Skip to content

Author: EthiopianReview.com

Bahrain's Maryam wins Stockholm race

Gulf Daily News

BAHRAIN’S Maryam Yusuf Jamal won the women’s 1,500m race by the narrowest of margins at the ‘GE Galan’ indoor athletics meeting in Stockholm late Thursday night.

Maryam, running in her first race of the year, comfortably paced herself in the front alongside Ethiopia’s Gelete Burka and Russia’s Olesya Chumakova over the race’s opening three laps (1,200m).

But the 23-year-old Bahraini struck with one lap to go, when she dropped Chumakova and opened up a significant gap ahead of Burka.

The Ethiopian youngster however would not give up easily, and was able to cut the gap to about a half-metre from first. But Maryam proved to be too strong in the end, and she was able to stave off the late challenge and clinch the win in four minutes 04.30 seconds, just seven-hundredths of a second ahead of Burka.

Chumakova was also not far behind, finishing in 4:07.42 for third. In fourth and fifth place respectively were Britons Lisa Dobriskey (4:08.88) and Susan Scott (4:09.07), who each set a new personal best in the event.

Sonja Roman (4:11.42) of Slovakia, Helen Clitheroe (4:12.22) from the UK and Sandra Teixeira (4:14.72) of Portugal rounded up the top eight. Thirteen runners took part in the event, with only one not finishing.

The meeting was held as part of the International Association of Athletics Federations indoor season. It will Maryam’s only indoor event, according to her husband and coach Tareq Sabt, as she prepares to represent Bahrain in the World Indoor Championships in Valencia next month.

ምርጫ ቦርድ የተቃዋሚ እጩዎችን መታወቂያ ከለከለ

የምርጫ ቦርድ ህግ በሚያዘው መሰረት አስፈላጊውን ሂደት አሟልተው ለሚያዝያው የአከባቢና የማሟያ ምርጫ ራሳቸውን ያዘጋጁ የተቃዋሚ ፓርቲ እጩዎች ለመወዳደር ብቁ የሚያደርጋቸውን መታወቂያ ቢጠይቁም ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ሰበቦችን በመደርደር ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡

በህጋዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ ከምርጫ ቦርድ ፈቃድ ያወጡ ፓርቲዎች በምርጫ ወቅት ለመወዳደር የሚያስችላቸውን መታወቂያ ለማግኘት ፎቶ ግራፎችና አንዳንድ አስፈላጊ ፎርማሊቲዎችን አሟልተው እንደቀረቡ ቦርዱ ወዲያውኑ መታወቂያቸውን በመስጠት እጩዎቹ ወደ ህዝብ በመሄድ ራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ መፍቀድ እንዳለበት በህጉ የተደነገገ ቢሆንም ወያኔን ላይመርጡ ይችላሉ ተብለው በሚታሰቡ የምርጫ ጣቢያዎች ላሉና ጠንካራ ተፎካካሪዎች መሆናቸው ለተረጋገጠ እጩዎች መታወቂያውን ላለመስጠት መወሰኑን በሚረጋግጥ መንገድ እስካሁን በእንቢታው እንደጸና ይገኛል፡፡

ሁኔታውን አስመልክቶ ምን እርምጃ ለመውሰድ አስባችኋል በማለት ለተለያዩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን ቦርዱ በአስነዋሪ አቋሙ የሚጸና ከሆነ በቀጣዩ ሳምንት በጋራ ሆነው ጉዳዩን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡

አቶ በድሩ አደምን ለማባበል የተደረገው ጥረት አልተሳካም

ከአቶ ሃይሉ ሻውል ጋር በመሆን በተለያዩ የውጭ አገራት በመዘዋወር የገንዘብ ማሰባሰብ ሲያደርጉ የቆዩት አቶ በድሩ አደም ወደ አዲስ አበባ ከተመለሱ በኋላ ቸርችል ጎዳና ወደሚገኘው የቀድሞው የቅንጅት ቢሮ እንዲመጡ በእነ አቶ አባይነህ ቢጠየቁም ደርሶብኛል በሚሉት በደል የተነሳ ቅሬታ ስላደረባቸው አኩርፈው መቀመጣቸውን የቅርብ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡

በዛሬው እለት ጠዋት ሁለት የመኢአድ አባላት እቤታቸው ድረስ በመሄድ ያነጋገሯቸው ሲሆን እረፍት ላይ ስለሆንኩ በድርጅታዊ ጉዳዮች ላይ ሊቀመንበሩ እስኪመለሱ አልሳተፍም በማለት መልሰዋል፡፡

ተልእኳቸውን ያጠናቀቁ የሚመስሉት አቶ በድሩ ያኮረፉት ላደረጉት የውጭ አገር የድጋፍ ቅስቀሳና የገንዘብ ማሰባሰብ ከፍተኛ መጠን ያለው ክፍያ በመጠየቃቸው ነው መባሉ በአቶ ሃይሉ ሻውል ስር ያሉት ግለሰቦች በሙሉ ተመሳሳይ አቋም ያላቸው አድርጓአዋል ሲሉ በትግሉ አብረዋቸው የቆዩ አባላት በቅሬታ ገልጸዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ አዲስ ፓርቲ የማቋቋም ጥያቄ በመያዝ ወደ ምርጫ ቦርድ የሄደው የቅንጅት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከአዲስ አበባ 750፤ እንዲሆም ከአራቱ ክልሎች (ኦሮሚያ፤ ደቡብ፤ ትግራይና አማራ) እንዲሁ 750 በአጠቃላይ 1500 መስራች አባላትን ለማቅረብ ዝግጁ ሆኖ እየተጠባበቀ ይገኛል፡፡

የቅንጅት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው ቢሮ ከማግኘት ጋር በተያያዘ እየደረሰበት ያለውን ጫና ለመቀነስ ይረዳል በማለትም የመከራያ ዋጋውን መጠን በእጥፍ በማሳደግ (እስከ አስር ሺህ ብር) በማፈላለግ ላይ ይገኛል፡፡

እነ አቶ አባይነህ በመኢአድ ሰርተፍኬት እየተንቀሳቀሱ ነው

የቅንጅት ከፍተና አመራሮችን አግደናል በማለት ከህገ ደንብ ውጭ የሆኑ አፍራሽ እንቅስቃሴዎችን ሲያካሂዱ የቆዩት እነ አቶ አባይነህ የመኢአድን ሰርተፍኬት በማደስ በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለዜና አገልግሎቱ ገለጹ፡፡ ስራ አስፈጻሚው መታገድ ዋንኛ አላማም ይህ ምስጢራዊ አጀንዳ እንደነበር ታውቋል፡፡

የሚቀርቧቸው ሰዎች እርምጃው አደገኛ አይሆንም ወይ በማለት ጠይቀዋቸው አሁንም እየሰራን ያለነው የቅንጅቱን ስራ ነው፤ ይሁንና በህጋዊ መንገድ ገንዘብ ለማንቀሳቀስና ህገ-ወጥ ናችሁ የሚለውን ክስ ለመከላከል ነው የሚል ምላሽ በአቶ አባይነህ ተሰጥቷል፡፡

ራሳቸውን ህጋዊ ካባ አልብሰው ለመንቀሳቀስ የመጀመርያው እንቅፋት የነበረው የታገደው አመራር በመሆኑ በአሁኑ ሰአት ያለምንም ተጽእኖ በመንቀሳቀስ ላይ ይገናሉ፡፡ በገዢው ፓርቲ በኩል አንዳችም እንቅፋት እንዳይገጥማቸውና ለሁለት ተከፍለው እስከተጓዙ እንዲቆራቆሱ በሚል በወያኔ ካድሬዎች ጉዳዩ በቸልታ እንዲታይ መደረጉን ሁኔታው አመልክቷል፡፡

የአንዳርጋቸው ጽጌ ጽሁፍ በከፍተኛ ቅጅ እየተሰራጨ ነው

የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የላእላይ ም/ቤት አባል በሆኑት በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የተጻፈውና 27 ገጽ ያለው በቅንጅት ዙርያ የሚያጠነጥን ጽሁፍ በድብቅ በከፍተኛ ቅጅ በመሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡

‹‹ያለፈውንና ያለንበትን አይቶ የወደፊቱን አቅዶ መንቀሳቀስ›› በሚል ርእስ ጥር 2000 ዓ.ም. የተጻፈውን ይህን ፖለቲካዊ ጽሁፍ በማባዛት የሚያሰራጩት ወገኖች ማንነት የማይታወቅ ቢሆንም የብዙዎች ምስጢራዊ የመነጋገርያ ርእስ ሆኗል፡፡

በድብቅ እያባዙ እስከ 30 ብር ከሚሸጡት ግለሰቦች ጽሁፉን ያገኙት የዜና አገልግሎቱ ባልደረቦች በትንታኔው አንድም ቦታ ላይ ስለ ትጥቅ ትግል የሚያወሳ እንዳላገኙ የገለጹ ቢሆንም የወያኔ ካድሬዎች ‹‹አንዳርጋቸው የትጥቅ ትግል ጀምረናል ብሎ ጽፏል››የሚል ውዥንብር በመንዛታቸው ብዙዎች ጽሁፉን ለማግኘት እንዲነሳሱ አድርጓቸዋል፡፡

ጸሃፊው በአራት ምእራፎች በመክፈል ሃሳባቸውን ያንጸባረቁ ሲሆን በሳል የፖለቲካ መፍትሄዎችን በማቅረብ አመላካች የትግል ስልቶችን መዘርዘራቸው ተመልክቷል፡፡

በሚያዝያው ምርጫ ወያኔ ኮሮጆ መገልበጥ አያስፈልገውም

ከሁለት ወር በኋላ ለሚደረገው የአከባቢና የማሟያ ምርጫ ወያኔ ካድሬዎች በአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌዎች እስከአምስት የሚደርሱ መታወቂያዎችን በመጠቀም ምርጫውን ሂደት ስለሚያዛቡት ኮሮጆ በመገልበጥ የማጭበርበር ድርጊት መፈጸም እንደማያስፈልጋቸው ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡

ከተለያዩ ክልሎች በመምጣት የአዲስ አበባን መታወቂያ እንዲያገኙ የሚደረጉት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ካድሬዎች ጉዳይ በአንዳንድ የቀበሌ ሃላፊዎች ተቃውሞ ሲገጥማቸው በልዩ ትእዛዝ እንዲያገኙ ስለሚደረግ የምርጫው ውጤት ካሁኑ ታውቋል በማለት ምንጮቻችን ሁኔታውን ይገልጹታል፡፡

ምርጫ ቦርድ ከፍተኛ ህዝባዊ ተሳትፎ ከታየበት ከምርጫ 97 ጋር የሚቀራረብ አሃዝ ያለው ህዝብ መመዝገቡን ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ አስፈላጊ ምርመራዎችን ማድረግ የሚችል አካል ቢኖር ይህን የውንብድና ተግባር ለማጋለጥ ሁኔታዎቹ በግልጽ እንደሚደረስባቸው ጠቁመዋል፡፡