በቀጣዩ ሚያዝያ ለሚካሄደው አከባቢና የማሟያ እንዲሁም የቀበሌ ም/ቤት ምርጫ አላማቸውን ማስተዋወቅ ለሚፈልጉ ፓርቲዎች በተዘጋጀና በወያኔ ካድሬዎች ቁጥጥር በሚደረግበት መድረክ ላይ የተለያዩ አመለካከቶች ተንጸባረቁ፡፡
‹‹ለውድድሩ ካቀረብናቸው ወጣቶች 1/3ኛ ያህሉ ታስረዋል፡፡›› – አቶ ቡልቻ ደመቅሳ
‹‹ብዙ አኮኖሚስቶች፤ብዙ አናሊስቶች፤ብዙ…አሉን›› – አየለ ጫሚሶ
‹‹አባሎቻችን የኢዴአፓ አባልነታችሁ ኤክስፓየር አድርጓል ተብለዋል፡፡›› – አብዱረህማን
‹‹ህዝቡን ወተት በቧንቧ እናስመጣላችኋለን አንለውም፡፡›› – መስፍን ሽፈራው/መኢብን/
‹‹ደሃው ካለመረጣችሁ ማን ይመርጣችኋል?›› – በስብሰባው የተገኙት የወያኔ ጋዜጠኞች ጥያቄ
የየፓርቲው አመራሮች አላማቸውን ከማንጸባረቅ በተጨማሪ ምርጫውን ተከትሎ እየደረሱባቸው ያሉትን እንግልቶችና ውክቢያዎች ይፋ አድርገዋል፡፡ገንቢ በሆኑ አስተያየቶች የብዙዎችን ትኩረት እየሳቡ የመጡት የኦፌዴን ሊቀ መንበር አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ለምርጫ በእጩነት ካቀረቧቸው ወጣቶች አብዛኞቹ ያለምንም የህግ ስርአት እንደታሰሩ የገለጹ ሲሆን ‹‹ኢህአዴግ በወጣቶች ላይ ምን እንዳየ አልገባንም፡፡›› ብለዋል፡፡
ለቅንጅት የስራ አስፈጻሚ አካል ፓርቲውን ለማስረከብ እንቅስቃሴ ጀምሮ የነበረውና በጸሃፊውና በምክትሉ እቅዱ የከሸፈበት አየለ ጫሚሶ በውይይቱ ላይ ያቀረበው አንድ ሃሳብም አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ‹‹ቅንጅቱ…›› በማለት ዙርያውን ከገረመመ በኋላ ‹‹… ብዙ ኢኮኖሚስቶች፤ ብዙ አናሊስቶች፤ ብዙ ምሁራን… አሉን፡፡›› በማለት ስለማን እየተናገሩ እንዳለ ጠቋሚ ሊባል የሚችል ንግግር አድርጓል፡፡ በአሁኑ ሰአት በአየለ ዙርያ ያሉት ጥቂት ግለሰቦች ያላቸው የትምህርት ደረጃ የአብዛኞቹ ኮሌጅ ፈር በመሆኑ አሉኝ የሚላቸው ተሳክቶ ነገሮች መስመር ቢይዙ የምሁራን ስብስብ የሆነውን የስራ አስፈጻሚ ቡድን እንደሆነ ጠቁሟል፡፡ ይሁንና ይህ ግብ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በሚፈጠሩ ችግሮች መጨረሻውን ማወቅ አልተቻለም፡፡
በሌላ በኩል በትግሉ ውስጥ የቆየውና የመኢብን ሊቀ መንበር የሆነው መስፍን ሽፈራው የምርጫ ቅስቀሳ ሊፈጸሙ የሚችሉ ቃል ኪዳኖች ብቻ ሊፈጸምባቸው ሚገቡ መሆናቸውን ለማመልከት ‹‹ለህዝቡ ወተት በቧንቧ እናስመጣላችኋለን ብለን ቃል አንገባም፡፡›› በማለት ሁኔታውን ገልጧል፡፡
የኢዴአፓው አብዱረህማን አባሎቻችን ላይ በደል እየተፈጸመ ነው በማለት ያቀረበው ዝርዝር ማን ምንን ይነካል የሚል ከትዝብት ያላለፈ ጥያቄ አጭሮ አልፏል፡፡
ከሁሉም አሳዛኝ የተባለው አጋጣሚ ደግሞ በምርጫ 97 ወቅት ለይቶላቸው ለወያኔ ሲሟገቱ የነበሩት የወያኔ ጋዜጠኞች ለተቃዋሚዎች የተለመዱትን አፍራሽ ጥያቄዎች ሲያከታትሉ መታየቱ ነበር፡፡
በቀጣዩ ሚያዝያ ለሚካሄደው የአከባቢና የማሟያ ምርጫ የህዝቡን አመለካከት ለመገንዘብ በሚል በዛሬው እለት ከረፋዱ 4፡00 ሰአት ጀምሮ የወያኔ ካድሬዎች በአዲስ አበባ ክፍለ ከተሞች የቤት ለቤት ቅስቀሳ ጀመሩ፡፡
አብዛኛው ሰው ከጠዋት የአምልኮ ስፍራዎች ተመልሶ እቤት ይገኛል ተብሎ በሚታሰብበት ሰአት ቅስቀሳው የተጀመረ ሲሆን ህዝቡ ለካድሬዎቹ ይሰጥ የነበረው ምላሽ ተቃውሞ የነበረበት ነው ባይባልም ጉዳዩን በዝምታ በመመልከት የተወሰነና ለምርጫው ባለቤት ያለመሆኑን እንደሚያመለክት ከምልልሱ መረዳት ይቻል እንደነበር ሂደቱን የተከታተሉት ሪፖርተሮቻችን ዘገባ ያመለክታል፡፡
በቤት ለቤት ቅስቀሳው ወቅት ካድሬዎቹ ያነሷቸው ከነበሩት ጥያቄዎች የተወሰኑት ‹‹እስካሁን የነበረውን ኢኮኖሚያዊ እድገት የበለጠ ለማሳደግ መንግስት ምን ማድረግ አለበት ይላሉ?››፤ ‹‹የቤት እመቤቶች ኑሯቸውን ለማሻሻል በመንግስት ምን አይነት እገዛ ሊደረግላቸው ይገባል… (ይህ ጥያቄ የሚቀርበው ካድሬው በሩን ሲያንኳኳ የሚከፍቱት የቤት እመቤቶች ከሆኑ ነው)፤ በምርጫ 97 ያጋጠሙት ችግሮች እንዳይደገሙ ከመንግስት፤ ከህዝቡና ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይጠበቃል ብለው ያስባሉ?›› እና የመሳሰሉት የተለሳለሱ ውይይታዊ መሰል ጥያቄዎች ይገኙባቸዋል፡፡
በህዝቡ በኩል በምርጫ ታሪክ ይወክለኛል በሚል ሙሉ እምነት ጥሎ የመረጠው ቅንጅት ባለበት አሳሳቢ ችግር (ቀውስ) ውስጥ በመሆኑ፤ በቀጣዩ ምርጫ ራሳቸውን በተቃዋሚነት ካቀረቡት ጠንካራ ሊባሉ የሚችሉ ፓርቲዎች የተወሰኑት ብሄር ተኮር መሆናቸውና ህብረብሔራዊ ፓርቲዎቹም የጎላ ሚና መጫወት እንደማይችሉ በተለያዩ አጋጣሚዎች በማሳየታቸው፤ በጸጥታ ውስጥ ሆኖ የቅንጅትን ትንሳኤ የሚጠብቅ በመሆኑ፤ ለካድሬዎቹ መጠይቆች ተቃውሞ ማሳየቱ እርባና እንደሌለው የቆጠረ እንዳስመሰለው ሁኔታውን የተከታተሉት ሪፖርተሮቻችን ዘገባ ይጠቁማል፡፡
በምርጫ ታሪክ አስገራሚ ክንውኖች እየተካሄደበት ባለው የሚያዝያው ምርጫ ከአዲስ አበባ ደቡብ ምእራብ 19 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ በምትገኘው የአለም ገና ወረዳ የሚገኙት የምርጫ አስፈጻሚዎች ጽ/ቤታቸውን በመዝጋት የወያኔ እጩዎችን ብቻ በማስተናገድ ላይ እንደሚገኙ በስፍራው ተገኝቶ ያረጋገጠው ሪፖርተራችን ዘገባ አመለከተ፡፡ የምርጫ ጣብያው ሃላፊ የሆኑት አቦይ ሃይሌ በርሄ ሃላፊነት የተሞላው ተግባር በማከናወን ላይ ነን የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ወረዳዋ ለአዲስ አበባ ካላት ቀረቤታ አንጻር ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎቻቸውን ያቀረቡ ቢሆንም ባለፈው ሳምንት አንድ የኦህኮ እጩ ላይ ከፍተኛ ድብደባ ከተፈጸመ በኋላ የምርጫ አስፈጻሚዎቹ ከቀበሌው የአስተዳደር ሰራተኞች ጋር በመሆን በለየለት ሁኔታ የወያኔን እጩዎች ብቻ ማስተናገድ ጀምረዋል፡፡
በተያያዘ ዜና በምእራብ ሸዋ ዞን ከአምቦ ከተማ 33 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ በምትገኘው ጉርሰሉ ከተማ ኦፌዴን እጩ የነበሩ ግለሰብ ትናንት ሌሊት ላይ ከቤታቸው ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን እስካሁን የደረሱበት እንደማይታወቅ ከጽ/ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ምርጫ 97ትን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ ወያኔ ያሰራቸውንና የተፈረደባቸውን እስረኞች ለማስፈታት በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የቅንጅት የስራ አስፈጻሚ ቡድን ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆኑን አንድ የስራ አስፈጻሚ አባል ለዜና አገልግሎቱ ገለጹ፡፡ ወ/ት ብርቱካን በዚህ ሳምንት አሜሪካ ውስጥ በሚካሄደው የቅንጅት ሰሜን አሜሪካ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለመገኘት የነበራቸውን እቅድ የሰረዙበት ዋናው ምክንያት ይሄው መሆኑ ተጠቁሟል::
በቅርቡ 28 ያህል የቅንጅቱ ጠንካራ አባላት የይቅርታ ሰነድ ፈርመው እንደወጡ የሚታወስ ሲሆን ጉዳያቸው በሂደት ላይ የነበሩ እስረኞች የፍርድ ውሳኔ ሳያገኙ ይቅርታውን ሊያገኙ አይገባም የሚል አቋም ወያኔ በመያዙ የቆዩ ቢሆንም በአሁኑ ሰአት አስር ያህል አባላት የፍርድ ውሳኔ ያገኙ በመሆኑ እነሱን የማስፈታቱ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠሉን የስራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡
የፍርድ ሂደቱን በማጓተት የትግሉን አቅጣጫና ትኩረት እስረኞቹን በማስፈታቱ ላይ ብቻ ለማድረግ የወያኔ ፍርድ ቤት እያደረገ ያለውን የተጓተተ አሰራር አስመልክቶ አባሉ በሰጡት አስተያየት ካለው የስራ ክፍፍል አንጻር ችግር አይፈጥርብንም ብለዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከእስር የተፈቱትና ወደየትውልድ አከባቢያቸው የሄዱት አባላት በወያኔ ካድሬዎች የማስፈራራት ሙከራ እየተደረገባቸው መሆኑን ለዜና አገልግሎቱ ገልጸዋል፡፡
በአየለ ጫሚሶ ቡድን አባላት ፍላጎትና ተነሳሽነት ቅንጅትን በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሚመራው የስራ አስፈጻሚ አካል የማስረከብ ሂደት በግላዊ አጀንዳዎችና ፍላጎቶች የተነሳ ተቋረጠ፡፡
ተቀባይነት በማጣትና በደጋፊ ድርቅ የተመቱት የአየለ ጫሚሶ ቡድን አባላት ከህብረተሰቡ እየደረሰባቸው የነበረውን ጫናና የፖለቲካ ሚዛኑን በማስላት ከስራ አስፈጻሚው ወኪሎች ጋር ለመወያየት ጥረት አድርገው የነበረ ቢሆንም በተለይ የአየለ ምክትል የሆነው ለገሰ ቢራቱና ጸሃፊው ሳሳሁልህ ከበደ የተለያዩ መደራደሪያዎችን ለመጠየቅ በመሞከራቸው ጉዳዩ በአጭሩ ቀርቷል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ቀጣዩን የትግል እንቅስቃሴ በጽናት ይወጣሉ የተባሉ የቅንጅቱ ነባር አባላት በሁሉም ክፍለ ከተሞች ውስጥ አባላትን የማደራጀትና ህጋዊ ፓርቲ በሚመሰረትበት ወቅት ሊከናወኑ በሚገባቸው ተግባራት ላይ በሰፊው እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ አንድ የአመራር አባል ለዜና አገልግሎቱ ገልጸዋል፡፡
By Louis Charbonneau
UNITED NATIONS, (Reuters) – Eritrea does not want another war with Ethiopia and seeks good relations with its neighbor, provided Addis Ababa withdraws from Eritrean territory, Eritrea’s U.N. ambassador said on Friday.
Ethiopia and Eritrea have both moved tens of thousands of troops to the border because of a dispute over their 620-mile (1,000-km) border. U.N. officials have expressed fears that the present withdrawal of U.N. peacekeepers from the border region could open the door to a new conflict.
“I would like to assure you that we in Eritrea are sick and tired of wars,” Ambassador Araya Desta told Reuters in an interview. “We don’t want another war. We are not warmongers.
“There is no reason why we should not have good relations with Ethiopia, provided they withdraw from Eritrean territory,” he said.
Ethiopia also has said it does not want a new war.
U.N. peacekeepers started work in 2000 after a two-year border war between the Horn of Africa neighbors that killed an estimated 70,000 people.
The peacekeepers have been stationed in a 15.5-mile (25-km) buffer zone inside Eritrea. But Asmara turned against the mission because of U.N. inability to enforce rulings by an independent boundary commission awarding chunks of Ethiopian-held territory, including the town of Badme, to Eritrea.
On Thursday, the U.N. Security Council condemned what it called “systematic violations” of its resolutions by Eritrea, including a food and fuel blockade, which led to a decision by the U.N. mission on the Ethiopian-Eritrean border to withdraw.
The council statement came as the 1,700-member force, known as UNMEE, sought to regroup in the Eritrean capital Asmara after being forced by the blockade to leave the disputed border it monitored for more than seven years.
“We are very sorry about that (council statement),” Desta said. “We are very mad about this … We are cooperating (with UNMEE) in all areas.”
ERITREA: U.N. TROOPS HAVE FOOD
Although Asmara has said the U.N. presence on the border was tantamount to occupation, U.N. officials have said the Eritreans were making it difficult for UNMEE to leave the border zone. However, a U.N. spokesman said on Friday there had been no problems reported on Thursday.
Desta denied there was a food or fuel blockade.
“We didn’t cut off the food supplies,” he said. “Food has reached those people in the countryside. They (currently) have enough for one good month.”
Western diplomats have said they suspected Eritrean soldiers wanted to get their hands on UNMEE’s equipment, which would explain why they were making it difficult for them to withdraw. Desta denied that allegation.
“We are not expecting anything from UNMEE,” he said.
On Wednesday, Eritrea accused the United Nations of making false accusations against it.
“The press offices of the United Nations and other private media have been leveling unfounded accusations against Eritrea about UNMEE’s situation in the country,” the Eritrean mission to the United Nations said in a statement.
Desta said he had personally complained to the United Nations about what Asmara sees as incorrect information it has been providing to the media.
(Editing by Bill Trott)