Skip to content

Transitional government in exile is the way to go

Here is another well-presented argument in support of an Ethiopian Transitional Government in Exile.

Source: Ethiopian Current Affairs Discussion Forum

Click here for PDF version

ትንቢተ ኤልያስ፡ የስደት መንግስት የኛም ፍካሬ ነው

የሚሳፈር ይሳፈር፡ የማይሳፈር ይቅር፡ ቀኑ ሲደርስ ግን ሁሉም ይሳፈራል

አገሬ መግባት አፈልጋለሁ!!

“አገሬ መግባት እፈልጋለሁ!! እኔ ሌላ ምንም ዓላማ የለኝም። ወያኔ አትገባም ብሎ ከሶኛል። ወያኔ ከተሰቀለበት የትእቢትና እብሪት ሰቀላ ተፈጥፍጦ ወርዶ ማየትና በአገሬ በነጻነት መኖር እፈልጋለሁ።” አለኝ ኤልያስ ክፍሌ፡ ከኤርትራ መልስ አንዳንድ ነገሮችን ስናወጋ። ይኸው ነው ይሄንን ልጅ እንቅልፍ አሳጥቶ ሰላም ነስቶ ከዲሲ አስመራ፡ ከዚህ እዚያ የሚያንከራትተው። ኤልያስ፡ አንዳንድ ግዜ ያበሳጭ ይሆናል። “ኤልያስ፡ ተው ሰው አትንካ፡ የትጥቅ ትግልን ለማራመድ የግድ ብርቱካንን ማውገዝ የለብንም። የለም ሰላማዊ ትግል አያዋጣም፡ የቀረን ትጥቅ ትግል ብቻ ነው ብለህ መከራከር ትችላለህ። ያንተን ክርክር አሳማኝ ለማድረግ ግን እነ ብርቱካን ሚደቅሳን መዘልዘል፡ እነ ዶ/ር ሀይሉን ማዋረድ የለብንም። እነ ዶ/ር መራራን ማበሻቀጥ አያስፈልገንም። እንደዚያ አይነቱ ነገር ትክክል ስላልሆነ ብቻ ሳይሆን፡ ይንን ባደረግክ ቁጥር ፍጥጫው በኛና በኢህአዴግ መሀከል መሆኑ ይቀርና፡ የትጥቅ ትግል በሚያራምዱ ወገኖችና በሰላማዊ ትግሉ አራማጆች፡ በተለይም ደግሞ በአንድነት ደጋፊዎች መካከል ይሆናል። ተው ሰው አትንካ።

የኢህአዴግ ስራ ይበቃል፡ የሕወሐት ጥፋት

ሰዉን የትጥቅ ትግልን እንዲቀበል፡ ኢህአዴግ የሚሰራው ስራ በቂ ነው። ኢህአዴግ የሰላማዊውን ትግል ምህዳር እያጠበበ እያጠበበ፡ ሲመጣ፡ በአራት ዓመት ውስጥ አንድ ሰላማዊ ሰልፍ ሲከለከል፡ በአራት አመት ውስጥ ሁለት ሕዝባዊ ስብሰባ ሲነፈግ፡ በአምስት ዓመት ውስጥ፡ አንድ የቴሌቪዥም ማስታወቂያ ማሰማት ሳይቻል ሲቀር፡ የሰማኒያ ዓመት አዛውንት ያለፍርድ ሲታሰሩ፡ የአስራሰባት ዓመት ወጣቶች በግንባራቸው ተመትተው ሲገደሉ፡ በየዓመቱ በረሀብ የሚቀጠፍ ሰው ቁጥር ሲጨምር፡ በየዓመቱ የሚሰደድ ሰው ሲያሻቅብ፡ የአገሪቱ መሬት ለአረብና ሱዳን ሲቸበቸብ፡ የአንድ ብሄር ልጆች እንደ እንቧይ እስኪያብጡ ሲፈነጨብንና ሲወቅጡን፡ ይሄ ሁሉ ሕዝቡን ወደለየለትና ወደባሰበት የትጥቅ ትግል ያመጣል። ከኢህአዴግ በኩል የሚሰራው ስራ በቂ ነዉና፡ ከኛ በኩል ሕዝቡን ወይንም ድርጅቶችን የትጥቅ ትግል እንዲመርጡ የሚያስገድድ ማስፈራሪያና ስድብ፡ አታካራና ጭቅጭቅ አያስፈልግም። ኢህአዴግ ያንን ስራ በሚገባ እየሰራ ነው። የኛ ስራ ሌላ ነው።

አብዮተኛው ኤልያስ፡ አብዮታዊ ሀሳቦች

ኤልያስ ዘወትር የሚያነሳቸው ሀሳቦች አብዮታዊ፡ ከዘመናቸው የቀደሙ፡ ደፋርና ሰው ለመግባትና ለማንሳት የሚፈራቸው ናቸው። ለምሳሌ አንድ ግዜ ኤልያስ በሌሊት ተነሳና፡ “የግዞት መንግስት ማቋቋም ያስፈልገናል አለ”። ብዙዎች ተንጫጩ። ይሄ ሰው ምንድነው የሚያወራው? ምነስ ነው የሚናገረው? ብለው ተሳለቁበት። ጥቂቶቻችን ግን አስደነቀን። አስፈነደቀንም። ወዳጄ ተክሌ የሻው፡ ሰሞኑን “ኢትዮጵያ የምትባለው አገር የለችም” የሚል አስደንጋጭ ክርክር አምጥቷል። የክርክሩን ሙሉ ቃል አልሰማሁትም። ግን ኢትዮጵያን ኢህአዴግ አፍርሷታል ነው የሚለው። ወይም ኢትዮጵያ መሆን እንደሚገባትና እንደነበረችው የለችም ነው የሚለው። ያ ለጊዜው ይቅር። ኢትዮጵያ ግን አሁን ትክክለኛና ሕጋዊ መንግስት የላትም። አጼ ሀይለስላሴ፡ በዚያም በዚህም ብለው በመለኮታዊ መቀባት ስልጣኔን አገኘሁ ብለው ለዓመታት ሕዝቡን አሳምነውት ሕዝቡም ጸሀዩ ንጉሳችን እያላቸው ኖሩ። ኢህአዴግ ግን፡ የሽፍታ ጭምብሉንና ኮንጎ ጫማውን በሲቪል ልብስ ለውጦ ስልጣን ላይ ያለ ምንም ህጋዊ መሰረት በጡንቻውና በዓለም አቀፉ መንግስታት ችሮታ ብቻ ስልጣን ላይ የቆየ አገዛዝ ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያን የሚወክል የግዞት መንግስት ለማቋቋም መብቱም ችሎታውም አለን። የኤልያስ ሀሳብ ትክክል ነው።

የግዞት መንግስተ ለምን? ከነማንስ ጋር?

የግዞት መንግስት ብናቋቋም የሚቀበሉን መንግስታት አናጣም። ኤርትራ በተማመን ከጎናችን ነች። ሌሎች ከኢህአዴግ ጋር የተጣሉ መንግስታትም ከጎናችን ናቸው። ኤርትራ ራሷ ልታመጣልን የምትችለው የወዳጅና የአቅም ብዛት የትየለሌ ነው። ብዙ ሰዎች ያለፈውን የጦርነትና የደም መፋሰስ አመታት በማሰብ ኤርትራን እንደ መንጸፈ ደይን ይፈሯታል። ብዙ ሰዎች እንደውም ከሀጢያት ይልቅ ኤርትራን ይፈራሉ። እዚህ ጋር ሲኦል እዚህ ጋር ኤርትራ አለች ቢባሉ፡ ወደሲኦል የሚመርጡም አሉ። ያ ስህተት ነው። ያለፈ አልፏል። ያለፈውን አንለውጠውም። ዘመን ይለወጣል። ከኤርትራ ጋር ለመስራትና ለመወዳጀት የሚያስፈልጉን ነገሮች በጣም ኢምንትና ጥቂት ናቸው። አንደኛ፡ ኤርትራ አገር መሆኗንና በምንም መልኩ የኤርትራን ሉአላዊነት እንደማናሰጋ ቃል መግባት። ቃል መስጠት። ሁለተኛ ኤርትራና ኢትዮጵያ እንደ ጎረቤት አገሮች አንዳቸው ባንዳቸው ላይ ኢኮኖሚያዊ ትስስር ፈጥረው በሰላምና በትብብር እንደሚኖሩ መስማማት። እነሱ ባህር አላቸው። እኛም ምጣኔ ሀብት። እነሱ ጨው አላቸው። እኛም በርበሬ። ሶስተኛ ታላላቅ ሰዎችና ድርጅቶች ግንባር ፈጥረው በቀጥታ ከኤርትራ መንግስት ጋር ልኡካን ልከው መነጋገርና መቀመጫችውን በአስመራ አድርገው የግዞት መንግስት መቋቋም። አለቀ። ለጊዜው ብዙዎች ወይንም የኢትዮጵያ ህዝብ ይሄንን ላይደግፈው ይችላል። ግን ራሱን አህአዴግንና ሻእቢያን ጨምሮ ማንም ሀያል ሕዝብ በደገፈው መንገድ አይደለም ስልጣን ላይ የመጣው ወይም የወጣው። ካሸነፍን ሕዝብ ሁልግዜም ካሸናፊ ወገን ነው። የአጼ ምኒሊክ እርግማንና ግዝት ልጅ ኢያሱን አልጠቀመም፡ የሀይለስላሴ ድል አድራጊነት ግን ስልጣን ላይ አቆያቸው። 50 ዓመታት ግድም። ግማሽ ክፍለዘመን። ስለዚህ የምንፈልገው ማሸነፍ ከሆነና በኤርትራ መጓዙ እንዲሁም የግዞት መንግስት መቋቋሙ ለማሸነፍ ከረዳን ሰዎች ደገፉትም ተቃወሙትም ያንን ለማድረግ ማመንታት የለብንም።

ግንቦት ሰባት፡ ግንቦት ሀያ፡ ግንቦት ሰባት

አሁን የወሬ ግዜ አብቅቷል ብሏል ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ። አሁን የስራ ግዜ ነው። ኢህአዴግ ስራውን ሰርቷል። እየሰራም ነው። ከግንቦት ሀያ በፊትም በኋላም። የቀረው የኛ ክፍል ነው። የኛ ስራ። ኢህአዴግን ለመጣል ግንቦት ሰባት የሚጸየፋቸውና የሚያፍራቸው መንገደች ሊኖሩ አይገባም። ዶ/ር ብርሀኑ ጓደኞቹንና የስራ ባልደረቦቹን ሰብስቦ ወደ አስመራ ቢወርድ፡ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ለሙአመር ጋዳፊ የአደረጉትን ያህል ደማቅ አቀባበል ነው የሚያደርጉለት። ዝርዝሩን መነጋገር ነው። ካለመነጋገር ነው፡ ካለመጠየቅ ደጃዝማችነት ይቀራል። ኢህአዴግ የሰላምና የእፎይታ አገዛዝ መግዛት የለበትም። ሕወሀትም ይሁን ልጆቹ እንቅልፍ አጥተው፡ እንቅልፋቸውን እንግሊዝ እንዲተኙ ማድረግ አለብን። እስካሁን ለንደንና ዲሲ፡ ጀርመንና ሰዊዘርላንድ ሰርተናል። አሁን ደግሞ እዚያው ሜዳ ላይ መውጪያ ግዜ ነው። ከኤርትራ የተሻለ፡ ከኤርትራ የቀረበ፡ ከኤርትራ የተመቸ ሜዳና መንገድ እንደሌለ ደግሞ ከዚህ ቀደም ጽፈናል። ተራው የግንቦት 7 ነው። ከፍተኛ ልኡካን ልኮ ከኤርትራ መንግስት ጋር መነጋገርና ከኤርትራ ጋር መስራት፡ የስደት መንግስት ማቋቋምና ከዓለም መንግስታት ጋር መጻጻፍ ለብቸኝነት የቀረበ መንገድ ነው።

ልጅ ተክሌ ነኝ፡ ግንቦት 2009፡ ካናዳ

8 thoughts on “Transitional government in exile is the way to go

  1. Now I read something fantastic in two-decade long political discourse. The equation of opposition impotency will be resolved by this idea. Long live Eritrea and Long live Ethiopia!! Great initiative! I hope G7 authorities are reading this!

  2. “A transitional government in exile is the way to go” is a good proposal to consider; however, isn’t Ginbot 7, whose president is Dr. Berhanu Nega, also a government in exile? Does it make any difference to create a new government in exile rather than to encourage and support the existing one – Ginbot 7? If Ginbot 7 is not yet embraced by most people in the diaspora and at home, isn’t it time to declare Ginbot 7 as a legitimate government in Exile?

    By the way, do we have any proof that government in exile will work and be able to change the existing Woyanne government in Ethiopia?

    The government of Ethiopia during Emperor Haile Selassie was in exile for five years, and after five years, it was restored to the King by the help of the British people. This remarkable event was accomplished for three factors: (1) while the King was in exile, he was tirelessly working, applying to the world leaders to help him denounce Italy as an aggressor; (2) the world was fighting against Hitler and Mussolini, and Mussolini was regarded by most of the leaders of the world as a fascist and as an adventurer; and (3) most Ethiopian patriots were fighting against Mussolini for five years. These three important factors helped the exiled King to come back and inter Addis Ababa triumphantly.

    The Polish government had been in exile from 1939 to 1990, and finally it was restored when the Soviet Union collapsed; however, the government of Tibet is still in exile, and Dali Lama many never go back to Tibet and restore his government.

    These three governments mentioned above had been tested in their own respective countries, and some of them were able to come back from their exiles and establish their former status; others like the Tibetan government have not been that much lucky.

    At least for some times, Dr. Nega had served his country and many Ethiopians are now familiar with his name and his popularity. To me, Dr. Nega would be the ideal person to run the government in exile.

    Nevertheless, we should have a debate on this issue: Is it essential to create a new government in exile or should we declare Ginbot 7 as a legitimate government in exile? After we have solved this crucial issue, then we should consider the next issue: Should we have to elect a new president for the new government in exile, or should we have to ask Dr. Nega to be the president of the new government in exile?

    We remember that Emperor Amaha Selassie, the son of Emperor Haile Selassie, lived in exile for many years and could not win the hearts of the Ethiopian people, so he died in exile without seeing his country again.

    To be effective, the transitional government in exile must have enough support from the United States government, the European Union, the Eritrean government, and from the other East African states. More than these, it needs thousands of Ethiopian patriots fighting the Woyanne regime from every corner of the country.

    Finally, the transitional government in exile will certainly succeed if it inspires the hearts and minds of the Tigrean army, the common people of Ethiopia, and especially the Ethiopian Orthodox Tewahido Church clergies, monks, deacons, the Ethiopian Jewish Rabies, and the Ethiopian Muslim Imams. Without them, there will be no easy victory at all, so let us convince them and bring them to our side, and “If God is on our side, who is against us?”

  3. It is a way forward. Ginbot 7 first needs to extend its reach to various factions (like ONLF, OLF and others) before the establishing the exile government. It should also show that it has a big support from various groups using large demonstrations of the Diaspora.

Leave a Reply