Skip to content

Author: EthiopianReview.com

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስለቀጣዩ ወር ምርጫ እየተወያዩ ነው

በቀጣዩ ወር በመላው አገሪቱ የሚካሄደውን የአከባቢና የማሟያ ምርጫ ከፍተኛ የመብት ጥሰትና ወከባ በመፍጠር የወያኔ ካድሬዎች በነጻ ምርጫ ስም በህዝቡ ላይ ተጨማሪ የጭቆና ዘመን ከመፍጠር ባለፈ ተቃዋሚዎች አንዳችም ወንበር የማያገኙበት በመሆኑ ከምርጫው ለመውጣት ጥምረታዊ ውይይት በማካሄድ ላይ መሆናቸውን ማንነታቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ ታማኝ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡

በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍተኛ አሃዝ ያለው የእጩዎች ስብስብ በግዳጅና በተለያዩ መደለያዎች ያዘጋጀው ወያኔ በቀጣዩ ምርጫ የተወሰኑ መቀመጫዎችን ራሱ ላዘጋጃቸው ተቃዋሚ ተብዬዎች ከመልቀቅ ባለፈ ህዝቡ የሚደግፋቸውን ተቃዋሚዎች የመምረጥ እድሉ ሙሉ ለሙሉ በአደጋ ስለተከበበ በምርጫው መሳተፍ ሳይጀመር መጨረሻው የታወቀውን ምርጫ ህጋዊ ካባ ማላበስ ነው ሲሉ ፓርቲያቸውን በመወከል በጉዳዩ ዙርያ ከሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በመወያየት ላይ ያሉት ምንጫችን እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡ ህዝቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርግ ለምን ይፋዊ መግለጫ አትሰጡም በማለት ከዜና አገልግሎቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱም ያንን ማድረጋችን አይቀርም ሆኖም በአሁኑ ሰአት መግለጫውን መስጠቱ በእጩዎች ላይ እንግልት የሚፈጥር ከመሆኑም በላይ ውይይቱ ስላልተቋጨ የተወሰኑ ጊዜያት ያስፈልጋሉ በሚል እምነት መሆኑን አስታውሰዋል፡፡

በትግል ውስጥ ረዥም ዘመን በማሳለፍ የሚታወቁት እኒህ የፖለቲካ ሰው ጨምረው እንደገለጹት አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለአላማው ያሳዩት አዎንታዊ ምላሽ ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ ይህ ዴሞክራሲያዊ መብትን የመጠቀም እርምጃ ከዴሞክራሲ ጋር እስከወዲያኛው የተጣሉትን ወያኔዎችን አስቆጥቶ ወደ ሃይል እርምጃ ሊከታቸው ወይም በምርጫ 97 እንደሆነው ‹‹የአመጽ አማራጭ›› ተብሎ መስዋእትነት ሊያስከፍል ቢችልም አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መንፈሳዊ ዝግጅት ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

ውሳኔው ይፋ በሚደረግበት ወቅት ሊደርሱ የሚችሉ የመብት ጥሰቶችን አስመልክቶ በአገር ውስጥ ያሉም ሆኑ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከጎናቸው በመቆም የተለመደ ድጋፋቸውን እንደሚያሳዩዋቸው ያላቸውን እምነትም ገልጸዋል፡፡

አንድነት ፓርቲ ሁለት ከፍተኛ ስብሰባዎችን አካሄደ

በተቀዳሚ ፕሬዝዳንት ወ/ሪት ብርቱካን የሚመራው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በዛሬው እለት ጠዋትና ከሰአት በኋላ ሁለት የተለያዩ ውጤታማ ስብሰባዎችን አካሄደ፡፡

የመጀመርያውና እስከ እኩለ ቀን የቆየው ስብሰባ በወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳና በዶ/ር ኃይሉ አርአያ የተመራ ሲሆን የቀድሞ የቅንጅት ታዋቂና ብቃት ያላቸው አባላትን ያሰባሰበ ነበር፡፡ በዚህ 42 የአስተባባሪነት ብቃት ያላቸውን የቀድሞ አባላት ባሰባሰበ የውይይት መድረክ ላይ በርካታ ሃሳቦች ተነስተው የተንሸራሸሩ ሲሆን በቀጣዩ የትግል ሂደት ላይ መከናወን ያለባቸው አበይት ጉዳዮች ተነስተው ገንቢ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡

አባላቱ ቀደም ባሉት ቀናት በአቶ አባይነህ የሚመራውን ስብስብ በማነጋገር ወደ ትግሉ ለመመለስ ጊዜው እንዳልመሸበት ቢያሳስቡም ቡድኑ በአፍራሽ እንቅስቃሴው እንደቀጠለበት በስብሰባው ላይ ተጠቁሟል፡፡ በመጨረሻም ለትግሉ ፍሬያማነት ከምንጊዜውም በበለጠ መስራት እንዳለባቸው በመወሰን የመስራች አባላት ፊርማ የማሰባሰቡን ሂደት በሃላፊነት እንደሚረከቡ አረጋግጠዋል፡፡

ከሰአት በኋላ በተካሄደው ስብሰባ ላይ ደግሞ በ1997 ቅንጅትን በመወከል የአዲስ አበባ የቅንጅት የክልል ም/ቤት ተመራጮች የነበሩ አባላት በፓርቲው ጽ/ቤት ባደረጉት ስብሰባ ቀጣዩን የትግል ስልት አስመልክቶ የመከሩ ሲሆን ፓርቲው የሚጠናከርባቸውንና ከህዝቡ ጋር የሚኖረው ግንኙነት ከምንጊዜውም በበለጠ እንዲሻሻል ለማድረግ በየተመረጡባቸው ክ/ከተሞች ሰፊ ስራ እንደሚሰሩ በመስማማት ተጠናቋል፡፡ በስብሰባው ላይ ዶ/ር ኃይሉ የተገኙ ሲሆን በአጠቃላይ 25 ተመራጮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

Research on the eating habits between men and women

By Ivy Revereza

When it comes to what we eat, men and women really are different according to scientific research presented today at the 2008 International Conference on Emerging Infectious Diseases in Atlanta.

In general, men are more likely to report eating meat and poultry items and women are more likely to report eating fruits and vegetables.

The findings come from the most recent population survey of the Foodborne Disease Active Surveillance Network (FoodNet). From May 2006 to April 2007 over 14,000 American adults participated in an extensive survey outlining their eating habits, including high risk foods for foodborne illness.

‘There was such a variety of data we thought it would be interesting to see whether there were any gender differences. To our knowledge, there have been studies in the literature on gender differences in eating habits, but nothing this extensive,’ said Beletshachew Shiferaw, a lead researcher on the study.

Shiferaw and her colleagues found that men were significantly more likely to eat meat and poultry products especially duck, veal, and ham.

They were also more likely to eat certain shellfish such as shrimp and oysters.

Women, on the other hand were more likely to eat vegetables, especially carrots and tomatoes. As for fruits, they were more likely to eat strawberries, blueberries, raspberries and apples.

Women also preferred dry foods, such as almonds and walnuts, and were more likely to consume eggs and yogurt when compared with men.

There were some exceptions to the general trend. Men were significantly more likely to consume asparagus and brussels sprouts than women while women were more likely to consume fresh hamburgers (as opposed to frozen, which the men preferred).

The researchers also looked at reported behavior in regards to consumption of 6 risky foods: undercooked hamburger, runny or undercooked eggs, raw oysters, unpasteurized milk, cheese made from unpasteurized milk and alfalfa sprouts.

Men were significantly more likely to eat undercooked hamburger and runny eggs while women were more likely to eat alfalfa sprouts.

This information is important to public health officials because better understanding of gender differences in eating habits can help them create more targeted strategies for prevention.

‘The reason we looked at consumption and risky behaviors was to see if there was a statistically significant difference between men and women and if there is this information could be used by health educators to target interventions,’ said Shiferaw.

Source: American Society for Microbiology

The International Conference on Emerging Infectious Diseases is organized by the Centers for Disease Control and Prevention (CDC), the American Society for Microbiology, the Council of State and Territorial Epidemiologists, the Association of Public Health Laboratories and the World Health Organization. More information on the meeting can be found online at www.iceid.org.

የወያኔ እጩዎች ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል እያሉ ነው

በቀጣዩ ሚያዝያ ለሚካሄደው የአከባቢና የማሟያ ምርጫ ያለፈቃዳቸው በወያኔ መልማዮች ለምርጫው የታጩ ዜጎች ህገ መንግስታዊ መብትን በመጠቀም ሽፋን ያለፍላጎታቸው በመመዝገብ መብታቸው እየተጣሰ መሆኑን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ፡፡

በሰሜን ሸዋ ዞን ኦሮሚያ ክልል አሌልቱ ወረዳ ኦህዴድን በመወከል ከቀረቡት 300 የቀበሌ ም/ቤት እጩዎች ሁለት ሶስተኛ ያህሉ ኮታ እንዲሞላ ብቻ ያለፈቃዳቸው የተመዘገቡ መሆናቸውን ለዜና አገልግሎቱ ቀረቤታ ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል፡፡ ቁጥራቸው 80 የሚሆን የግዳጅ እቹዎች በትናንትናው እለት የሚቀዋ ከተማ የምርጫ ጽ/ቤት ጉዳዩን እንዲመረምረው በሚል ፊርማ አሰባስበው በወኪሎቻቸው በኩል አቤቱታ ለማቅረብ ቢሞክሩም ወኪሎቹ ማስፈራርያ የደረሰባቸው ሲሆን ‹‹የቅንጅት አሽከሮች›› የሚል ዘለፋ እንደደረሰባቸው ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡

ምርጫው ከመካሄዱ አስቀድሞ ወያኔ በአዲስ አበባ የመከላከያ ሚኒስትሩን አቶ ኩማ ደመቅሳን ለከንቲባነት እንዲሁም ሌሎች ሹማምንቱን በተመሳሳይ ሃላፊነት ላይ ለማስቀመጥ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ የአደባባ ምስጢር መሆኑ ይታወቃል፡፡

የምርጫ ቦርድ ጨዋታ ዛሬም ቀጥሏል

የቀድሞው ቅንጅት አመራሮች አዲስ የፓርቲ ስያሜ በመያዝ የመስራች አባላት ማሰባሰቢያ ፈቃድ ለማኘት ለዛሬ የተቀጠሩ ቢሆንም የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ሰራተኞች ጉዳዩ የሚወሰነው የቦርድ አባላት ተሰብስበው በሚያሳልፉት ውሳኔ ብቻ ነው የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው ተወክለው የሄዱት የአንድነት ፓርቲ ሃላፊዎች ለዜና አገልግሎቱ ገለጹ፡፡

በህጉ መሰረት የፓርቲ ፈቃድ ለመጠየቅ ምርጫ ቦርድ መሄድ የሚያስፈልገው የ1500 መስራች አባላት ፊርማ ከተሰባሰበ፤ ጠቅላላ ጉባኤ ከተጠራ፤ አመራር ከተመረጠና የፓርቲው ፕሮገራምና መተዳደርያ ተያይዞ ለቦርዱ ከቀረበ በኋላ ቢሆንም ፈጽሞ ከህግና ስርአት ውጭ ነገሮች እየተካሄዱ ይገኛሉ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የቅንጅትን ስያሜ በፍርድ ቤት እናስመልሳለን የሚለው የአቶ አባይነህ ቡድን አጠቃላይ ጉባኤ ለመጥራት የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል፡፡

ምርጫ ቦርድ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችን በሰበቦች ማመላለስ ጀመረ

በወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የቀድሞው የቅንጅት አመራር ‹አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ› በሚል አዲስ ስያሜ ፓርቲ ለማቋቋም ከምርጫ ቦርድ ህግ ውጭ በቅድሚያ ስያሜውን እንዲያቀርብ በተጠየቀው መሰረት ከትናንት በስቲያ ማመልከቻውን ቢያቀርብም እስከዛሬ ባሉት ቀናት ‹በደብዳቤው ላይ የሚፈርም ሰው የለም› በሚል ሰበብ የመስራች አባላት ፊርማ ማሰባሰቢያ ፈቃዱን ሊሰጣቸው እንዳልቻለ ምንጮቻችን ጠቆሙ፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ አመራሮች ፈቃዱን በአስቸኳይ በማግኘት በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በመጓዝ አባላት የማደራጀትና መስራች አባላትን የማሰባሰብ እቅድ ቢኖራቸውም ብዙዎች እንደገመቱት ምርጫ ቦርድ አሳማኝ ባልሆኑ ምክንያቶች ሂደቱን ማራዘም መጀመሩ ሁኔታውን አሳሳቢ አድርጎታል፡፡ ደብዳቤውን ለማግኘት አመራሩ ለነገ መቀጠሩንም ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡