የሚችል ጠንካራ አጀንዳ ለመቅረጽ እንዲችሉ መርዳት አለብን፡፡ ማደረግ ያለብን መንገዱን ማመላከት ነው፡፡ ጉማሬዎቹ ውሃ ለማቀበል ፈቃደኞች እስከሆኑ ድረስ አቦሸማኔዎቹ ከባዱን ጫና ለመሸከም ፈቃደኛ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ወጣቶች ለሠላማዊ ለውጥ መንገድ ለመክፈት፤ ብሔራዊ  የድርድር ሂደት ማመቻቸት አለባቸው፡፡

ቀደም ሲል ያልኩት ጉዳይ ቢሆንም አሁንም ደግሜ ደጋግሜ አነሳዋለሁ፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ አይቀሬ ስለሆነው ከፈላጭ ቆራጭ የጭቆና አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲ ሽግግሩ  አበክሬ ጽፌያለሁ፡፡ ሽግግሩንም ለማመቻቸት እንዲቻል ብሔራዊ  ውይይት እንዲካሄድ ድምጼን ደጋግሜ አሰምቻለሁ፡፡ ይህንንም ወጣቱ ተቀብሎ ከሥር መሰረቱ አንስቶ የአንድ ለአንድ በየብሄሮቹ ሁሉ በሃይማኖቶቹም፤ መንገድ ተልሞ እንዲያካሂድ ጠይቄአለሁ፡፡ ይህንንም ጥሪ ሳሰማ እምነቴ የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ያለው ጊዜው ባለፈበት የጉማሬ መንጋጋ የስልጣን ጥመኞች ሳይሆን፤ ለስላሳና ስስ በሆነው የአቦሸማኔዎቹ መዳፍ ውስጥ እንደሆነ እርግጠኛ በመሆኔ ነው፡፡ በዚህ የአቦሸማኔዎቹ ዓመት በሃገር ውስጥ ያሉትን ወጣቶችና በዲያስፖራው ያሉትንም ወጣቶች  ዕርቀ ሰላም የሚደረገበትን አስቸጋሪ ሁኔታ በማላላት መፍትሄ እንዲያስገኙ አሁንም ተማጽኖዬ ይቀጥላል፡፡ ጉማሬዎቹ ለዚህ ዕርቀሰላም መንገዱን ሁሉ የዘጉትና  ፈቃደኝነታቸውንም የነፈጉ ይመስለኛል፡፡ ጉማሬዎች ዕርቀሰላሙን በተደጋጋሚ ቢካሂዱም የተጠቀሙበት መንገድ ግን እርስ በርስ በመጠቋቆም ነው፡፡ አንዱ ሌላውን በመወንጀል እራሱን ነጻ ለማድረግ በመሟገት ነው፡፡ ወጣቶቹ  ግን፤ ይህን በሰላማዊና መግባባት በሚቻልበት፤ የተጣመመውን በማቅናት የጠበበውን በማስፋት፤ ትእግስትንና ቻይነት ባነገበ የሰለጠነ መንገድ ከመጓዝ ባሻገር ምርጫ የላቸውም፡፡ ይህን ሳያደርጉ ቢቀሩ ደግሞ የጎሳና የሃይማኖት ነፋስን ወራሽ መሆን አይቀርላቸውም፡፡

ተማጽኖዬን ለኢትዮጵያዊያን አቦሸማኔዎች ሳቀርብ፤እርስ በርሳቸው የሚመስላቸዉን ውይይት እንዲጀምሩ ነው፡፡ እንደሚታያቸው ብሄራዊ እርቀሰላምን ይተርጉሙት፡፡ የራሳቸውን ፖለቲካዊ መንገድ በመፍጠር አንድዮሽ ውይይት በሀይማኖት፤ በቋንቋ፤በጾታ፤ በክልልና በመደብ ያካሂዱ፡፡ የጦታውን ተሳትፎ ትኩረት በመስጠት የወጣት ሴቶችን በብሄራዊ እርቅ ላየ ተሳትፎ ማበራከት አስፈላጊነት አንዳለው አሰምርበታለሁ፡፡ እርቀ ሰላምን ውጤታማ ማድረግ፤ ድርድር ማካሄድን በተመለከተ፤ በሳይነሳዊ አመለካከትም እንደተረጋገጠው፤ ሴቶች ከወንዶች የበለጠ እርቀሰላምን ውጤታማ የማድረግ ብቃቱ አላቸው፡፡

ውይይት እርስ በርስ መነጋገርን ማካተት ብቻ ሳይሆን መደማመጥንም ይጥይቃል፡፡ የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች የስብጥር፤ የዓይነት ብዛታቸውን እንደጥንካሬ በመቁጠር ይሄው ብዛታቸው ለመበታተኛነት፤ በመከፋፈል ለሽንፈታቸው እንዳይውል እንዳይዳረግም መጠንቀቅ አለባቸው፡፡

ብድግ አንበል ከኢትዮጵያዊያን አቦሸማኔዎች ጋር!

አፍሪካውያን ጉማሬዎች (ለሰብአዊ ፍጡራን የተመደበውን ተምሳሌታዊነት ጨምሮ) አንሰሳት ድንበራቸውን በማስከበር ረገድ አደገኛ አውሬዎች እንደሆኑና ያንን ድንበር አልፎ የመጣባቸውንም ለጥቃት እንደሚዳርጉ ጠንቅቀው ያውቃሉ፡ በየዓመቱ በአፍሪካ ውስጥ ከአንበሳና ከዝሆኖች ሰላባ ግድያ በበለጠ በጉማሬዎች አንደሚፈጸሙ (ለሰብአዊ ፍጡራን የተመደበውን ተምሳሌታዊነት ጨምሮ) የታወቀ ነው፡፡ አቦሸማኔዎችን በፍጥነት የሚያህላቸው የለም፤ድክመታቸው ግን ሌሎች አዳኝ አውሬዎች ሲያግጥሟቸው ጅብ ቢገጥማቸው እንኳን፤ ፈጥነው አደናቸውን መተዋቸው ነው፡፡ የጉማሬ መንጋዎች ግጭት፤ ውድቀት፤ ይባላል፡፡ የአቦሸማኔዎች መንጋ ደግሞ ኅብረት በመባል ይተወቃል፡፡ በጎሳ፤በሃይማኖት፤ በቋንቋ፤በክልል አወቃቀር መስመር የሚደረግ የአቦሸማኔዎች ኅብረት፤ የጉማሬዎችን ግጭት ገጭቶ ለመጣልና የጅቦችን ማስካካት በማሸነፍ ኢትዮጵያን ማዳን ይችህላል፡፡

በዚህ የኢትዮጵያዊያኖች የአቦሸማኔ ዓመት፤የኢትዮጵያን ወጣቶች ለመርዳትና በበለጠ ጥንካሬያቸውን በማጎልበትና አስተዋጽኦዬን በማጠናከር ወደ ከፍተኛው አመርታቸው እንዲሸጋገሩ ሙግቴንና ክርከሬን አቀጠላለሁ፡፡ ሁሉንም ጉማሬዎች እህቶቼንና ወንድሞቼን በዚህ ሂደት እንዲተባበሩኝና አብረውኝ እንዲወግኑ እጠይቃለሁ፡፡ ምንግዜም ጨለማ ለብርሃን መንገዱን ይለቃል፡፡ ‹‹በጨፈገገው ሰማይ ላይ ነው አንጸባራቂ ከዋክብትን የምናያቸው›› የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች በመንፈስና በፈቃደኝነታቸው ሊጠነክሩ ይገባል፡፡ ጋንዲ እንዳለው፡– ‹‹ጥንካሬ ከአካል ግንባታ የሚገኝ አይደለም›› ወይም ከጠብመንጃ፤ ከታንክና ከጦር አውሮፕላኖችም አይገኝም:: ‹‹የሚገኘው ከማይበገር ፈቃደኝነት ነው::›› ዊንስተን ቸርችል ከጋንዲ የተማረ መሆኑን የምናውቀው ‹‹ ለማንኛውም ነገር ትልቅም ይሁን አነስተኛ፤ ፈጽሞ- ፈጽሞ- ፈጽሞ- በጭራሽ ፈጽሞ አታሸብርክ፤ ማሸብረክ የሚገባህ ለክብርህ ከሚኖረው የጸና እምነት ውጪ ለሌላ አታሸብርክ››  ለሃይል አታጎብድድ፤ ከጠላት በኩል ለሚታየው ግዙፍ ለሚመስል የጠላት ድንፋታ አታሸብርክ›› ሲል ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ አቦሸማኔዎች ጨርሶ ሊያሸበርኩ አይገባም:: በምንም አይነት! ጨርሶ ጨርሶ!

ፕሮፌስር ዓለማየሁ ገብረማርያም በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሳን በርናርዲኆ የፖሊቲካ ሳይንስ መምሀርና የህግ ጠበቃ ናችው።

*የተቶረገመው ጽሁፍ (translated from):   http://open.salon.com/blog/almariam/2013/01/06/ethiopia_2013_year_of_the_cheetah_generation

(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::) ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን  ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24