Skip to content

Author: Elias Kifle

Testimony of a former Woyanne on abuse of U.S. aid to Ethiopia

The following is a testimonial letter from Amare Mammo — a former cadre of the ruling TPLF/EPRDF regime — who used to work for the Ethiopian Agricultural and Food Organization.

Letter addressed to: Dr. Seid Hassan – Murray State University
Received: November 23, 2009.

ከውጭ በርዳታ የሚገኘው በሙስና የተዘፈቀው ድጎማ (Safety Net) በኢትዮጵያ ምን ይምስላል?

ጤና ይስጥልኝ ዶ/ር ስይድ።

ኢትዮጵያን እያሽመደመደ የሚገኘውን ሙስና በሚመለከት ትኩረት ሰጥተው በመያዘዎ አመሰግናለሁ። በድጎማ መልክ ለገበሬው የሚሰጠውን ገንዘብ በሚመለከት ግንዛቤ እንዲኖረዎትና፤ መረጃ እንዲሆንዎት የግሌን ለማበርከት/ለመወጣት ይህችን ደብድዳቤ ጽፌአለሁ። ስለ እኔ ትንሽ ለማለት ያህል፤ ወደ አሜርካ ከመጣሁ ይኸውና ሁለተኛ አመቴ ነው። በግብርና እና የምግብ ድርጅት የገበሬዎች የእርሻ አማከሪ ሆኘ በተለያዩ የደቡብ ኢትዮጵያ ወረዳዎች ሠርቻለሁ።

ከላይ በተገለፀው አርዕስት ያለውን ሁኔታ ከመግለፄ በፊት፤ ከ1997 ዓ/ም ምርጫ በኋል፤ የገጠሩ ሕዝብ ኢሕአደግን የመረጠው ለማስመስልና ከተሜውን ለማሸበር ይነገሩ በነበሩት ግጥሞች መካክል ልጀምር፤

መራቡን ይራበው – የከተማ ሕዝብ፤
የዋህ ገጠሬ ሕዝብ – ይብላ ይደልብ።
ንብ ትነድፋለች አለ – የከተማ ሰው?
በልቶ ይመርቃል – ድሀ ገበሬው።

እንደሚታወቀው በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር የኢትዮጵያ ገበሬ በርሀብ ተጠቅቶ እንዳይሞት ከውጭ አገር በሚደርግ ድጎማ ሳያሰልስ “እየተረዳ” ነው። ይህ ድጎማ በእንግሊዝኛው ሴፍቲ ኔት (Safety Net) የሚባለው ተቋም ነው። ፕሮጀክቱ በአብዛኛው የሚመራውም በመንግሥት ካድሬዎች ሲሆን የድርጅታዊ አወቃቀሩና አከፋፈሉም እንደዚህ ነው።

ሀ) ሴፍቲ ኔት (Safety Net) ከ7 ተኩል እስከ 14 ሚሊዮን የሚሆነውን የገጠር ሕዝብን ያቀፈ ፕሮግራም (ተቋም) ነው። ፕሮግራሙ ከ1997 እስከ 2002 ዓ/ም ለአምስት ዓመት የሚቆይ ነው። [ለአንባቢያን ማሳወቂያ፡ – የዚህ ድጎማ ለጋሾች በአብዛኛው የዓለም ባንክና የአሜሪካ መንግሥት ሲሆኑ፤ በቅርቡ የዓለም ባንክ ያደርግ የነበረውን ድጎማ አሁን እንደገና አዲሷል። በድጎማው 292 ወረዳዎች እነደሚረዱም ገልጿል።] ድጎማው የሚያተኩርባቸው አካባቢዎች ድርቅ ያጠቃቸው ቢሆኑም በየክፍለ ግዛቱ ለሚጋኙት ሁሉ ነው። ለዚህ ድጎማ ተጠቃሚ የሚሆነውን አርሶ አደር የመመልመያ መለኪያዎች እነዚህ ናቸው፤

1. ብዙ ልጅች ያለው ቤተሰብ፤
2. ኑሮው ዝቅተኛ የሆነ -ድህነት ያጠቃው – ለምሳሌ ክብቶችና የቤት እንስሳት የሌለው፤
3. ቤቱ የተቃጠለበት፤
4. አባት ወይም እናት የሌላቸው ልጆች፤
5. በእድሜ የገፉ አዣውንቶች፤
6. አካለ-ስንኩላን የሆኑና መሥራት የማይችሉ።

ለ) በድጎማው ተጠቃሚ ከሚሆነው አርሶ አደር የሚጠበቅበት ሥራ፤ አንድ የድጎማ (ሴፍቲ ኔት) ተጠቃሚ አርሶ አደር በወር ስድስት (6) ቀን ፤ በቀን 8 ሰዓት በራሱ ስም መሥራት አለበት። ባለቤቱም እንደዚሁ 6 ቀናት በቀን 8 ሰዓት መሥራት አለባት። እሷ መሥራት ካልቻለች፤ ባሏ በወር 12 ቀናት መሥራት አለበት።

ሐ) የሥራው ዓይነት፤ አብዛኛው ሰው የሚሠራው ለመኪና መሄጃ የሚሆን የመንገድ ሥራ ነው። የሚሠራ መንገድ ከሌለ የድርጅት ጽሕፈት ቤትን መሥራት፤ ይህ ካልሆነ ለአርሶ አደሩ መሰብሰቢያ የሚሆን የፖለቲካ ድርጅት ጽ/ቤትን በመሥራት በተለይም የዉሃ ማቆር ጉድጓድን በመቆፈር ይከናወናል።

መ) የአከፋፈል ዘዴ- ፓኬጅ ይባላል። በሰው (ነፍስወከፍ) 30 ብር፤ ለምሳሌ አንድ አባዎራ 5 ቤተሰብ ካለው 150 ብር በወር ይከፈለዋል። ክፍያው ለአንድ ዙር ለ6 ወራት ይቆያል።

ሌላው ደግሞ፤ የመጀመሪያው ፓኬጅ ተብሎ የሚጠራው 1,600 ብር ለአንድ አርሶ አደር በሁልት ዓመት የሚመለስ ተብሎ በብድር የሚሰጠው ነው። ነገር ግን ይህንን ብድር የሚያገኙት ገበሬዎች ሁሉም ሳይሆኑ ለሌላው አርዓያ ይሆናሉ ተብለው የተመረጡት ናቸው። የዚህ ብድር ተጠቃሚዎች አብዛኞቹ እርዳታው የማያስፈልጋቸው ከሌላው ገበሬ ጋር ሲወዳደሩ “ሀብታም” ናቸው ሊባሉ የሚበቁ ናቸው። በሁለተኛው ፓኬጅ 4,000 (አራት ሽህ) ብር ይሰጣል — ከላይ እንደተጠቀሰው በብድር ነክ ሆኖ አርዓያ ይሆናሉ ተብለው ለተመረጡት ነው የሚሰጠው።

ለዚህ ገንዝብ አከፋፈል እንደ መመሪያ ሆኖ የሚያገለግል ተጠርዞ የሚታደል “መጽሀፍም” አለ። እንግዲህ ከላይ እንደተገለጸው፤ ለአንድ ሰው የሚሰጠው ክፍያ በቤተሰብ ልክ ስለሆነ፤ አንድ አባወራ በፕሮጀክቱ የሚሰጠውን ብር ለማበርከት በርከት ያሉ ልጆችን እንዲያፈራ ይጋብዘዋል ማለት ነው። ልጅ የሌለውም አንዳንድ ጊዜ ብሩን ለማግኘት ሲል ከጎርቤት ልጅ ይዋሳል/ያሳድጋል። እርዳታው የሚሰጠው “ከብት ለሌለው” ነው ስለሚልም፤ አንዳንድ ገበሬዎች እርዳታውን ለማግኘት ከብቶቻቸውን ይሸጣሉ። ቤቶቻቸውን አቃጥለውም ተጠቃሚ የሆኑም አልጠፉ።

ለሚሠራው የመንገድ፤ የዉሀ ማቆር፤ የፓርቲና የገበሬ ጽ/ቤት ሥራ አስተባባሪዎቹና አዛዦቹ ካድሬዎች ናቸው። እነዚህም ካድሬዎች በተለይ የግብርናን ሥራ አስመልክቶ ችሎታ የሌላቸው ስለሆኑ፤ ይጥቀምም ይጉዳ እነሱ ከመሰላቸው ገበሬውን በማዘዝ ማስቆፈር ነው። ገንዘቡ የግድ ለገበሬው እየተሰጠ ነው መባል ስላለበትም ገበሬዎች መቆፈር አለባቸው። በሀላፊነት የተሾሙት ከሚያስቆፍሩትም አንዱ የውሀ ማቆር (ጉድጓድ) ስለሆነ የሚቆፈሩት ጉድጓዶች እንዳው ይብዙ እንጂ ዉሀ የማይቆጥሩ ናቸው። እንዳውም “መሠራት አለበት” ተብሎ የሚቆፈሩት የውሃ ማቆሪያዎች ከመብዛታቸውም በላይ ስለማይታጠሩ ባልታጠሩት ጉድጓዶች ውስጥ ከብቶች እየገቡ በመሠበራቸውና በመሞታቸው የተነሳ ገብሬዎቹ በጣም ይማረራሉ። ገበሬውችም “ጉዷዶቹ ይደፈኑልን” ብለው ለካድሬዎቹ ጥያቄዎች ሲያቀርቡ በአብነት እኔ እመሰክራለሁ።

ለውሀ ማቆር መገንቢያ ተብሎ አንድ ጊዜ እኔ በነበርኩበት ቦታ በ8 የአይሱዙ (Isuzu) መኪናዎች 250 ኩንታል ሲሚንቶ ተልኮ ነበር። ሲሚንቶውን ፈርሞ የተረከበውም እንደኔ የግብርና ባለሙያ የተባለው እኔ የማውቀው ግለሰብ ነበር። ነገር ግን ተከምሮ የነበረው አብዛኛው ሲሚንቶ የካብኔ አባላት ቤቶችን ማደሻና ማስጨረሻ ነው የሆነው። [ካብኔ ማለት በኢሕአደግ (በየወረዳው) የሚሾም ሥራ አስፈጻሚ ሰው ነው።] አብዛኛውን ሲሚንቶ የግብርና ባለሙያው ለካድሬዎቹ (ለካብኔ አባላቱ) በርካሽ ሸጠላቸው። የቀረው ለሙከራ ተብሎ ወደ የውሀ ማቆር ቦታ ተወስዶ ተከምሮ ለብዙ ጊዜ ስለቆየ ደርቆ ተበላሸ። በአጠቃላይ ሲታይ፤ በሀላፊነት ሲሚንቶውን የተረከበውም ሆነ የካብኔ አባላት ተጠቃሚ ስልሆኑ “ለጥፋቱ ተጠያቂ ማነው?” ብሎ የሚጠይቅ ማንም የለም ማለት ነው።

ከላይ እንደገለጽኩት አንዱና ዋናው ሥራ በየቀበሌው የሚገነባው የፖለቲካ ጽሕፈት ቤት ነው። ገበሬውን በነዚህ መሰብሰቢያ ቤቶች እያጎርን እንጨቀጭቀዋለን። እኛ ወደ ገጠር የተላክነው ዋናው ሥራችን ይህ ነው። እንዳውም አንድ ጊዜ አንዱ ፀሀፊያችን ይህንን አስመለክቶ በቀልድ አስመስሎ እውነቱን ለመናገር ሲነግረን “ኢትዮጵያ ሥብሰባ ማድረግን ስለምትችልበት ይህን ችሎታችንን አሽገን (“ስብሰባን ፓክ” አድርገን) ለውጭ ገበያ ብናቀርብ ብዙ ትርፋማ እንሆናለን እና ይታሰብበት” ብሎ ተናገረና በጣም አሳቀን።

በሴፍቲ ኔት ተጠቃሚ የሆኑትም የኢሕአደግ አባላት እንዲሆኑ በምርጫም ጊዜ ለዚሁ ፓርቲ ድጋፋቸውን እንዲሰጡ (እንዲመርጡ) ይጠየቃሉ፤ ይነገራቸዋል፤ ማስጠንቀቂያም ይሰጣቸዋል። ባይጠየቁም እራሱ ጥቅሙ ይገዛቸዋል ብየ አስባለሁ። ይህንንም በከፊል ተገንዝቤአለሁ። ድጎማውን አስመልክቶ ዋና ተጠቃሚና የከበሩ የካብኔ አባላት ለገበሬው ድጎማውን ሰጥተው እያባበሉም ገና የምርጫ ጊዜው ሳይደርስ እነሱንና የእነሱን ፓርቲ ተዎካዮች እንዲመርጥም ያዋክቡታል። እነሱን ከመምረጥ ሌላ ምርጫ የለውም፤ በቃ!

ሌላው መረሳት የሌለበት ደግም እንደኔ ላሉት ወደ ገጠር ለሚላኩት “ሙያተኞች” የሚሰጠው የቀን አበል (per dime) ነው። የዚህ አበል እኔም ተጠቃሚ ነበርኩ። ይህንን በሚመለከት እስቲ አንድ ጊዜ የሆነውን ላጫውተዎ። አንድ ጊዜ ለሥራ ወደ ገጠር ተላክን። የተላክነው ለሁለት ቀናት ብቻ ነበር። ነገር ግን ተጽፎ የወሰድነው አበል ለ10 ቀናት ሆኖ አገኘነው። ከ5 ቀናት በኋላም (የመጀመሪያውን ሳንጨርስ) ወደ ሌላ ቀበሌ ለተመሳሳይ ሥራ የ12 ቀናት አበል ተፃፈልን። እንደገናም ወደ ሌላ ቀበሌ ተልከን የ8 ቀን አበል ወሰድን። በአጠቃላይ ሣንሠራ ሠርታችኋል፤ ባልሄድንበት ቦታ ሄዳችኋል ተብለን የ30 ቀናት አበለ ወሰድን ማለት ነው። በጋምቤላ አካባቢ አንድ የካብኔ አባል በአንድ ዓመት ውስጥ የ458 የቀን አበል፤ ሁለተኛው ደግሞ የ378 የቀን አበል በመውሰዳቸው ሁለቱም ከሥራ እንደተባረሩ አውቃለሁ። እንደዚህ አይኑን ያፈጠጠ የሙስና ተግባር ላይ በግልጽ የተሠማሩትና የታወቀባቸው “ሙያተኞች” “ከሥራቸው ተባረዋል” ቢባልም ነገር ግን አብዛኞቹ ቅጣት ሳይሆን ወደ ሌላ ወረዳ እንዲዛወሩ ነው የሚደረገው።

ረ) ሌሎችንም ልጨምርልዎ፤

1. አንዳንድ ገበሬዎች ምርጥ የዘር በጎች፤ የወተት ላሞች፤ የመሳሰሉትን ተገዝተው ይሰጣቸዋል። እነዚህን የቤት እንሥሳዎች ገበሬው ፈርሞ ሲወስድ ከተገዙበት በላይ ተጨምሮበት ነው። አንዳንድ ጊዜ ገበሬው የተገዙበትን ዋጋ ቢያውቅም አፉን ሸብቦ ከመቀበል ሌላ አማራጭ የለውም። ካጉረመረመ ሊያገኛቸው የሚችላቸውን እንሰሳዎች ከናካቴው ማጣት ስለሚሆንበት።

2. ሌላው ደግሞ ለድጎማው (ሴፍቲ ኔት) ተብሎ የተመደበውንና የሚላከውን ገንዘብ አስከትሎ ለፕሮጀክቶች (የፕሮግራሞች መጠቀሚያ) ተብሎ የሚከፍለው/የሚፈሰው የገንዝብ መባከን ነው። ይህን ለማስረዳት አንድ ምሳሌ ልጠቀማም፤ አንድ ጊዜ በርከት ያሉ ለገበሬዎች የሚሰጡ ምርጥ የዘር በጎች ተገዝተው ወደተፈለገበት ቦታ ጭኖ ለመውሰድ አንድ የግል የጭነት መኪና (Isuzu) ተከራየን። መክፈል የሚገባን የገበያ ዋጋ 1,800 (አንድ ሺህ ስምንት መቶ) ብር መሆን ሲገባው፤ ለነጋዴው 6,000 (ስድስት ሺህ) ብር ተሰጠው። ታዲያ ይህን ያህል ገንዘብ የተከፈለው የመኪና ነጋዴ በተዘዋዋሪ ለአለቆቻችን ያካፍል ይሆን፤ ወይስ ገንዘቡ የግል ስላልሆነ ነው እንደዚያ የሚረጨው? ድርጊቱ ሁለቱም ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ሁለቱም ጥፋት ነው። የመጀመሪያው ሙስናውና ከሱም ጋር ተያይዘው የሚመጡት የፖለቲካ፤ የኤኮኖሚና የባሕል የተወሳሰቡ አባዜዎች ሲሆኑ፤ ሁለተኛው ድርጊት በተናጠል ሲታይ ደግሞ ሀገሪቱን ወጥሮ ለያዛት ግሽበት ችግር አባባሽ ነው። ይህንን ጉድ በአርባ ምንጭ ዞን በኮምባ ወረዳ ከታዘብኩ በኋላ ወደ ሌላ ቦታ ለተመሳሳይ ሥራ ተዘዋወርኩ። ቦታው ወደ አዋሳ ቀረብ ያለ፤ በሲዳማ ዞን ቦርቻ ወረዳ ይባላል። እዚህም ሆኘ እያየሁት ያለው ተመሳሳይ ጉድ ነው። በተጨማሪም፤ በዚህ አካባቢ አንድ ጊዜ የአህያና የፈረስ ጋሪዎች ከአዋሳ ከተማ ተሠርተውና ተገዝተው ለገበሬዎች እንዲሰጡ የሚያደርግና በተግባር ላይ የዋለ ፕሮጀክት ነበር። ነገር ግን ገበሬው እነዚህን ጋሪዎች ሲረከብ፤ ከተገዙበት ዋጋ ከ400 እስከ 500 ብር ድረስ ተጨምሮበት ነው። 500 ጋሪዎች ተገዝተው ሲታደሉ በዓይኔ አይቻለሁ። ይህንን ፕሮጀክት የቀረፀውም፤ በሥራ ላይ ያዋለውም ገንዘብ ያዡ ነው። ገበሬው ጋሪ ባያስፈልገውም፤ ወይም የጋሪው ብዛት ጥቅሙን ዋጋ-ቢስ ቢያደርገውም፤ የከብኔ አባላት ችግራቸው አይደለም። ለገበሬው ችግር አዋቂውች እነሱ ብቻ ስለሆኑ የገብሬው ሃሳብ ወይም ፍላጎት ከቁጥር አይገቡም። ቁም ነገሩ ግን በዚህ የጋሪ ማደል ፕሮጀክት ቢያንስ ወደ 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ) ብር ለግል ጥቅም ስለሚሰበሰብ፤ በዚህ አንድ ፕሮጀክት ብቻ 16 የሚሆኑት ተባባሪ የካብኔ አባላት መካፈላቸው ነው። ከሥር ያሉት ደግሞ የሚካሄድውን ሙስና እንዳያጋልጡ ከ20 እስክ 30 የሚሆን የቀን አበል ይጻፍላቸውና አፋቸው ይሸበባል። በነገራችን ላይ እኔ የአንድ አምስት የካብኔ አባላት መኖሪያ ቤቶችን ጎብኝቸ ነበር። የቤቶቻቸው ውበት ምን ልበለዎ! አንዳንዶቹም እስከ አምስት ቤት ድረስ እንዳላቸውም ተገንዝቤአለሁ። ብዙና ትርፍ ቤቶች አላችሁ እንዳይባሉም ትርፍ ቤቶቻቸውን በልጆቻቸው ስም እንዲመዘገቡ ያደርጋሉ።

3. በሄድኩበት ወረዳ ሁሉ በግብርናው ጽ/ቤት ሆነው የሚሠሩት አብዛኞቹ (ሁሉም ማለት ይቻላል) የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት አስተማሪዎች ከሌሎቹ የሥራ ባለድረቦቻቸው ጋር ሲመጣጠኑም ብቃት ያነሳቸው፤ ይህንኑም ችሎታ/ብቃት ማነስ የተገነዘቡ፤ ነገር ግን በጋለ ምጣድ ላይ ሆኖ እንደሚቆላ ነገር ምላሳቸው የሚንጣጣ አፈኞች ናቸው። አንዳቸውም የግብርና ሙያ የላቸውም። እኔ እንደሚመስለኝ፤ አሁን ለተፈጠረው የእህል ዋጋ መናር እንደነዚህ ያሉት በደሎች ሁሉ ተጨማምረው ነው። ፖለቲካውም እንደዚህ አላግባብ በሆነ መልክ በከበሩ ጥቂት ነቀርሳዎች ተወጥሮ ነው የተያዘው።

4. የገጠሩን ጉዳይ በዚህ ላይ ላቁምና በከተማው፤ በተለይ በአዲስ አበባ እያጋጠመን ያለውን ችግር በጥቂቱ ላካፍለዎ። እኔ እኖርበት በነበረው አካባቢ በሳምንት እስከ 5 ቀናት ድረስ መብራት ይቋረጣል። እንዳው ችግሩን ዘርዝሮ መግለጽ ስለማይቻል፤ እስቲ አንዳንዱን ልበል። በርካታ የቤተሰብ አባላት ያሏቸው ሰዎች ሥጋ ገዝተው ቤተሰቦቻቸውን በአንድ ሙሉ ኪሎ ሥጋ መመገብ ስለማይችሉ አንዱን ኪሎ ሥጋ ለ3 ሲቃረጡ ይታያል። ሁለት ጊዜ በልቶ ማደር ብርቅ እየሆነብን ነው ብለው የነገሩኝ ብዙ ናቸው። አንድ ጊዜ ብቻ በልቶ የሚያድረውን የሕብረተሰብ ክፍል ፈጣሪ ይወቀው። የጤፍ እንጀራን በዓመት አንድ ጊዜ እንኳ ያልቀመሰ ሰው እየበረከተ መምጣቱንም ተግንዝቤአለሁ። ከጥቂት አመታት በፊት አንድ “ደረቅ እንጀራ ይሸጣል?” ተብሎ ይጠየቅ የነበረው አሁን ያ ቋንቋ ተለውጦ “ደረቅ ምሳ ይሸጣል?” በሚል ተቀይሯል። ወጥ ከተጨመረበት ከአቅም በላይ ሰለሚሆን! በአንፃሩ ግን፤ ቡና ቤት ገብተው ውስኪያቸውን የሚያንቆረቁሩ፤ ምግብ ቤት ገብተው ጮማቸውን የሚቆርጡም አሉ። እንደነዚህ ያሉትን ጥጋበኞች የትካሻ/ጫንቃ ማበጥ የተመለከተ ሰው፤ የተራቡትን 5 ሰዎች ሊሸከም ይችላል ብሎ ማሰብ ይችላል።

እንግዲህ ሕዝባችን እንደዚህ ባለ የርሀብ ቸነፈር እየተቆላ ነው “ጀግናው መሪያችን” ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ አይናቸውን ፍጥጥ እያደረጉ “ኢኮኖሚአችን በ 11.8% አድጓል” ብለው ሲናገሩ በሰሙትም ሆነ ባልሰሙት ጉዳይ ላይ ሁለት እጃቸውን በጣም ከፍ አድርገው አውጥተው (ማጨብጨባቸው እንዲታወቅላቸም ይሆናል) የፓርላማ አባላት ሲያጨበጭቡላቸው፤ አቶ መለስ መነጽራቸውን ከፊታቸው ወረድ-ቀና፤ በእጃቸው ከፍ-ዝቅ እያደረጉ በጋለ መልክ ሲናገሩ ይታያሉ። ይህ እየሆነ እያለ፤ በአንፃሩ ደግሞ በርሀብ የተቆላው ሕዝብ አንጀቱ እርር ይላል! በነገራችን ላይ የ97ቱን ምርጫ አስገድፎ የተመረጡት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትም የጭብጨባው ውድድር ተካፋይ ስለሆኑ በጭብጨባው ያላቸው ፉክክርና ትብብር አሳፋሪ እንዳይሆን ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል ተብሎ በሰፊው ይነገራል። ማስጠንቀቂያውም፤ “ማጨብጨባችሁን ቀጥሉበት ነገር ግን እንደበፊቱ ሳይሆን ትንሽ የሚባለውንም እያዳመጣችሁ አድርጉት” ተብለዋል ነው የሚባለው።

እንግዲህ በአዲስ አበባ (እኔ እዚያ እንደነበርኩም ሆነ አሁን) በከተማው ሕዝብ የሚባለውን፤ ከእርሰዎ ሙያ ጋር የሚስማማውን ትንሽ ብየ ልጨረስ። ኢኮኖሚያቸውን በ11.8% ያሳደጉት የ”ጀግናው መሪያችን” መለስ ዘናዊ እውቅና በጣም እየናረና እየገነነ መጥቷል። በዚህም የተነሳ ተፈላጊነታቸው በዝቶ “ጀግናው መሪያችን” ግን የሚያናግሯቸውን ሰዎች ለመምረጥ ተገደዋል። የኢትዮጵያን ኤኮኖሚ 11.8% ያሳደጉት፤ ይህንንም በድፍረትና በመደጋገም የተናገሩትን “ጀግና” ለማናገር ተሠልፈው ከየሚገኙት መካከልም፤ የሀገራቸው ኤኮኖሚ ያሽቆለቆለው፤ የምዕራብ አገሮች ታላላቅ መሪዎች — አቶ ኦባንም ጨምሮ እንዲሚገኝ እየተነገረ ነው ያለው። እነዚህም የታላላቅ አገሮች መሪዎች እንደዚህ የደቀቀውን ኤኮኖሚያቸውን ለማቅናት ደፋ-ቀና እያሉ ከሚኳትኑ፤ እልቁንስ በ12% የሀገሩን ኢኮኖሚ እያሳደገ ያለውን “ጀግናውን የኢትዮጵያ” መሪ ጥቂት ደቂቃዎች ባልሞላ ጊዜ አማከረው መፍትሄ ቢያገኙ አይሻላቸውም? ይባልና፤ እንዳውም አንዳንዶቹ፤ ታወቅን የሚሉ የኤኮኖሚ ጠበብቶችም፤ የኤኮኖሚ እድገት ትምህርታቸውን ከልሰው እውቀታቸውን ለማዳበር “ከጀግናውና ከታላቁ የኢኮኖሚ ምሁር” ከአቶ መለስ ለመውሰድ ቦታው ሳይሞላ ተራቸውን ቢይዙ/ቢመዘገቡ ይሻላቸዋል! ብለው በድፍረት የሚናገሩም አልጠፉ።

አዎ፤ ይገባኛል! “የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ቀመሩ ተዥሞልሙሎ የተሠራው በነ አቶ መለስ መኝታ ቤት ስለሆነ የእነዚህ የታላላቅ አገሮች መሪዎች ሕዝብ ይህንን ሲያውቅ እንደሚቆጣባቸው፤ ከሥልጣን አሽቀንጥሮም እንደሚጥላቸው የአዲስ አበባ ሕዝብ እንዴት ይህንን ማሰታዎስ አቃተው?” ብለው ይጠይቁኝ ይሆናል። ቁጣን ካነሱማ፤ ከኛስ ሕዝብ ምን ቀርቶ። በወያኔ ካድሬ እየተገረፈ፤ እየተቃጠለ ያለ የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ አንድ ቀን መገንፈሉ ይቀራል ብለው አያስቡም? በአገራችን አነጋገር፤ “ቡና እንኳ እሳት ላይ ብዙ ከቆየ መገንፈሉ አይቀርም” ይባል የለ?! ፈጣሪ ይርዳን።

በሌላ ርዕስ በሌላ ጊዜ እስከምንገናኝ እስከዚያው ቸር ይገጠመን።

አማረ ማሞ።

* * * * * * * * *

አንባቢ ሆይ፤

ከሚደርሱኝ ደብዳቤዎች መካከል ይቺ የአቶ አማረ ማሞ ደብዳቤ በገጠሩ አንሠራፍቶ ያለውን የፖለቲካና የኢኮኖሚ እውነታ ያንፀባረቀች ስለሆነች አቶ አማረ በፋክስ የላከልኝን በእጅ የተጻፈ የስምንት ገጽ ደብደቤ እንደገና በኮምፑተር ጽፌ (ታይፕ አድርጌ) ለማካፈል ወስንኩ። የዚህ ፀሀፊ ደብዳቤ ወደ ገጠሩ ወሰድ አድርጎን፤ እየሆነ ያለውን ለሌሎቻችን ከማቅረቡም በላይ ለምሳሌ “ድጎማ” ተብሎ የሚሠጠው “እርዳታ” ምን እንደሚመስልና የሚያደርሰውን የለማኝነትና የጥገኝነት ስሜት አባዜ፤ አሁን የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች እንደሚነግሩንም፤ “ድጎማው” የፖለቲካ መጠቀሚያ መሆኑን፤ በገለማው ሙስና የከበሩና እየከበሩ ያሉ ግለስቦች እንዳሉ፤ በሕዝብ ሕይዎት የሚጫወት የአውሬነት/አረመኔነት ጠባይ ያለው የሕበረተሰብ ክፍል (ክላስ) እንደተፈጠረ፤ ለ”ድጎማ” ተብሎ የሚሰጠው ገንዘብ ለግሽበቱ አንዱ ምክንያት እንደሆነ፤ ወ.ዘ.ተ. ያሳያል።

ምስጋና ለአቶ አማረ ማሞና ኢትዮጵያን ወጥሮ እያብጠለጠላት ስላለው ሙስና መረጃን ለምትልኩልኝ ሁሉ!

(I can be reached at [email protected] or [email protected])

Environmental destruction in Ethiopia (video)

For the next few days the eye of the world will be focused on the City of Copenhagen, Denmark. Leaders from 192 counties will gather to discuss how to protect the earth’s climate from heating up. African leaders thieves and murderers have appointed one of their own, Meles Zenawi, to represent them at the Conference. The minute he was named to represent African despots, Meles has started to accuse developed countries of producing climate-warming pollutions and demanded billions of dollars in compensation. Transferring blame is second nature to Ethiopia’s genocidal tyrant. In 2005, after he ordered his death squads to gun down pro-democracy protesters, he blamed the massacre on the opposition party leaders and put them in jail. The following 2-part film shows the environmental disaster that is being caused by Meles Zenawi’s regime at one of Ethiopia’s many lakes. It is a must watch documentary for all the participants of the Copenhagen Climate Conference.
Part 1 (see Part 2 below)

Part 2

Over 1,000 Ethiopians entered Yemen in November

Yemen’s Ministry of Interior said today that 1,048 Ethiopians have illegally entered the country by smuggling boats last November. Many of the refugees are women and children.

The Ethiopians were fleeing from the U.S.- and World Bank-financed brutal dictatorship in Ethiopia.

The regime in Ethiopia, led by Meles Zenawi, is currently waging a genocidal war in Ethiopia’s Ogaden region where entire villages are being burned down.

Interior ministry voiced its concerns about the escalating flow of refugees from Ethiopia, ordering the security authorities in coastal provinces to close of inlets the Ethiopians used to enter the country.

Ethiopia’s tyrant faces opposition in Copenhagen (video)

Opposition grows against the participation of Ethiopia’s brutal tyrant Meles Zenawi at the Copenhagen Climate Conference this month. Some are suggesting that his place should be rerouted to The Hague for trial at the International Criminal Court.

Freelance journalist Doug McGill, a former New York Times reporter, argues that Meles Zenawi should not be allowed to represent Africa at the United Nations Climate Change Conference (COP15). Also interviewed in the video below: Ethiopian immigrant Magn Nyang, PhD, who speaks of the genocide in his native Anuak region of Ethiopia in 2003.

Filmed at the Humphrey Institute for Public Affairs, University of Minnesota, 4 December 2009 by Chuck Olsen for The UpTake: theuptake.org.

Tsegaye Kebede lives up to expectations in Japan

By Brett Larner | Japan Running News

Tsegaye Kebede Fukuoka Japan 06dec2009Beijing Olympics and Berlin World Championships double bronze medalist, defending champion and Japanese all-comers record holder Tsegaye Kebede of Ethiopia lived up to expectations and more with a history-making 2:05:18 win at the 2009 Fukuoka International Marathon. Kebede’s time was a PB by two seconds and a new course and new Japanese all-comers record, no doubt pleasing race organizers and his accountant by keeping Fukuoka among the world’s very best courses. Most significantly, though, Kebede’s performance was the 10th of the year to break 2:06, the first time the top ten fastest times of the year have cleared this former barrier. Coming in the last first-rate marathon of the year worldwide, it seals 2009 as the start of a new era in men’s marathoning.

Kebede breaks the sound barrier. Click photo for more great pictures, detailed splits and more from race broadcaster TV Asahi’s Fukuoka website.

Japanese ace Yu Mitsuya (Team Toyota Kyushu), acting as pacemaker, took the pack through 5 km right on 3:00/km pace. Shortly afterwards fellow pacemakers Samson Ramadhani (Tanzania) and John Kales (Kenya) picked things up to 2:57, leading away a pack of six: Kebede, Ethiopians Tekeste Kebede and Dereje Tesfaye, 2005 Fukuoka winner Dmytro Baranovskyy (Ukraine), 2008 Chicago Marathon winner Evans Cheruiyot (Kenya) and Japan-resident marathon debutant Mekubo Mogusu (Team Aidem). Mitsuya held on at a credible 3:00 pace leading a pack of five: Japanese runners Tomoyuki Sato (Team Asahi Kasei) and Yuki Kawauchi (Saitama T&F Assoc.), Russian Oleg Kulkov, Korean Kyo-Jick Lee, and Kenyan first-timer Joseph Gitau (Team JFE Steel).

After a moderate 1:03:05 first half, exactly on pace to match his 2:06:10 course and Japanese all-comers record from last year’s Fukuoka, Tsegaye Kebede broke away with a slowly building surge from 27 km. To the disappointment of Japanese fans, the popular Mogusu was the first to falter, dropping back at 26 km and eventually out at 31 km. Cheruiyot and Baranovskyy were the next to lose touch, leaving the three Ethiopians up front. In the second pack things strung out after halfway, Lee dropping out at 25 km and Gitau and talented amateur Kawauchi losing contact. As the only elite Japanese runner in the field, stalwart 2:09 man Sato pressed ahead on track for a sizeable PB.

After 30 km only his training partner Dereje Tesfaye could keep up with Tsegaye Kebede’s continuous acceleration, pacing him through 32 km before losing touch. You could almost see the checklist going through his mind as Kebede ran on over the final 10 km: “First 2:05 in Japan, check. PB, check. 2:04: question mark.” In the end the PB was as far as he went, and barely. He had to run the final lap of the track in 66 seconds to get there, but he made it. In his post-race interview Kebede was elated, animated and charismatic, pointing first to the clock and then to himself as he posed for pictures.

Tesfaye faded to 4th but ran a solid PB of 2:08:36. Overtaking him were Tekeste Kebede, creating no end of headaches for broadcasters by running a 2-minute PB of 2:07:52 for 2nd (A Kebede 1-2 finish!), and 2005 winner Baranovskyy, who ecstatically beat his Fukuoka-winning time with his 2nd-best-ever mark of 2:08:19. Cheruiyot came in slow for 5th in an unremarkable 2:09:46, failing again to capitalize on the promise of his 2:06:25 in the heat of the 2008 Chicago Marathon.

In the second pack things got ugly. Sato did his best to live up to the pressure of being the top Japanese man in the field but couldn’t sustain the strain of his 1:03:35 first half, staggering in to an agonizing 2:23:59 31st-place finish back among the amateurs. The little-known Tadashi Shitamori (Team Yasukawa Denki) came up through the pack after a modest 1:04:52 first half to take the top Japanese spot, 9th overall in 2:14:42. Whether he is selected for next year’s Asian Games national team on such a performance remains to be seen. Takayuki Ota (Team Fujitsu) was the 2nd Japanese runner, 11th in 2:15:23.

More notable, perhaps, were the 3rd and 4th Japanese runners, amateurs Kawauchi, 13th in 2:17:33, and Nobuaki Takata (Hirakata Masters AC), 14th in 2:19:00. Kawauchi was clearly in trouble at 25 km after a screaming (for an amateur) 1:03:44 first half just 31 seconds off his half-marathon PB, but gutted out a 45 second PB in his third marathon of the year. Takata, aka the Tokyo Marathon Man in the Wig, ran with seriousness and focus through a 1:08:10 first half en route to a 31 second PB. 60+ world record holder Yoshihisa Hosaka (Natural Foods), dealing with seasonal asthma, banged out a 1:15:48 first half before struggling in to a 2:40:39.

Sitting on the sidelines, Mogusu was a sad figure. An undeniably talented runner with his own drive and motivations, Mogusu seemed to lack the fire that made him so popular as a Hakone Ekiden star. His predecessor at Yamanashi Gakuin University, Ombeche Mokamba (Kenya), went on to train solo at the non-ekiden-oriented Team Aidem but never acheived any marathon results worthy of his name. Mogusu’s throroughly lackluster debut raises the depressing spectre that he may follow Mokamba down the same road.

2009 Fukuoka International Marathon – Top Finishers
click here for complete results in English
1. Tsegaye Kebede (Ethiopia) – 2:05:18 – PB, CR, Japanese all-comers record
2. Tekeste Kebede (Ethiopia) – 2:07:52 – PB
3. Dmytro Baranovskyy (Ukraine) – 2:08:19
4. Dereje Tesfaye (Ethiopia) – 2:08:36 – PB
5. Evans Cheruiyot (Kenya) – 2:09:46
6. Luis Feiteira (Portugal) – 2:13:07
7. Oleg Kulkov (Russia) – 2:13:49
8. Harun Njoroge (Team Komori Corp.) – 2:14:17 – debut
9. Tadashi Shitamori (Team Yasukawa Denki) – 2:14:42
10. Vitaliy Shafar (Ukraine) – 2:15:07
11. Takayuki Ota (Team Fujitsu) – 2:15:23 – PB
12. Thomas Payn (U.K.) – 2:17:29
13. Yuki Kawauchi (Saitama T&F Assoc.) – 2:17:33 – PB
14. Nobuaki Takata (Hirakata Masters AC) – 2:19:00 – PB

Ethiopian soccer great Italo Vassalo speaks out

Italo Vassalo is one of the most beloved Ethiopians of this century, on a par with Tilahun Gessesse, Abebe Bikila and others. From Emperor HaileSelassie on down, every Ethiopian loved him and his elder brother Lucciano, the captain of Ethiopia’s National Team in 1960s. Italo helped win Ethiopia’s first African Cup in 1962 by scoring against then powerful Egyptian team.

In 1991, the anti-Ethiopia tribal junta led by Meles Zenawi came to power. A few years later, using its war with Eritrea as an excuse, the junta stripped off Italo Vassalo’s citizenship and kicked him out of Ethiopia, along with tens of thousands of other Ethiopians of Eritrean origin.

In the interview below, Italo expresses his affection for the people of Ethiopia and Emperor HaileSelassie, while indicting Meles Zenawi’s regime for committing a campaign of ethnic cleansing, which is a crime against humanity, against Eritrean-Ethiopians.