Skip to content

Woyanne’s desperation – Analysis by Tesfaye GebreAb

Tesfaye GebreAb analyzes the recent developments inside the Woyanne regime in Ethiopia, including the alleged coup plot, desperate measures against Amhara officers in the Woyanne army, Meles Zenawi’s possible retirement next year, who may take his place, etc.

[click here for PDF]
[Source: EMF]

የግንቦት ማስታወሻ

ከተስፋዬ ገብረአብ

እነሆ! ዛሬ ቅዳሜ ነው።

እለቱም ግንቦት 9፣ 2009።

ትናንት ደግሞ ግንቦት 8 ነበር። በአበሻ የዘመን አቆጣጠር ልክ የዛሬ ሃያ አመት ግድም “ጥቂት ጄኔራሎች” ኰሎኔል መንግስቱ ላይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አድርገው ነበር። ሳይሳካላቸው በመክሸፉ ዛሬ በህይወት የሉም። ማንኛውም አጥንት – አስከሬን ሆነዋል። አምላክ የጄኔራሎቹን ነፍስ ይማር። እኒያ ሰዎች ከነሙሉ ችግራቸው ከኰሎኔል መንግስቱ የተሻሉ ዜጎች ነበሩ ብዬ አምናለሁ።

ቀደም ሲል ደግሞ ጄኔራል መንግስቱ ነዋይ ጃንሆይን ለማስወገድ በመሞከራቸው የዚያ ዘመን ወጣት ትውልድ ጃንሆይን መንካትና መድፈር እንደሚቻል ትምህርት ማግኘት መቻሉ ይታመናል። ሰሞኑን ደግሞ ታሪክ ራሱን ለመድገም ሞከረ። የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ርእሰ አጀንዳ ሆኖ ሲያነጋግረን ሰነበተ።

እኔም ታዲያ ምንም ስንኳ የፓለቲካ ተንታኝ ባልሆንም፣ እንደ ጋዜጠኛነቴ በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየቴን በጨረፍታ ለማኖር ፈቅጄያለሁ። ለነገሩ ይቺን “ብጫቂ ወረቀት” የመጫር አሳብ የመጣው ከኔው አልነበረም። በፀጥታ ተቀምጬ፣ “የደራሲው ማስታወሻ” የሚል ስም የሰጠሁትን ቀጣይ መፅሃፌን እየፃፍኩ ሳለ የethioforum.org ዋና አዘጋጅ ክንፉ አሰፋ መስመር ላይ አገኘኝና፣

“የሰሞኑ ግርግር ላይ አስተያየትህን ለምን አትፅፍም?” ሲል ጠየቀኝ።

* * *

የሰሞኑን የመፈንቅለ መንግስት ግርግር ጉዳይ ከማንሳቴ በፊት ግን በዚህ ወቅት የማንም የፖለቲካ ድርጅት አባል አለመሆኔን ከወዲሁ መግለፅ ግዴታ ሆኖ አጊንቸዋለሁ። ቀደም ሲል የወያኔ አባል ለመሆን የበቃሁትም ባልጠበቅሁት ሁኔታ ከተራራ ወደ ሸለቆ እንደ ኳስ እየተጠለዝኩ መሆኑን በ“ጋዜጠኛው ማስታወሻ” አውግቼያችሁዋለሁና እሱን እዚህ አልደግመውም። ይህን ርእሰ ጉዳይ ማንሳት ያስፈለገበት ምክንያትም በቅርቡ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ እየታማሁ በመሆኑ ነው።

በመሰረቱ በግንቦት 7 አባልነት መታማት የሚያኮራ ነው።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ የመግባት ሃሳብ ቢኖረኝ ኖሮ ግንቦት 7 ከአማራጮቼ አንዱ በሆነ ነበር። ቅሬታዬን መግለፅ የፈለግሁትም የአብርሃ በላይ ድረገፅ አትሞት የነበረው አንድ ፅሁፍ ግንቦት 7ን ለማጥቃት ሆን ተብሎ በወያኔ ካድሬዎች የተፃፈ ሊሆን ይችላል ብዬ በመገመቴ ነበር። “የአድአው ጥቁር አፈር” በሚል ርእስ ኢትዮሚዲያ ድረገፅ ላይ የታተመው ፅሁፍ ከኔ በላይ ግንቦት7ን የሚያጠቃ ሆኖ ነበር ያገኘሁት።

በዚያን ሰሞን የፀሃፊውን ማንነት ለማወቅ ብዙ ጥረት አድርጌ ነበር። ፍንጭ የሚሰጠኝ ግን ጠፋ። ‘ያያ አባ ቦር’ በሚል የብእር ስም ግንቦት 7ን ከኔ ጋር ደርቦ በቃላት መድፍ ሲደበድበኝ የከረመው ፀሃፊ ለካስ የሩቅ ወዳጄ ኦቦ በፈቃዱ ሞረዳ ኖሮአል።

በፈቃዱ ሞረዳ በፃፍው መጣጥፍ እኔን ‘ወኔ ቢስ፣ፈሪ!’ ብሎ የቻለውን ያህል በሚያጥላሉ ቃላት ሲገልፅ፣ ራሱን ደግሞ ‘የግንባር ስጋ’ ወይም ‘ጀግና’ ‘እውነተኛ ጋዜጠኛ’ ሲል ገልፆአል። እዚህ ላይ ማንበቤን በማቆም ጥቂት ተክዤ ቆየሁ። በፈቃዱ ስለራሱ ጀግናነት በአደባባይ እስኪናገር ድረስ ርግጠኛ መሆን ከቻለ በውነቱ በጣም እድለኛ ሰው ሆኖ ይሰማኛል። ጀግና መሆን መልካም ነው። ሰዎች በምርጫቸው ፈሪ ሆነው አያውቁም። ለነገሩ የጀግንነትና የፈሪነት መለኪያዎች ከቶ ምን ይሆኑ? ስንት አይነት ጀግንነቶችስ አሉ? እና በፍቃዱ ሞረዳ ራሱን ጀግና ብሎ እኔን ወደ ፈሪዎች ቀበሌ የላከኝ በየትኞቹ መለኪያዎች ይሆን?

በፍቃዱ ከ1981 ጀምሮ እንደሚያውቀኝም ፅፎአል።

እውነቱን ነው።

ግጥሞቹን በጣም ስለምወዳቸው ራሴ ነኝ ፈልጌ የተዋወቅሁት። እኔ ከዚያ በፊት በስነ -ግጥሞቹ አውቀው ነበር። እሱም እንደኔው ሃረር ላይ ያቺኑ የፉገራ ፖለቲካ ተምሮ ነበርና እኛ ስንመረቅ በፍቃዱ የኢሰፓ ጋዜጠኛና ካድሬ ሆኖ መጣ። አዲሳባን እንጂ ጦርነትን አያውቃትም። ሃረር ላይ ግማሽ ሰአት ያህል ስነፅሁፍ ነክ ወሬ ተጨዋውተን ተለያየን። በዚሁ አበቃ። በፍቃዱ ሞረዳ ወደ አዲሳባ፣ እኔ ወደ አሰቃቂው ጦርነት ተለያየን። መልአከ ሞት ደግሞ ሬሳ በዝቶበት ነው መሰለኝ፣

“አንተን ለጊዜው አንፈልግህም” ብሎ ሳይወስደኝ ቀረ።

ደርግ ወድቆ አዲሳባ ስንገባ ከበፈቃዱ ጋር በድጋሚ ተገናኘን። አሁን ደግሞ ሁለታችንም ስደተኞች ነን። ከስደቱ በሁዋላ ወያኔን በጋራ እንታገለዋለን ብዬ ስጠብቅ በፈቃዱ ሞረዳ ፊቱን ወደኔ አዙሮ በባዙቃ ይደበድበኝ ያዘ። አብርሃ በላይም፣ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ የበፈቃዱ ሞረዳን ፅሁፍ ከድረገፁ ነቅሎ ጣለው። እንዳልኳችሁ ግን “የግንቦት 7 አምባሳደር” ሆኜ አስመራ ልጓዝ እንደተዘጋጀሁ የሚገልፀውን የፈጠራ ፅሁፍ የፃፈው በፈቃዱ ሞረዳ ሊሆን ይችላል ብዬ አልገመትኩም ነበር።

ያን ሰሞን ታዲያ ለቀጣዩ መፅሃፌ ከበፈቃዱ ሞረዳ ውብ ግጥሞች፣ “ጀጎል” የተባለችውን ልጠቀምባት በማሰብ፣ “ጀጎል’ የተባለች ግጥምህን ላክልኝ” የሚል ኢሜይል ፃፍኩለት። በጀጎል ፈንታ በኔ ላይ ያለውን ጥላቻ የሚተርከውን ፅሁፍ በፒዲፍ አስሮ ላከልኝ። “የአደአው ጥቁር አፈር” መድፈኛ እሱራሱ እንደሆነም ነገረኝ።

በእውነቱ ወያኔዎች በዚህ ነው የሚበልጡን። የራሳቸውን ሰው በመደብደብ ሃይል አያባክኑም። በፍቃዱ ሞረዳ እኔን በመደብደብ ወያኔን ብቻ ነው ማስደሰት የቻለው። በርግጥ በፍቃዱ ወደ ኦነግ ስለ መግባቱ ያልተረጋገጠ ጭምጭምታ ወሬ ሰምቻለሁ። ወሬው እውነት ከሆነ ለገጣሚው ያያ አባ ቦር መልካም ትግል እመኝለታለሁ…

በዚያን እለት ምሽት ወደ ፕሪቶሪያ ደቡብ ነዳሁ። የከተማችን ደቡባዊ አቅጣጫ ኮረብታማ ነው። ገና ሙሉ በሙሉ አልመሸም ነበር። ባቡሮች የጉልበት ሰራተኞችን እየጫኑ፣ ፕሪቶሪያን እያቋጡ፣ በውበቱ ከቶውንም ተወዳዳሪ ወደሌለው ወደ ኩዋዙሉ ናታል ከፍለሃገር ይከንፋሉ። ኮረብቶቹ በጣም ውብ ሲሆኑ ጃኪቻን የተባለው የፊልም አክተር “…” የተባለውን ፊልም ለመስራት እኒያን ኮረብቶች ተጠቅሞባቸዋል። እዚያ ኮረብታ ላይ ወጣሁና ቁጭ አልሁ። ቁጭ አልኩ ብቻዬን።

በወርቃማው ዘመን ስለ ተፈጠሩት የሩስያ ደራስያን አሰብኩና ቅናት ሰቅዞ ያዘኝ። በአንድ ወቅት ሃያስያን ወደ ቶልስቶይ ቀርበው ስለ ቼኾቭ ጠይቀውት ነበር።

ሳያመነታ እንዲህ መለሰ፣

“ወደድኩም ጠላሁም አንቶን ቼኾቭ እንደሚበልጠኝ አመኜያልሁ!!”

* * *

የሆነው ሆኖ በፈቃዱ ሞረዳ ስለ ግንቦት 7 የገመተውን እንርሳውና እንደ አንድ የስነፅሁፍ ሰው በሰሞኑ አጀንዳ ላይ የግል እይታዬን ላውጋችሁ…..

ከትናንት በስቲያ ግንቦት 7 ነበር እለቱ።

መለስና በረከት የኰሎኔል መንግስቱ ርኩስ መንፈስ ምን ሹክ እንዳላቸው ባይታወቅም፣ እንደ መርዶ ነጋሪ በጠዋት ተነስተው፣ “ግንቦት 7 ወንበራችንን ሊሰርቅ ሲል ለጥቂት ያዝነው!!” ሲሉ በጩኸት ነገሩን።

አያያዘናም በረከት፣

“ለግንቦት 20 ሲያስቡን፣ ግንቦት 7 ላይ አስቀረናቸው” አለን።

በርግጥ በረከት እንደዚህ ሲል አልሰማሁትም። አይልም ግን አይባልም።

እንደዋዛ ከጀመርኩት ወግ ወዲያ ማዶ ታዲያ አያሌ መራራ አጀንዳዎች አሉ። በአስር ሺዎች የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ እስረኞች በየማጎሪያው የከፋውን ስቃይ እየተቀበሉ ይገኛሉ። ቴዲ አፍሮ አንዱ ነው። ብርቱካን ሚደቅሳ – ሁለት። ገመቹ አባቢያ – ሶስት። ገመቹን የሚያውቀው አለ? ምናልባት የምናውቀው ጥቂቶች ሳንሆን አንቀርም። የኦነግ ታጋይ ነበር። ወያኔ አስሮታል። ከናይሮቢ አፍነው ወሰዱትና አሁን የት እንዳለ አይታወቅም።

የስንቱ ስም ተዘርዝሮ ይቻላል?

በርግጥ የሹርሹራ ጓደኛ ስለሆነው ገመቹ በቀጣዩ መፅሃፌ በስፋት አወጋችሁዋለሁ። “ሹርሹራ ደግሞ ማነው?” ትሉ ይሆናል። ለማንኛውም ሹርሹራ በህይወት የለም። የወለጋ ምድር ላይ በክብር አርፎአል። እንግዲህ በየማጎሪያው ከተወረወሩት ወገኖቻችን መካከል እነ ጄኔራል ተፈራ ማሞ የዚህ ማስታወሻ መነሻና ማእከል ናቸውና ወደዚያው ልዝለቅ….

* * *

ወያኔ አብላጫ ቁጥር ባላቸው ብሄሮች መካከል እንዴት አክሮባት እየሰራ መዝለቅ እንዳለበት የቤት ስራውን የሰራው ደርግ ከመውደቁ በፊት እንጂ ትናንት አልነበረም። ቀድሞውንም በተዳከመ የግንኙነት ማእቀፍ ውስጥ የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ጣራው ተደርምሶበት፣ የሚያገናኙት የጋራ የስሜት ክሮች እየተበጣጠሱ አንዱ ለሌላው ጠላት በሚሆኑበት ጎዳና ላይ ሲደነቃቀፍ ዘመናት ባጅተዋል።

ጄኔራል ከማል ገልቹ ከ150 በላይ የታጠቁ የሰራዊት አባላትን አስከትሎ የኤርትራን ድንበር ሲያቋርጥ “የወያኔ ሰራዊት ፍፃሜ ተቃረበ!” ተብሎ ነበር። የጄኔራሉን መኮብለል ተከትሎ በረከት ሰምኦን በሰጠው ቃለምልልስ “ተገላገልን!” ሲል ነበር የገለፀው። ወያኔ ራሱን የሚያጠናክርበት በር ተከፈተለት። ከ20 ሺህ ያላነሱ ኦሮሞ ወታደሮች ከየጦር ክፍሉ ተመንጥረው ትግራይ ውስጥ ታሰሩ። በመቶዎች የሚገመቱ ኦሮሞ መኮንኖች ደግሞ ደሴ አካባቢ ወደሚገኝ ወታደራዊ እስር ቤት ተላኩ። መኮንኖቹን የተረከበቻቸው የእስርቤቱ ሃላፊ፣ ኮሎኔል ብራ የተባለች ነባር የህወሃት አባል ስትሆን፣ የአሉላ ክፍለጦር ኮሚሳር ከነበረችበት ጊዜ አንስቶ በጨካኝነቷ ትታወቃለች። ኮሎኔል ብራ የሃገር መከላከያ ከፍተኛ መኮንኖችን እርቃናቸውን አስቁማ ታስገርፋለች። እንደ ወይራ በጠነከረ የጎማ ዱላ ተደብድበው፣ፓራላይዝድ ሆነው ዛሬም ድረስ ማገገሚያ ጣቢያ የተቆለፈባቸው አንድ ሁለት መኮንኖችን አውቃለሁ።

መኮንኖቹ በግርፊያው ወቅት የተጠየቁት አንድ አጭር ጥያቄ ብቻ ነበር፣

“ከኦሮሞ ጄኔራሎች መካከል ከኦነግ ጋር ግንኙነት ያለው ማነው?”

ድብደባው ሲበዛባችው የአባዱላን ስም ጠሩ።

ኮሎኔል ብራ ወቀጣው እንዲቆም አዘዘችና ያገኘችውን “ምርጥ የምርመራ ውጤት” ለአለቆቿ አቀረበች። አለቆቿ ግን አባዱላ ዝንተአለም እንደማይከዳ ያውቁ ነበር።

ጄኔራል ከማል ሰራዊቱ ውስጥ በህቡእ ካደራጀው የኦነግ ደጋፊዎች መካከል ሲሶውን እንኳ ይዞ አለመውጣቱን ገልዖ ነበር። ይህ ለወያኔ እልል በቅምጤ ሆነለት። በዚያ ሰበብ ምንጠራውን ለማካሄድ በቂ ምክንያት አገኙ። ከጠረጋው በሁዋላ በጎደለ ለመሙላት በተደረገው የስልጣን ሽግሽግ ወያኔ ከአማራ የሰራዊቱ አባላት ድጋፍ ለማግኘት ጥቂት ሞካክሮአል። በዚያን ጊዜ አፍንጫ ሲመታ አይን ሳያለቀስ ቀረ።

ይህን ዘዴ ወያኔ ደጋግሞ ይጠቀምበታል።

ቅንጅት አዲሳባ ላይ በምርጫ ሲያሸንፍ በአንድ አዳር ፊንፊኔ የኦሮሚያ ዋና ከተማ ሆና አደረች። በዚሁ ሰሞንም ኢህአዴግ አዳማ ከተማ ላይ ባዘጋጀው አንድ ግብዣ ላይ የኢህአዴግ አባላት በትግርኛና በኦሮምኛ ብቻ ጨፈሩ። አባዱላም የሚያምነው ታቦት ስላልነበረው በጠመንጃ ስም እየማለ ታሪካዊ ንግግር አደረገ። ግብዣው ላይ የነበሩ እንደሚተርኩት አባዱላ እንባው ባይኑ ቸፈፍ ብሎ፣

“ፊንፊኔ ወደ እናት ክልሏ እንደምትመለስ ህልም ነበረኝ!!” ሲል እንደ ማርቲን ሉተር ኪንግ ድምፁን ቢለቀው ዝቋላና ካካ ተራሮች ደግሞ ያንን በገደል ማሚቷቸው በኩል አገማሸሩት።

አባዱላ እንባውና ህልሙን አጣጥሞ ሳያበቃ መለስ ዜናዊ ጠርቶ፣

“ህልምህን ህፃናት የማይደርሱበት ቦታ አስቀምጠው። ለጊዜው ግን አዳማ ትቆያላችሁ” አለው።

ወያኔ ሁለቱ አብላጫ ቁጥር ያላቸውን ብሄሮች በተመሳሳይ ጊዜ አጥቅቷቸው አያውቅም። አንዱን ሲያጠቃ የሌላው ድጋፍ ስለሚያስፈልገው የፈረቃ ቁማር ይቆምራል። የህወሃት አባላትም ምንጊዜም ፍርድ ሰጪ ዳኛ ሆነው መካከል ላይ ይገኛሉ። የኮሜዲያን ክበበው ገዳ “ገብረመድህን” የተባለው ገፀባህርይ ለዚህ አባባሌ እንደ መልካም ማሳያ ሊጠቀስ የሚችል ነው።

የሰሞኑ፣ “የመፈንቅለ መንግስት ድራማ” ለአየር ከበቃ በሁዋላ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ በቃለመጠይቁ ሲገልፅ እንደነበረው ከጄኔራል ከማል ኩብለላ በሁዋላ በሰራዊቱ ውስጥ በተካሄደው ጠረጋ የአገዛዙ ስርአት ዘረኛ አካሄድ ላይ ጥያቄ ያሳደሩ ምርጥ የሰራዊቱ አባላት በአብዛኛው እየታፈኑ ተሰውረዋል።

ወያኔን እንቅልፍ የሚከለክሉ የሰራዊቱ አባላት አንድ ባንድ እየተመነጠሩ ጥጋቸውን ይዘዋል። ሃይሌ ጥላሁን ሊጠቀሱ ከሚችሉት መካከል ነው። በሰሞኑ “የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ” ጣት ከሾለባቸው መካከልም ሃይሌ ዋናው መሆኑን ውስጥ አዋቂዎች ያወጋሉ። ዳሩ ግን ወያኔ በዚህ ጊዜ በቀጥታ ጄኔራል ሃይሌን ሊነካው እንደማይፈልግ የምናውቅ ከጥቂት በላይ ነን። በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅት ጄኔራል ሃይሌን የተመለከቱ ጥቂት አስገራሚ ወጎች ነበሩ። በዚያን ወቅት የህወሃት ጦር ኮማንደሮች በከባድ መሳሪያ ግዢ ሰበብ በሚሊዮናት ዶላር ኮሚሽን እየበሉ የመሆናቸው ወሬ አየሩን በክሎት ነበር። ጄኔራል ሃይሌ ደግሞ እዚሁ ግዢ አካባቢ የተመደበ ባለስልጣን ነበር። እና ድምፁን ከፍ አድርጎ በስብሰባ ላይ እንዲህ ሲል ተናገረ፣

“እኔ እዚህ ተቀመጬ የሃገሪቱን ገንዘብ አትበሉም! ስትዘርፉ እያየሁ ዝም አልላችሁም!”

ጄኔራል ሃይሌ ከነታምራትና በረከት ጋር ኢህዴንን ከመሰረቱት ነባር ታጋዮች አንዱ ሲሆን፣ አዲስአበባ እስክትያዝም በኢህአዴግ ደረጃ ትግሉን የመራ ሰው ነው። በስብሰባ ላይ የህወሃት ኮማንደሮችን እንዲያ ከተናገረ በሁዋላ ግን የሃይሌ ጉዳይ ያለቀለት ሆነ። “ጡረታ!” አሉና አገለሉት። ጉዳዩ ተራ የእድሜና የአስተዳደር ጉዳይ ቢሆን ኖሮ፣ ሳሞራ የኑስ ቀድሞት ጡረታ ሊወጣ በተገባ ነበር። እነደሰማሁት ጡረታ ከወጣም በሁዋላ ሃይሌ አላረፈም። ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ፣

“እንተዋወቃለን!” እያለ ይናገራል አሉ።

እነ ሳሞራም “የትም አይደርስ” በሚል ችላ ብለውት ሰንብተዋል።

እንግዲህ በዚህ መረጃ ዙሪያ አንዳንድ ፍንጮችን ማሽተት የሚገድ አይሆንም። ዛሬ በመፈንቅለ መንግስት ወይም በሽብርተኛነት ስም ተይዘው የታሰሩት ከፍተኛና ጄኔራል መኮንኖች ከሃይሌ ጥላሁን ጋር ያላቸውን የጠበቀ ግንኙነት ወያኔም ሆነ የቅርብ የብአዴን አባላት አሳምረው ያውቁታል።

የመፈንቅለ መንግስቱን ወሬ እንደሰማሁ የሚፃፉትን ዜናዎችና ዜና ትንታኔዎች ለማንበብ ሞክሬ ነበር። ወያኔ ጉዳዩን ከመፈንቅለ መንግስት ወደ ሽብርተኛነት ሊለውጠው ለምን እንደፈለገ ገልፅ ነበር። “ሽብርተኛነት ክስ ለመመስረት የሚያመች ሲሆን፣ ባንፃሩ “መፈንቅለ መንግስት” የሚለው ግንቦት 7 የተባለውን ድርጅት ዝና ይበልጥ ከፍ ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አሳድሮባቸዋል። “ከሰራዊቱ እየተመነጠሩ ያሉት አማራ መኮንኖች የግንቦት 7 አባላት ናቸው ወይስ አይደሉም?” የሚለው ጥያቄም አከራካሪ አይደለም። ቢሆኑም ብርሃኑና አንዳርጋቸው፣ “አባላቶቻችን ናቸው!” ብለው ይነግሩን ዘንድ አንጠብቅም። ይህ ለታሪክ የሚቆይ ይሆናል። እንደምንሰማው ግን ከግንቦት 7 ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያልመሰረቱ፣ በአላማው ዙሪያ በራስ አነሳሽነት የተደራጁ ወጣቶች የክፍለ ሃገር ከተሞችን እያጥለቀለቁ ይገኛሉ። በየአካባቢው “ወንድም ጋሻ!” የመሆን የአርበኛነት ስሜት ተቀስቅሷል። ብርቱካን ሚደቅሳ እንደገለፀችው፣ አንድ አላማ በህዝብ ተቀባይነት ካገኘ የሚያደራጀውን አካል ሳይጠብቅ እንደ መንፈስ ይሰራጫል። ቀደም ሲል ለቅንጅት አላማዎች ህይወታቸውን የሰጡት አብዛኞቹ ወጣቶች በአባልነት የተመዘገቡ እንዳልነበሩ እናስታውሳለን። የወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ሰለባ የሆነውን ሰፊ ህዝብ እንተወውና በዚህ ቀውጢ ወቅት ተፈራ ዋልዋ ራሱ የግንቦት 7 ደጋፊ ሆኖ ቢገኝ አይደንቀኝም።

ከመነሻው ብአዴኖች ውስጣቸው ጥሩ አለመሆኑን የውስጥ መረጃዎች አሉኝ። ከኢህአዴግ አራት አባል ድርጅቶች መካከል ክፉኛ ሞራሉ ተነክቶ በቀውስ ላይ የሚገኘው ብአዴን ነው።

ኦህዴድን በቀላል ቋንቋ ላስቀምጥላችሁ!

አመራሩ ንፁህ ወያኔ ሲሆን፣ አባላቶቹ ደግሞ በአብዛኛው የስራ እድል ለማግኘት ድርጅቱን የተቀላቀሉ በአመለካከት ወደ ኦነግ የሚቀርቡ ናቸው።

“ደቡብ ህዝቦች” በሚል ስም አባይ ፀሃዬ ያቋቋመው ድርጅት “አለ ይባላል በሳይንስ ግን አልተረጋገጠም” እየተባለ የሚቀለድበት፣ ዶክተር ካሱ ይላላ እንደፈለገ የሚያንገላታው ከሞቱት በላይ ያለ እቁብተኛ ነው።

ወደ ብአዴን ስንመጣ ከፍተኛ አደጋ ውስጥ ወድቀዋል። መለስ ዜናዊ እንደሚለውም ቀዩን የፈንጂ መስመር ረግጠዋል።

አመራሩን በጨረፍታ ላስጎብኛችሁ…

አዲሱ ለገሰ ከጤንነቱ መበላሸት ሁኔታ ጋር ተደማምሮ ስልጣን ላይ መቆየት እንደማይፈልግ ማመልከት የጀመረው ከሚሊኒየሙ ዋዜማ ጀምሮ ነበር። ተፈራ ዋልዋ፣ “የታገልነው ለዚህ አልነበረም!” እና “መምራት አቅቶናል!” የተባሉ ሁለት ነጠላ ዘፈኖችን ውስጥ ውስጡን ማንጎራጎር መጀመሩን በምሰማበት መንገድ ሰምቻለሁ። ህላዌ ዮሴፍ ቀድሞውንም “ከኢህአፓ መንፈስ አልተላቀቁም!” እየተባሉ ከሚታወቁት አንዱ ነበር። ህላዌ “ኢትዮጵያዊነት!” የሚል መንፈሳቸው ጠንካራ ከነበሩ የቀድሞ የኢህአፓ ትንታጎች አንዱ ነበር። የሽግግር መንግስቱ ስራ ከጀመረ በሁዋላ መለስ ዜናዊ፣

“ህላዌ ዮሴፍ ሆይ! አንተ አማራ ብቻ ነበርክ፣ አማራ ብቻ ሆነህም ትኖራለህ!! ስለሌላው አያገባህም!” ብሎት ሲያበቃ አረንጓዴዋን ቀንሶ በቀይና ቢጫ ቀለማት ያማረች ክራቫት አሰረለት። ከኢህዴን ላይ የተቀነሰችው አረንጓዴ ቀለም ሁመራ መሆኗም በሹክሹክታ ተናፈሰ። ጄኔራል ሃይሌ ጥላሁን ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት ለይቶለታል። መኮንኖች ክበብ ብቅ ሲል፣ “እነዚህ የቀን ሌቦች፣ ተጫወቱብን!” ማለቱን ቀጥሎአል።

ከምርጫ 97 አንድ ወር ቀደም ብሎ መኮንኖች ክበብ ላይ በተደረገ አንድ ግብዣ ላይ ስብሃት ነጋ፣

“ነፍጠኛው ወደ ስልጣን ይመጣል ብሎ የሚያልም ካለ የዋህ ነው!” ብሎ ሲናገር ህላዌ ዮሴፍ የሚጠጣው ትን ብሎት ወደ መፀዳጃ ቤት መሄዱ ተሰምቶአል።

ብአዴን ማለት እንግዲህ እነዚሁ ናችው። ያልተጠቀሱ ቢኖሩ ታደሰ ጥንቅሹና በረከት ስምኦን ናችው። ታደሰ ብአዴን ውስጥ የህወሃት ትክል መሆኑ ነው የሚነገርለት። በረከት ያው በረከት ነው። በወያኔ ዘረኛ ፖለቲካ ውስጥ ገብቶ የወገኖቹን የስቃይ ጊዜ ከሚያራዝም፣ አንዴ ጎንደር ሌላ ጊዜ ቡግና ከሚንከራተት፣ “አማራ ነኝ!” እያለ በምድረበዳ ከሚጮህ፣ የጎንደር ልጅነቱን አክብሮ፣ በኢትዮጵያዊነቱ ቢፀና እንዴት ባማረበት?

የሆነው ሆኖ ከመነሻው ብአዴኖች ውስጣቸው ጥሩ አለመሆኑን ገልጫለሁ። ከአባላቶቻቸውና ከህዝቡ የሚመጣውን ግፊት ከቶውንም ሊቋቋሙት ተቸግረዋል። ብአዴኖች በህወሃት ላይ የቆየ ቅሬታ እንዳላቸውም “የጋዜጠኛው ማስታወሻ” ላይ መግለፄ አይዘነጋም። ብርሃኑ ነጋ ጠቁሞት እንዳለፈውም ሰራዊቱ ውስጥ ቁጣ አለ። የሰሞነኛው ግርግር ከግንቦት 7 ባሻገር የብአዴን ውስጣዊ ሁኔታ ላይ እንዳተኩር ያደረገኝም ብአዴን የወያኔን ዘረኛ ፖሊሲ እያስፈፀመ መቀጠል ከማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱ ይበልጥ ግልፅ እየሆነ በመምጣቱ ነው። ከበረከትና ከታደሰ ጥንቅሹ ባሻገር ያሉት የብአዴን የአመራር አባላት የጄኔራል ሃይሌ ጥላሁንን ቁጣ ቢጋሩ አይደንቀኝም።

“የጋዜጠኛው ማስታወሻ” የተባለውን መፅሃፍ በረከትና ተፈራ ዋልዋ እነዳነበቡት ሰምቻለሁ። በረከት ጠረጴዛ እየደበደበ፣ “ውሸታም!! የውሸት ክምር!!” አለ ተባለ። ተፈራ ግን፣ “የሚያውቀውን ፅፎአል” ማለቱን ሰማሁ። እኔን የሳበኝ ሁለቱ የጥንት ጓደኛሞች የሁለት አለም ሰው መሆን የመጀመራቸው ፍንጭ ነው።

ተፈራ አይኑን መግለጥ ጀምሮ ይሆን?

በርግጥም ሚስቱን እስከ ማሰር ሊደፍሩት የበቁበትን ምክንያት እንደ ተራ ስህተት የሚታይ ሊሆን አይችልም። ተፈራና አዲሱ ያሻውን ያህል የስልጣን ጥመኞች ቢሆኑም፣ የመከላከያ አባላቶቻቸውና የቀድሞ የትግል ጓዶቻቸው እንደ አይጥ እየተለቀሙ ወደ ኮሎኔል ብራ ሲላኩ ድርጊቱን በደስታ ሊያስተናገዱት ከቶ አይችሉም። ለዘመናት ውስጥ ውስጡን ሲበላላ የባጀው የብአዴንና የህወሃት ሽኩቻ ካለፉት ጊዜያት በላቀ ደረጃ ወደ ግጭት አምርቶአል።

ህወሃት ብአዴንን ለማዳከም ይህን ጊዜ ለምን እንደመረጠ መረዳትም ከባድ አይደለም።

ምርጫ 2010 እየቀረበ ነው።

የማጭበርበሪያ ሜዳው ከወዲሁ መደልደል እንዳለበት ግልፅ ነው። “ኢትዮጵያዊነት” የሚል ባንዲራ የሚያስቀድሙ ሃይሎችና የትጥቅ ትግል ያወጁ፣ ኦነግ፣አርበኞች፣የኦጋዴን ነፃ አውጪ የመሳሰሉ አማፅያን “የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላቶች!” ተብለው ተፈርጀዋል። ወያኔ “የግንቦት 7” እና “የአንድነት” ፓርቲዎችን ሁለትነት አለማመኑም ግልፅ ነው። በቀጣዩ ምርጫ ወያኔ እንደለመደው ሊያጭበረብርና ጠመንጃ ሊጠቀም ሲሞክር የግንቦት 7 ትንታጎች መብረቅ እንዳያወርዱበት ሰግቶአል። ብአዴን ለግንቦት 7 የመፈልፈያ ጫካ ሊሆን እንደሚችልም ወያኔ ከምርጫ 97 በቂ ትምህርት አጊኝቶአል። እና ግንቦት 7 ወጣት ወታደሮቹን ይዞ የማይቀርለትን ፍልሚያ የሚጋፈጥ ከሆነ በርግጥም ማእከሉ መከላከያ ነው የሚሆን። የሰሞኑ የመፈንቅለ መንግስት ድራማ እንዲህ ሰፊና አሻገሮ የተመለከተ ስለመሆኑ ከቶ ምን ጥያቄ አለውና?

የብአዴን አመራር በበረከት ሰንሰለት ተጠፍሮ የታሰረ ተስፋ የቆረጠ አካል እንደመሆኑ በህወሃት የሚታዘዘውን የጎጥ አስተሳሰብ ተፈፃሚ የማድረግ ብቃቱን አጥቶአል። ይህ ማለት ግን ህወሃት አልቆለታል ማለት አይደለም። “ኢትዮጵያዊነት” የሚል ባንዲራ ያስቀደሙ ሃይሎች ሲበረቱበት አባዱላ ገመዳን ጠርቶ አንድ የቤት ስራ እንደሚሰጠው ከወዲሁ የሚጠበቅ ነው። አሁንም አፍንጫ ሲመታ አይን ካላለቀሰ ወያኔ ሊሳካለት ይችላል።

ወገኖቼ ሆይ!

ምን ቀረ?

ቀሪው ግልፅ ነው….

በቀጣዩ ምርጫ መለስ ዜናዊ ስልጣኑን እንደሚለቅ ነግሮናል። መለስ ቃሉ አይታመንም። አሳ የላሰው ድንጋይ ነው። በአሁኑ ንግግሩ “አሁንስ በቃኝ! እለቅላችሁዋለሁ!!” ማለቱን ግን እኔ በበኩሌ አምኜዋለሁ። መለስ በርግጥም ስልጣኑን ሊለቅ ወስኖአል። አማራጭም የለውም። ሁኔታዎችንና እድሜውን አስለቶ የቤት ስራውን ሰርቶ አብቅቶአል። ሆኖም ብቻውን እንደማይለቅም አስባለሁ። የፖሊት ቢሮ አባላቱን ሁሉ በትልቅ ዘንቢል ሸክፎ ዘወር ይል ዘንድ እንጠብቃለን። ይሁን እነጂ የዚህች ሃገር መከራ እዚህ ላይ ያበቃል ብላችሁ አትጠበቁ። የሚወራው እውነት ከሆነ አስመራ የተማረው ባለመነፅሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም መለስን ተክቶ ኢህአዴግን ሊመራ እጅጌውን ሰብስቦአል። የቅንጅት መሪዎች ከመፈታታቸው ቀደም ብሎ ስዬ አብርሃ ከእስር የተለቀቀበት የስምምነት ምስጢርም ያልተነካ ወሬ ነው። ህወሃት አንድ አስገራሚ ጠባይ አለው። ጥንካሬ ሲሰማው ርስበራስ ይባላሉ። ጠላት ሲበረታባቸው ደግሞ ልዩነታቸውን መሳቢያ ውስጥ አስቀመጠው ባንድ ሰልፍ ለውጊያ ይዘጋጃሉ። የስዬ አብርሃ በድንገት የመፈታትና የተቃዋሚ ንቅናቄ ውስጥ መገኘት የህወሃት ራስን የማዳን ስትራቴጂ አካል ስለመሆኑ የሚጠራጠር ካለም የዋህ ፖለቲከኛ መሆን ይኖርበታል።

ባጭሩ ቀጣዩ የሃይል አሰላለፍ በአንድ ወገን መለስና ቡድኑን የሚተካው ሃይል፣ በሌላ ወገን ደግሞ በስዬና በገብሩ የሚመራው ሃይል ይሆናሉ። ከዚህ ባሻገር ያሉ ሃይሎች እጣ ፈንታ ገብሩና ስዬን መቀላቀል አለያም መጥፋት ይሆናል። ስልጣን ከሁለቱ ሃይሎች እጅ እስካልወጣች ድረስም የህወሃት አላማዎች እንደተጠበቁ ይቆያሉ። ከዚህ ባሻገር መለስ ለግሉ የሚመኛቸው ጥቂት ነገሮች አይጠፉም። የሞ ኢብራሂም ሽልማት ቀዳሚው ይሆናል። ለገንዘቡ ሳይሆን ለክብሩ።

ይህ የወያኔ ሂሳብ ይሳካ ይሆን? ለማንኛውም ትግሉ ቀጥሎአል!…

* * *

እነሆ! ዛሬ ቅዳሜ ነው…

እለቱም ግንቦት 9፣ 2009።

ፕሪቶሪያ ቁጭ ብዬ እኔም ይቺን እጫጭራለሁ። የደቡብ አፍሪቃ ክረምት ከነጓዙ ገብቶአል። ዛሬ ጠዋት ከቤት ስወጣ ቆፈኑና ዝናቡ ፕሪቶሪያ ላይ እንደጉድ እየወረደባት ነበር። ያፍሪቃ መሪዎች አብዛኞቹ ፕሪቶሪያ ገብተዋል። ጃኮብ ዙማ መንበረ ስልጣኑን የሚረከብበት እለት ዛሬ ነው። የኛው አዛውንት ጋሽ ግርማም ገብተዋል። መኖሪያ ቤቴ ከቤተመንግስቱ ብዙም አይርቅ። እንደምንም እየተሹለከለክሁ ወደ ሰኒሳይድ አቅጣጫ ነዳሁ። አብዛኞቹ አበሾች እዚያ ቀበሌ ይኖራሉ። ሰኒሳይድ ውብ ናት። ሰኒፓርክ የተባለ አንድ ትልቅ የገበያ አዳራሽ አለ። እዚያ ገባሁና በረንዳው ላይ ቁጭ አልኩ።

ሰኒሳይድ በደስታ አብዳለች።

የዙሉ ጎሳ አባላት የቆዳ ልብስ ለብሰው ባህላዊ ጭፈራቸውን ያስነኩታል። እኔም ደስ አለኝ። ይህቺን መጣጥፍም መጫጫር ጀመርኩ። ሰጫጭር ቆየሁና ቀና ስል ለካስ አጠገቤ ካለ ጠረጴዛ ላይ አንዲት ነጭ ደቡብ አፍሪቃዊት ብቻዋን ቁጭ ብላለች፣

“ጋዜጠኛ ነህ እንዴ?” ስትል ጠየቀቺኝ።

ለማሳጠር ያህል፣

“ነኝ አዎ!” አልኩ።

“በምርጫው ስራ በዝቶባችሁ ከረመ?”

“እኔ እንኳ ደስተኛ አይደለሁም” አልኳት “….ምንም ስራ የለም። ምርጫው ቢጭበረበርና ግርግር ቢኖር ስራ ይኖረን ነበር..”

ቀልዱ ገብቶአት ሳቀች። እናም፣

“እናንተ ስራ ብታጡ ይሻላል” አለች።

በርግጥም ደቡብ አፍሪቃውያን ዛሬ ተደስተዋል። በጣም ተደስተዋል። ምርጫው በሰላም አለቀ። አልተጭበረበረም። እና ፕሪቶሪያ ደስ ብሎአታል። እንኳን ደስ ያላት።

አዲሳባስ ለዚህ አይነቱ የደስታ እለት የምትበቃው መቼ ይሆን?

(Tesfaye GebreAb can be reached at [email protected])

31 thoughts on “Woyanne’s desperation – Analysis by Tesfaye GebreAb

  1. Good writing.

    Woyane is suffering under two circumstances. The one is desperation, which is 25%, and the other is from a chronic fear.

    Woyane fear the most anything against them coming from Eritrea. For them is clear that the Eritrean side is the main highway they did able to reach Addis, staying there holding power with crimes and being kicked out.

    That is why recently they seem don’t sleep at all thinking Eritrea is serious this time to confront them working with Ethiopians organizing them in the name of one and united Ethiopia for all Ethiopians. The wall, room and door to the woyanes save heaven is located at the Eritrean side of Ethiopia. This is the best, ideal and right place to start with and finish the game against them. Other than that, will be…
    That is why these time the Tribalists and their supporters are crying all over fearing this time Eritrea is serious confronting them from the right spot which is starting from Tigry(their crime sources base).

  2. Wayanees are wetting their pants. I say this becuase they are accusing America and every organisation national and international. heat up the pressure as the leaders about cascade down a deep precipice or gadel.

  3. Wayanees are wetting their pants. they talk too much. Accuse America, natioal and international oragizations. They are on the edge of a deep political precipice, heat up the pressure , let them fly naked down the hill.

  4. first of all i would like to say thank you and keep up the good work that you doing.

    one more thing i would like to say is that the woyane trick is not working any more as they say differnt dog the same trick doesent work more than once so if the tplf bring differnt leader they will never be accepted by the Ethiopian people.

    it is time to say GAME OVER !!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

  5. Tesfaye you are an ethiopian hero!
    I have never seen a realistic and logical anaysis of current ethio politics than this one.
    Good job Tesfaye!!!!!!

  6. Thanks to Tesfaye – It reveals a Woyane conspiracy executed by “Abraha Belay of ETHIOMEDIA” and the Post-Meles Tigre revival through the rehabilitaton Seye Abraha and Gebru Asrat – criminals amidst the diaspora. Tesfaye has unravelled the evil and ugly mind of the Woyanne dictator, Legesse Zenawi.

    Ethiopians must be mindful of those wolves in the sheep clothing – namely Seye, Gebru and Abraha Belay!!!

  7. This is taken from an interview by the lion of Nakfa with a Nigerian journalist. Read.

    Meless has never taken arms let alone lead war.Interesting.

    Asked to comment on a question that there are parties which claim that “the existing situation between Eritrea and Ethiopia has been aggravated due to personal problems between President Isaias and Premier Meles since the days of the armed struggle,” the President indicated that in the days of the armed struggle he did not even know as an individual the person presently in power in Addis Ababa through the joint sacrifice of both the Eritrean and Ethiopian peoples, nor did he see him in the battlefield. “If you had participated together in the battlefield, you become closer to each other; but this person has never taken up arms, let alone lead war,” President Isaias stated.TM
    Top

  8. I wish I could just read the daily strange staff on the Internet. I mean you guy’s delusion, and hype and attitude of “since I am the best Ethiopian, everything I said is true and sacrosanct, but yours is uncounted and nil” when there such creature of a person in the country, you can sense that the country is in big trouble. A mind that is so simple satisfied with nonsense, fantasy, crudity and ignorance. You may say it is utterly insult, but it is very true. Self-assessment, assertiveness and inclusiveness are what a patriot should worry about…
    In my humble opinion, the best Ethiopians are not alive. They all were dead during and before the Italian invasion. Ironically, if there were some survived they also were killed by the dictator afterwards. The rest of the story has been boring till today…I was born during the beginning of Mengistu revolution and I am still listening Mottos….of Meles cadres like you are….what a luck…..what a generation….

    I said this because Mengistu called himself a hero because he killed Ethiopian and you call Meles a hero or intelligent leader because he killed Ethiopian and let Ethiopia be landlocked (what an extra ordinary hero and intellectual you have who traded a country for his fetish power, to reign over the hungry and poor people). Nevertheless, you are entitled for your fantasy, delusion, and hype, but make sure that you do not insult our intelligence, because you do not have that divine right of turning on and off our mind when you want. Just turn off and on yours

    Had someone dared to say something bad about Issayas between 1991 and 1998, he would have been killed from by TPLF, but today you tell us that he is the dangerious guy to Ethiopian survival. If Meles claim to be, Ethiopian so is Issyas. What is the difference? Well, the difference of course is in your mind not in us

    You said “The only reason that there is an Ethiopia is that the US needed it for the Cold War, and recreated it, otherwise it would have disappeared at the end of World War II.”

    Why it takes you all these years to condemn him…I know the answer of you intelligent people…” for the sake of peace …sake of our yearly 12% development…oh…what a curse!!!!!

  9. T, tell us about the lies of weyane during the fabricated border war with Eritrea in 1998. Tell us the deportation of Eritreans in broad day light was perfermed and so on. We need to know more about the hostile nature of weyane twards the neigboring nations and the invasion of Somalia. Please do not hesitate and share us more what you konw.

  10. እኔም ማስታወሻ አለኝ (በፈቃዱ ሞረዳ)

    የጋዜጠኛው ማስታወሻ Yegazetegnaw Mastawesha

    ከበፈቃዱ ሞረዳ

    ቀድሞው የጋዜጣችን ተወዳጅ አምደኛ፤ የዛሬው እንደኔው ስደተኛ ያያ አባቦር፤ ”የጋዜጠኛው ማስታወሻ” በተባለው መጽሐፍ ላይ ባለፈው የ”ናፍቆት ኢትዮጵያ” መጽሔት ዕትም (“የአደአው ጥቁር አፈር” ጋዜጠኛ ወይስ የፓርቲ ካድሬ?”) ባቀረበው ጽሑፍ መነሻነት ወይንም ተንኳሽነት የተጻፈ ማስታወሻ ነው ይኼ ጽሑፍ። ይህ የእኔ ማስታወሻ የተስፋዬ ገብረአብን ማስታወሻ ሥነጽሑፋዊ ወርድና ስፋት የመመርመር ተልዕኮ የለውም። ዕይታው ወዲህ ነው።

    (ያያ አባቦር “የአደአው ጥቁር አፈር ጋዜጠኛ ወይስ የፓርቲ ካድሬ?” በሚል ርዕስ የፃፉትን ከዚህ ጽሑፍ በፊት ለማንበብ ከፈለጉ እዚህ መጫን ይችላሉ!) ”ከየት መጀመር ይሻለኛል? ስለተስፋዬ ልጻፍ ወይስ ስለ ”የጋዜጠኛው (የካድሬው) ማስታወሻ” መጽሐፍ? እንዴትስ ነው የአንድን ፀሐፊ ሥራ (በተለይም መጽሐፍን) ከፀሐፊው ሁሉንተናዊ ስብዕና ነጥሎ በማውጣት ማወደስ ወይንም ማንኳሰስ የሚቻለው?” የሚሉ ጥያቄዎች በውስጤ ከተተራመሱ በኋላ የመጣልኝን እንደወረደ ጻፍኩት። ለጥያቄዎቼ ሁነኛ ምላሽ መስጠቴን ግን እርግጠኛ አይደለሁም። ወትሮውንስ ቢሆን ማነው በሕይወት ዘመኑ በአዕምሮው ውስጥ ለሚተረማመሱ ሕልቆ መሳፍርት የለሽ ጥያቄዎች መልስ ሰጥቶ የጨረሰውና ከዚህ ዓለም በእፎይታ የተሰናበተ?

    ነገር ግን፤ በእኔ ላይ ቢደርስብኝ የማያስደስተኝን ነገር፣ በሌላው ላይ እንዳላደርግ ሁሌም ለሚጎተጉተኝ ኅሊናዬ ታማኝ ለመሆን የሞከርኩ ይመስለኛል።

    ”ክፍሌ ሙላትና በፍቃዱ ሞረዳ የተባሉትን ጋዜጠኞች ግን ክንፈ አጥብቆ ይጠላቸው ነበር ’ደመኛ ጠላቶች’ ይላቸውም ነበር”

    ተስፋዬ ገብረአብ – ”የጋዜጠኛው ማስታወሻ” ገጽ 208
    ከተስፋዬ ገብረአብ ሥራዎች ጋር ለመተዋወቅ ግፊት ያሳደረብኝ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1980 ዓ.ም. (ደርግ ሳይወድቅ በፊት) እሠራበት የነበረው የራዲዮ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ የሲሳይ ታደሰ አድናቆት ነው።

    በሁርሶ የምድር ጦር መኮንኖች ማሠልጠኛ እጩ መኮንኖች ምረቃ ዘገባ ለመሥራት ወደ ሐረር ተልኬ የመሄድ አጋጣሚ ደግሞ ከተስፋዬ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል እንድንተዋወቅ ምክንያት ሆኖኛል። ያኔ ሳገኘው ቀጭንና ፊቱ ጥርስ በጥርስ (ሳቂታ) የሆነ ወጣት መኮንን ነበር።

    ከፊቱ ላይ ያነበብኩት የደስታ ስሜት በመኮንንነት በመመረቁ ወይንም ለተጨማሪ የወታደራዊ ካድሬነት (የፖለቲካ ሠራተኛነት) በመታጨቱ አልመሰለኝም። ይልቁንም የሥልጠናውን ውጣውረድ መገላገሉና ከልጅነቱ ጀምሮ ይመኘው እንደነበረ የነገረንን የጋዜጠኝነት ሙያ በጦር ኃይሎች ብዙኀን መገናኛ (ሚዲያ) ውስጥ የማግኘት ተስፋ ኮርኩሮት ይሆናል።

    በወታደራዊ ሥልጠናው ሂደት ”ደካማና ልፍስፍስ” ከሚባሉት ሠልጣኞች መሀከል ቁጥር አንድ እንደነበረ የሚነገርለት ተስፋዬ፣ በእርግጥም ከምረቃ በኋላ ወደ ጦር ግንባር የመሄድ ሕልም አልነበረውም የሚያሰኙ ምክንያቶች ቢኖሩም እዚያ ውስጥ መግባቱ ለዚህ ማስታወሻ ያለው ፋይዳ እምብዛም ነው።

    በኮርሱ የምረቃ መጽሔት ላይ ገበየሁ ዋለልኝ የተባለ መኮንን (የተስፋዬ የቅርብ ወዳጅ ነው) ”መተላለፍ” በሚል ርዕስ የጻፈው አጭር ልብወለድ በተስፋዬ የቅድመ ካዴት አፍላ የፍቅር ገጠመኝ ላይ የተመረኮዘ እንደነበረ ገበየሁ ነግሮኛል። ጭብጡ የፍቅርና የድህነት (ደሃ የመሆን) ጣጣ ነው።

    ወጣቱ መኮንን ሥልጠናውን (በተለይም የወታደራዊ ካድሬነቱን ሥልጠና) እንደጨረሰ በጦር ኃይሎች ራዲዮ ፕሮግራም ዝግጅት ክፍል ባልደረባነት እንዲመደብ ለአለቆች ሃሳብ ቀርቦ፣ ”ጦር ግንባር ሄዶ ልምድ ይውሰድ” መባሉን ከወቅቱ አለቆቼ ሰምቻለሁ። እናም በወቅቱ ”ሰሜን ምዕራብ ዕዝ” ተብሎ ወደሚጠራው ጦር ግንባር ተላከ። ያኔ እንደሰማነው በጦር ግንባሩ ተመድቦ ሥራ በጀመረ በአሥራ ዘጠነኛ ቀኑ፣ የአንድ ወር ደመወዙን እንኳን ሳይበላ ተማረከ። ስለአመራረኩ እርሱ በመጽሐፉ ላይ የተረከልን እንደተጠበቀ ሆኖ ይባል የነበረው ደግሞ ወዲህ ነው። ይህንኑ በተመለከተ እንደጨዋታ ይኖረናል።

    ተስፋዬ የኢህአዲግ ልሳን የነበረው የእፎይታ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ነበር፤ ”ዋለልኝ ብርሀነ” በሚል የሽፍታ ስም። በመጽሔቱ የመጨረሻ ገጾች ላይ ከየጋዜጣውና ከየመጽሔቱ የተቃረሙ ክብደት ያላቸው አንቀጾች፣ ዓረፍተ ነገሮችና ሐረጎች ይታተሙ ነበር። አንድ ቀን እኔ ከማሳትመው ጋዜጣ፣ አሁን በትክክል የማላስታውሰውን ዓረፍተ ነገር ነቅሶ በመጽሔቱ ላይ ይጽፍና (ያጽፍና) ከስሩ ”እነ መቶ አለቃ እገሌ ከሚያዘጋጁት ጋዜጣ የተወሰደ” ብሎ ይጽፍበታል። ”መቶ አለቃ” የሚለውን ነገር መጠቀም የፈለጉት ለውንጀላ ያመቻቸው ዘንድ ነው። እናም ተቃወምነው በጋዜጣችን። እንዲህ ብለን፦

    ”ስለማንኛው መቶ አለቃ ነው እፎይታ የምታወራው? መቶ አለቃውማ ካለበት አለ። ለዚያውም ጦር ግንባር በሄደ በአሥራ ዘጠነኛ ቀኑ፣ አንድ ኮዳ ውሀ፣ ሽጉጥና ያንጠለጠለውን ወንድነቱን ይዞ መሸሽ ያቃተው። እንዲያውም በዛፍ ጥላ ስር ቁጭ ብሎ የገበሬ ፍየል አርዶ እየበላ ሳለ ሴት ወያኔ ደርሳበት ”እጅ ወደላይ!” ብላ ስታንባርቅበት ”እግሬንስ ወዴት ላደርገው እመቤቴ!” እያለ በፍርሃት ሱሪውን ያበላሸ መቶ አለቃ የት እንዳለ እየታወቀ ወደእኛ ጣት መቀሰሩን ምን አመጣው?” አልነው። እኛ የምናውቀው የምርኮ ታሪኩም እንደዚያ ነው።

    ነገርዬው በታተመ በሣምንቱ ነገሩ በጣም የከነከነው መሆኑን የተረዳሁት ከብሔራዊ ቴአትር አቅጣጫ ሽቅብ ወደቸርችል ጎዳና እየነዳ ሳለ፣ ዋናው ፖስታ ቤት አካባቢ መብራት ይዞት ቆሟል። እኔ ደግሞ የመንገዱን ጠርዝ ይዤ በእግሬ አዘግማለሁ።

    የመኪናውን መስታወት ዝቅ አድርጎ በስሜ ጠራኝና ”አንተ ምን ልሁን እያልክ ነው?” አለኝ። በወያኔያዊ ፍጥጫ ጭምር። ”እንዴ! ምን ተፈጠረ ተስፍሽ?” አልኩት፤ ምን ለማለት እንደፈለገ ልቤ ሲያውቀው። ”ለምንድነው በጋዜጣህ የምትሳደበው?” አለኝ መልሶ።

    ”ኧረ! እኔ … እንዴትስ፤ ለምንስ ብዬ አንተን …” ብዬ ሳልጨርስ አረንጓዴ መብራት በርቶ ገላገለኝ። ከላይ ወደጀመርነው የወግ ፍሰት እንመለስ። ወያኔዎች አዲስ አበባን በወረሩ በሰባተኛው ቀን ተይዤ ሆለታ በሚገኘው ጦር ትምህርት ቤት ውስጥ ታሰርኩ። ከሣምንት በኋላ ታጋይ ተስፋዬ ገብረአብ መጥቶ እኔንና ሌሎች ሦስት ሰዎችን ይዞን ከሆለታ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። ዓላማው አዲሱን የኢህአዲግ ሠራዊት የሚያስተምርና የሚያዝናና የራዲዮ ፕሮግራም እንድንሠራ ነበር። እርሱ የተረጨውን ወያኔያዊ ጠበል ከተረጨን በኋላ።

    ያኔ ተስፋዬ አባል የነበረበት ”የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መኮንኖች ንቅናቄ” በመባል የሚታወቀው የህወሓት ጫጩት ወደሰፈረበት በቀድሞው ቤላ ኃይለሥላሴ ሆስፒታል ግቢ ነበር የወሰደን። እርሱ ግቢ በደርግ የመጨረሻ ዓመታት የጀኔራል መኮንኖች ማሠልጠኛ (ስታፍ ኮሌጅ) ነበር።

    ለአሥራ አምስት ቀናት ያህል እዚያ ግቢ በቆየሁበት ወቅት መደበኛም ሆነ መደበኛ ባልሆነ መንገድ በጦርነቱ ወቅት ስለኢህአዲግ የፕሮፖጋንዳ ሥራ ተዓማኝነት እያነሳን ተወያይተናል። ነገረ ሥራዬ ባይጥማቸው ነው መሰል ከአሥራ አምስት ቀን በኋላ እኔን ወደ ሆለታ እስር ቤት መልሰውኝ ሌሎችን አስቀሩ። ከስምንት ወራት እስራት (እነርሱ ተሃድሶ ይሉታል) በኋላ ወደ አዲስ አበባ ተመልሼ ሥራ መፈለግ ያዝኩ። ሰፈሬም አራት ኪሎ ስለሆነ ነው መሰል በማስታወቂያ ሚኒስቴር ፕሬስ መምሪያ አካባቢ አልጠፋም። በተለይም የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትን ቤተመጻሕፍት እጠቀም ስለነበር። በዚህም አጋጣሚ ነው ያኔ በሳባ ፊደል ሲዘጋጅ የነበረው በሪሳ የኦሮሚኛ ጋዜጣ ለአራሚነት የሥራ መደብ ያወጣውን ክፍት የሥራ ቦታ ያየሁት። እናም አመለከትኩ። አለፍኩም። ሆኖም መቀጠር ግን አልቻልኩም። ”እርሱን በአዲስ ዘመን ላይ የሪፖርተር ቦታ ስለምንፈልግለት በ185 ብር አራሚነት ከሚቀጠር ትንሽ ይጠብቅ” ብሎ ተስፋዬ ገብረአብ መመሪያ እንደሰጠና ቅጥሬ እንደተሰረዘ ሰማሁ። ውሎ አድሮም ለእኔም ለእርሱም ቅርብ የሆነ ሰው ሲነግረኝ ”ሰውየው ሊቀጠር አመልክቶ ነበር። ኦነግ ባይሆን ኖሮ እንቀጥረው ነበር።” አለ።

    ተስፋዬ ገብረአብ ”የጋዜጠኛው ማስታወሻ” ያለውን መጽሀፉን ሲጀምር ወታደር ከመሆኑ በፊት ለሥራ ፍለጋ ከደብረ ዘይት አዲስ አበባ መጥቶ የገጠመውን ተርኮልናል። የወቅቱ የፕሬስ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ የነበረው ሙሉጌታ ሉሌ ጎጃሜ በመሆኑ፣ ጎ ጃሜ ያልሆነው ተስፋዬ መቀጠር እንዳልቻለ በፈጣጣ አገላለጽ ነግሮናል። በእርግጥም ሙሉጌታ ሉሌ እንደዚያ አድርጎ ከሆነ ችግሩ ከእርሱ ሳይሆን ከወንበሩ መሆን አለበት። ተስፋዬ ገብረአብም በ”ኦነግነቴ” ሳይሆን በኦሮሞነቴ ምክንያት በዚያ መስሪያ ቤት ውስጥ እንዳልቀጠር አድርጎኛልና። ለእኔ ግን ከተስፋዬ ይልቅ ሙሉጌታ ታላቅ ሰው ነው።

    ሥራ አጥ ከርታታ ሆኜ በተስፋዬ ገብረአብ በሚመራው ፕሬስ መምሪያ ደጃፍ ስመላለስ፣ አልፎ አልፎ ወደ ክፍሌ ሙላቱ ቢሮ ሰላ እል ነበር። በወቅቱ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ እርሱ ያዘጋጀው በነበረው ”አድማስ” አምድ ላይ አንድ ጉደኛ ግጥም ተጽፎ በመገኘቱ ነው ክፍሌ የተባረረው። ክፍሌ ሙላት በአዲስ ዘመን ላይ ይሠራ በነበረበት ወቅት የእኔንም ግጥምች ያትምልኝ እንደነበር ከምስጋና ጋር ማስታወስ እወዳለሁ። ለክፍሌ ከሥራ መባረር ምክንያት የሆነውን የመጀመሪያ ፊደሎቹ ቁልቁል ሲነበቡ ”ትግራይ እስክትለማ ሌላው አገር ይድማ” የሚለውን ግጥም የሰጠሁት ግን እኔ አይደለሁም። ግጥሙ የማን እንደሆነ የሚያውቀው ክፍሌ ብቻ ነው።

    ተስፋዬ ገብረአብ በአዲሱ መጽሐፉ በገጽ 208 ላይ ”… ክፍሌ ሙላትና በፍቃዱ ሞረዳ የተባሉትን ጋዜጠኞች ግን ክንፈ አጥብቆ ይጠላቸው የነበረ ሲሆን ’ደመኛ ጠላቶች’ ይላቸው ነበር። …” ብሎ አለቆቹ እኔና ክፍሌን በአንድ ቅርጫት ውስጥ እንደጨመሩ ይነግረናል። ለምን ይሆን?

    ለእኔ እጅግ አስቸጋሪ በነበረበት በዚያ ወቅት ክፍሌ ሙላት፣ በእርሱም አቅጣጫ ጠቋሚነት ያገኘኋቸው እምሩ ወርቁ፣ ሰለሞን ለማና ሙሉጌታ ሉሌ የተባሉ አንጋፋ ጋዜጠኞች ዛሬ ላለሁበት ሕይወት ያደረጉልኝ ቀጥተኛ ያልሆነ አስተዋጽዖ ከአዕምሮዬ አይጠፋም። ምናልባትም ልብ ገዝቼ የሕይወቴን ተሞክሮ ቢያንስ ለልጆቼ በመጽሐፍ መልክ ማስቀመጥ ብችል ስለእነዚህና ሌሎችም ሰዎች ውለታ እጽፍ ዘንድ እግዜር የዕድሜዬና የመንጋጋ ደሃ አያድርገኝ።

    ተስፋዬ ከፕሬስ መምሪያ ሥራ አስኪያጅነቱ የተነሳው በብቃት ማጣት እንደነበረ እርሱ ራሱ ”የቅርብ ሰዎቼ ናቸው” የሚላቸው ይናገራሉ። እንዳያውም ፀሐፊው በውስጥ ስልክ እየደወለች ሊያነጋግረው የሚፈልግ ሰው መኖሩን ስትነግረው፣ ”ሰው ነው ወይስ ፈረንጅ?” እያለ እንደሚጠይቅና ፀሐፊው ”ፈረንጅ ነው” ካለች ”ወደ አቶ ያዕቆብን ላኪው” ይላት እንደነበር ማን እንደነገረኝ ረሳሁ። አቶ ያዕቆብ ወልደማርያም በመንግሥት የተመደቡለት ልዩ አማካሪው ነበሩ። ምን ያድርግ? ሪፖርተር ሳይሆን፣ አዘጋጅ ሳይሆን፣ … እንዲሁ ከአንዳች ዱብ ብሎ የአንድ ሀገር መንግሥት የፕሬስ መምሪያ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ የመሾምን ያህል ምን ፍርጃ አለ? ሥልጣን ያለልምድ፣ ሥልጣን ያለዕውቀት፣ ሥልጣን ያለችሎታ እብደት ነው።

    ከተስፋዬ ጋር ተገናኝተን ለመጨረሻ ጊዜ ያወራነው ዱከም ነው። ቀኑን ረሳሁት። እኔ ለሴሚናር ደብረዘይት ሄጄ፣ አዳራችንን አልጋ ወደተያዘልን የአትሌት ወርቁ ቢቂላ ሆቴል ወደ ዱከም መጥቼ እዚያ ሳገኘው መጽሐፍ እየጻፈ እንደሆነና ፀጥታ ፍለጋ ወደዚያ እንደመጣ ነግሮኛል። መኝታ ክፍሉ ውስጥ ሌላ ሰው ይኑር አይኑር አላየሁም። ቦታው ግን እርሱ እንደነገረኝ ፀጥታ ያለውና መጽሐፍ የሚጻፍበት አልነበረም።

    ”የጋዜጠኛው ማስታወሻ” የተባለው መጽሐፉ ከታተመ በኋላ አዲስ አበባ ካሉ ወዳጆቹ ጋር አምተነዋል። አንድ ለእርሱ ቅርበት የነበረው ጡረተኛ እንደነገረኝ፤ ተስፋዬ በመጽሐፉ የሰጠን መረጃ ከወቅቱ በጣም የራቀ ነው። እንደወዳጄ አባባል መጽሐፉ ”የአያሌ መናኛ ሰዎች የታሪክ ድሪቶ ነው።” ተስፋዬ አጋጣሚዎችን የማሰናኘት ችሎታ እንዳለው ግን ይህ ሰው አልደበቀለትም። ስለክንፈ ገብረመድህንና ስለራሱም ግንኙነት የጻፈውም ጉዳይ ከሚታወቀው በላይ የተጋነነ ነው። ክንፈ በሕይወት ባለመኖሩ፣ ተስፋዬ የሚለው ሁሉ ትክክል ነው።

    ሌላው ወትሮውንም የተስፋዬ ወዳጅ ያልነበረው ወዳጄ የጻፈልኝ ኢሜል ነው። ”ይሄ ሳሙና የሆነ ሰውዬ ያኔ የደርግ፣ ከዚያም የወያኔ ካድሬ ነበር። አሁን ደግሞ የሻዕቢያ ካድሬ ሆኖ ይላጥብናል እንዴ?” ሲል ጠይቆኛል። እኔ ምን ብዬ እንድመልስለት እንደፈለገ ግን አላውቅም።

    ተስፋዬ ለኢህአዲግ ከገበረበት ጊዜ ጀምሮ የህወሓት አባል እንደሆነ ከመጽሐፉ ነግሮናል። ”ዋሽቷል” ልበል? ምክንያቱም እኔ ሳውቀው የኢህአዲግ አንድ ክፍል ተደርጎ የሚቆጠረውና የምርኮኛ መኮንኖች ስልቻ የነበረው ”የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መኮንኖች ንቅናቄ” አባልና ሥራ አስፈጻሚ ነበር። ከእነመቶ አለቃ (ዛሬ ኮሎኔል) ዘውዱ እሸቴ፣ ከእነ ዓለምእሸት ደግፌ (የአየር ኃይል አዛዥ የነበረውና በቅርቡ የጄነራልነት ማዕረጉን ተነጥቆ የተባረረው)፣ ከእነ አባዱላ ገመዳ፣ ከእነ ሱሌይማን ደደፎ (አሁን አምባሣደር) እና ከሌሎችም ጭራሮዎች ጋር የዚያ ድርጅት ጢማም ባለሥልጣን ነበር። ስለዚያ ድርጅት አመሠራረትና አከሳሰም በመጽሐፉ ውስጥ ያልጠቀሰው ለአንዳች ብልሀት ሳይሆን አይቀርም ብለን እንለፍ?

    በማስታወሻው ስለ አቶ ደራራ ከፈኔ አሟሟት ጽፏል። ገዳዮቹም ኮሎኔል ድሪባና ሻለቃ ጀማል የተባሉ መኮንኖች እንደሆኑ ተርኳል። ዋና ገዳዩ እንደሆነ ከነገረን ከሻለቃ ጀማል ጋርም ተገናኝቶ ማውራቱን ጽፏል። እርሱ ይብላኝለት እንጂ የአምቦ ህዝብ ገዳዩቹ እነማን እንደሆኑ ለማወቅ የተስፋዬን ምስክርነት አይጠብቅም፤ አይፈልግምም። ገዳዩቹንም ለመፋረድ የተስፋዬን ትዕዛዝና አዝማችነት አይሻም። ጠላቶቹ እነማን እንደሆኑ ገና ድሮ ጠንቅቆ ያውቃል። የአምቦ ህዝብ ዓይን ኮሎኔል ድሪባና ሻለቃ ጀማል ከተባሉ ተላላኪዎች አሻግሮ የሚያስተውለው ነገር አለው።

    በቅርብ የማውቀውን ድምፃዊ ኤቢሳ አዱኛን የገደለው ጌታሁን የተባለው ኮሎኔል እንደሆነ ምናልባትም ከተስፋዬ የሰማው የደምቢዶሎ ህዝብ ተስፋዬንም፣ ኮሎኔሉንም፣ ጌቶቻቸውንም፣ ከመፋረድ የሚመለስ ከመሰለው በእርግጥም እርሱ የዋህ ነው። በመጽሐፉ ገጽ 177 ላይ እና 178 ላይ ”… ዛሬ ጉልበት አግኝተህ የምትገድለው ሰው፣ ጊዜ ጠብቆ ደሙን ይመልሳል። … በዚህ ዘመን እጅህ ላይ ደም ይዘህ መኮብለል እንደማይቻል ከቀልቤሳ ነገዎ መማር ይቻል ነበር። የኤብሳና የደራራ ድምፅ ይጮሀል። …” ብሏል። እውነት ነው። የኤቢሳ አዱኛ፣ የደራራ ከፈኔ፣ የአሰፋ ማሩ፣ የተስፋዬ ታደሰ፣ … እና የሺህዎች ደም የሚጮኸው በመለስ ወይም በአባዱላ ጆሮ ላይ ብቻ አይደለም። በተስፋዬም ጆሮ ላይ እንጂ። ደሙ በተስፋዬ እጅ ላይም አለ። ማስታወሻውም በህዝብ እጅ ላይ አለ። ታሪክ ግፈኞችን ብቻ ሳይሆን ግፍ ሲሠራ እያዩና እየሰሙ ዝም ያሉትን ጭምር ነውና የሚፋረዳቸው።

    በዚህ መጽሐፍ ገጽ 178 ላይ ፀሐፊው የተጠቀመበትን ፉሉል አገላለጽ መጥቀስ አማረኝ። ”ለገሰ አስፋው ከተባለው ድንጋይ (ሰረዝ የእኔ) የማይማር ሰው ከቶ ምን ስም ይገኝለታል?” ይላል። እርግጠኛ ነኝ ተስፋዬ በፎቶግራፍና በቴሌቪዥን ካልሆነ በስተቀር ለገሰ አስፋውን በቅርብ በዓይኑ አይቶትና አውቆት ድንጋይነቱን እየነገረን አይደለም። አለቆቹ እንደነገሩት ”ለገሰ አስፋው ሀውዜንን በአውሮፕላን አስደብድቧል።” ተስፋዬ ለለገሰ ያለው ጥላቻም ሆነ ፍቅር ይሄው ነው።

    የታሪክ መልካም ፈቃድ ቢሆንና የኃጥያት እዳን ማውረጃ ጊዜ ቢመጣ የለገሰ አስፋው ኃጥያት ከመለስና ከበረከት፣ ከኃየሎምና ከስዬ ቢያንስ እንጂ አይበዛም። ድንጋይነት በኃጥያት ብዛት ወይንም በደም በመነከር ብልጫ ከሆነ ጌቶቹ በምን አይነቱ ድንጋይ እንደሚመሰሉ ተስፋዬ በሚቀጥለው መጽሐፉ ይነግረን ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። ስለዚህ ”የጋዜጠኛው ማስታወሻ” ስለተባለው ባለ 412 ገጽ መጽሐፍ ብዙ ማለት በተቻለ ነበር። ሁለት ነገሮች ያስቸግሩናል እንጂ። የርዕሱ የወቅታዊነት ጥያቄና የመጽሔቱ (”ናፍቆት ኢትዮጵያ”) ገጽ ውሱንነት።

    ጽሑፌ አሰልቺ እንዳይሆን አድርጌ እንዳልጻፍኩት ይታወቀኛል። የበለጠ አሰልቺ እንዳይሆንም አንድ ሁለት ቁምነገሮችን ወጋ አድርጌ ጠቅላላ ሃሳቤን በአንድ እግሩ አቁሜው ሹልክ ልበል።

    በመጀመሪያ ደረጃ ተስፋዬ ይህን መጽሐፍ ሊጽፍ የማይችልበት ሁኔታ ነበረ? የሚለው ጥያቄ ነው። የእኔ ምላሽ አዎ! ነው። ለምን ቢሉ፣ በህወሓት መሀከል የተፈጠረው መከፋፈል ባይከሰት ኖሮ የተስፋዬ ነፍስ ፍርሐት ውስጥ አትገባም ነበር። አይሸሽምም። በተሸናፊው በዓለምሰገድ ገብረአምላክ ጎራ ውስጥ ሆኖ የበረከትና የክንፈ ሰለባም አይሆንም ነበረ። ቀድሞውኑም ሰልፉን ከእነ በረከት ጋር አስተካክሎ ቢሆን ኖሮም ምናልባት ይሾም ይሸለም እንደሁ እንጂ ዝንቡን ”እሽ” የሚልለት ”ወንድ” ባልተገኘም ነበር። ለማንኛውም እግዜር እንኳንም ”ልዩነት” የተባለውን ነገር ፈጠረ። ለወደፊቱም ልዩነት ለዘላለም ይኑር! ተፈጥሮም ነውና።

    ሌላው ወደድንም ጠላንም፣ በክፉም በደጉም የዚህን ሰው ነገር ስናነሳ፣ ስንጥል ታሪኩን እየጻፍንለት ነው። ብልጥ ሰዎች እየነከሱንም፣ እየሳሙንም፣ እየወደዱንም፣ እያወገዙንም፣ እያወደሱንም፣ እየሰበሩንም፣ እየጠገኑንም፣ … ታሪካቸውን ያጽፉናል። በቃልም፣ በወረቀትም። የእኛን አዳፍነን የእነሱን እንድናራግብ ይሸነቁጡናል። በእርፍናቸው ለበቅ፣ በእርድናቸው አኮርባጅ።

    ነገር ግን፣ እያንዳንዳችን ታሪክ አለን። እያንዳንዳችን የምትጻፍ፣ የምትነበብ፣ ነፍስ አለችን። እያንዳንዳችን አንድም ጥሩ መጽሐፍ ነን። አለበለዚያም ጥሩ መጽሐፍ ይዘን ኖረን፣ ያልተጻፈ ጥሩ መጽሐፍም ይዘን እናልፋለን። መጥኔ ለዕድል

  11. Tesfaye, we all know Hilawe and ohers have again become agents of the EPRP. Berhanu himself is flirtign with them. The EPRP is the shrillest anti Tigrean budn like you and your master Isayas. Leave Seye alone. He is a hero.Tigreans will thrive. Go bend over to Eyasu and Isayas.

  12. Like any other leader Isaias May have his shortcomings. For instance he is ruthless to his enemies and I believe sometimes he should be forgiving. However I do not think even Meless doubts Isaias’s War heroism. Isaias started his struggle as a fighter. Later he become the commander of one of the three Hisbawi Hailtat Birgades. Remebber that means he was one of the three known military leaders in the Hisbawi Hiltat. Many will tell you Isaias never look back during war and he had to be reminded that he should not do that. Actually all shaebia leaders except few had to prove themselves in a battle field before they climb to any leadership position. As to Melles do you know the history how he betrayed his friends when they were preparing to go from Asmara to the Battle field? He told them to go and he would follow them in a couple of days. Finally he ended up in Adi quala also Eritrea. When his friends worried and came back to know what happened to him they found him in a Bar in Adiquala and they had to take him with them. So Meless could be politically flexible and ready to serve others as long as they are ready to protect him but I do not think he is a war hero. By the way it is difficult to compare Meless and Isaias. While meless uses Ethiopian aid money to get his children educated in the Goregetown University Isaias sends his children to Sawa like any other Eritrean. While Meless squanders Ethiopian money to European banks and establishing private printing press in Kampala Isaias and his family live in a small Villa in Asmara.What about what Azeb Mesfin is doing? I should not talk about it in here because it is widely known by Ethiopians. Let me tell you what they do in Uganda. All spouses of the president and minsters have private business. When someone wants to bribe the president or ministers he/she has to meet the presidents and minsters spouses. That is how africa is governed, how is Ethiopia different form this?

    By the way don’t count professor Tasfatsion as an Eritrean. He is one of those who do not see light at the end of the tunnel. During the durge Era he told Eritreans to accept autonomy with Ethiopia. He even worked with durg to distengrate eritrea into smaller states. He is a loser who can not controll his perosnal ambition. “Ane intemoite Saeri Aitbukela” If I die grass should not grow said donkey. kind of thing. Did you hear the Eritrean leadership responding to him? Never. They do not take him seriously. He is interested in selling useless books by resurrecting dead ideas. Long live Eritrea

  13. ስለ ”የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መኮንኖች ንቅናቄ” ያለህን በሚቀጥለው ማስታወሻ ብታወጋን ጥሩ ይመስለኛል።

    “ተስፋዬ ለኢህአዲግ ከገበረበት ጊዜ ጀምሮ የህወሓት አባል እንደሆነ ከመጽሐፉ ነግሮናል። ”ዋሽቷል” ልበል? ምክንያቱም እኔ ሳውቀው የኢህአዲግ አንድ ክፍል ተደርጎ የሚቆጠረውና የምርኮኛ መኮንኖች ስልቻ የነበረው ”የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መኮንኖች ንቅናቄ” አባልና ሥራ አስፈጻሚ ነበር። ”
    እኔም ማስታወሻ አለኝ (በፈቃዱ ሞረዳ)

  14. To Fekadu Moreda!
    I read twice your article but Í couldn’t get your point. You repeat only what Tesfaye put in his Book, as he was not competent to do the Job assigned for and so on. He said one word about you and with that word he systematically told us you are worthless person. You wrote one page to make Tesfaye dawn but you still totally failed but you expose yourself that you are a crying baby. It is no wonder that you were rejected from the Job you applied. You are unbalanced and biased with complexes. You said Tesfaye’s command of English was poor. Come on! Mastering English is not all. Those of us who studied at German Universities or France don’t master English either but does it mean we are less intelligent? As far as Tesfaye is concerned, he is good in Amharic.

  15. Tesfaye Gebreab,

    Thanks for the excellent analysis presenterd once again with outstanding literature skill.
    Do not take corrupted people like Befikadu Moreda seriously!
    I also listned your interview with Abebe Belew of Addis Dimts. He did not act as journalist. He tried to make it Hard talk. But, he was one sided, exposing his political motivation including by defending his Woyane friend Abreha Belay!
    Abreha Belay is another diabolic Woyane trying to come back with other evil woyanes like Siye and Gebru through another door.

  16. Tesfaye was just 23 years old young when he assumed the head of the press office under woyana. Who is not tempted to hold that position in that age? What is funny is that we know many Drs and I know it all people who joined woyana after woyana had controlled Addis Abeba. Among them are current political opposition groups and leaders.

    Tesfaye clearly told us that it was not his child dream to become politician what so ever, but to be a writer like Bahalu Girma and others who inspired him. He said he is sorry in his book and presented himself, as he was the victim of woyana because they exploited his young hood and his Eritrean root more than he wanted.
    He is a hero because he came forward when he was awake. He confessed all of the sins he has done.
    Tesfaye is a person with a human value and has high moral standard. Thank you Tesfaye…Ethiopia needs you today more than ever…. don’t be distracted with these lame and jealous and unconfident guys…they see you how you started, but can’t see how you grow each day in intellect and moral. They are fixed morons and you are progressive…

    Please do not touch Tesfaye…he magnanimous and progressive…he could not sell himself forever….

    Hi, Tesfaye…. We love you…. and you know better the more you Ethiopian the more the enemies multiply…let this man ego go…don’t give him answer……….

  17. I am already biased about this man

    What a writer, this helps me not to quite hope on ethiopian journalist.

    Please be carefull of those woyane hit men.

    peace

  18. Dear Ato Befikadu Moreda,

    First of all i would like to remind you that i am someone who strongly believes that anyone should have unreserved right and freedom to express his/her own will (or better to say his/her own view)..but, as you might know, whatever one says is limited to his/her own understanding and it does by no means portray the mind of nations as a whole…. let me remind you again, in case you overlooked or forgot it, What makes unity with in a country of nations that has got variety of cultural and other differences is not their similar thinking- it is neither their similar approach they use to address a problem.. it is only their common purpose.. it is that common destiny all seek to achieve that binds all as one…….. Remember the story of David in Bible…. you don’t need to be a religious person to appreciate stories… you got so much to learn from the story.. just consider it as a story that narrated past events….. David did sin so much (even more than what king Saul did)..But David was so much graceful in front of his God hence his people as well… Do you know what made him so much loved in front of his God and people????? He had a soft heart.. David was always so determined to admit his trespasses.. and God and the people as well love this kind of person… there is no better hero than that one who admits mistakes …… Individuals have their own way of coming to truth.. some wait till others tell them..some feel it and go by themselves..others will be forced by situations till they admit their trespasses…… it doesn’t matter whichever way one comes through…… so long as he holds the banner for our common purpose… so long as he got his real commitment to contribute (in his own way) for the struggle to our freedom …… After all, we all know what makes South Africa better off today…it has not been even two decades since humanity prevailed.. we all know what made Mandela an international hero..let me tell you in case you don’t know, Mandela (who suffered so much during apartheid regime) has a soft heart like king David – that he was so determined to forgive those who committed unthinkable atrocity against himself and his people.. and the people followed his example – because he is so gracious in front of his people… and now, South Africa is better off than those old days…….. You see – the struggle of Ethiopian people is not a political struggle in a sense- i do personally believe that our struggle is for justice, our struggle is to compel those tribal gangs who are destroying Ethiopia to come to a term where they know that all men are created equal and Ethiopia belongs to all equally…. In the course of our struggle to secure justice in Ethiopia, we condemn those ethnic blinded TPLF gangs who are not demonstrating any sign of remorse for their vicious actions…and yet, we are not struggling to condemn .. beware Ato Befekadu Moreda, let me remind you again – Our struggle is not to condemn personalities, rather it is to secure justice and to rebuild Ethiopia…. one way or another we all sin …. Let us all welcome all those sinners (who betrayed their people and country) who demonstrated real remorse for their past wrong doings and who are now committed to help destroy lawlessness and dictatorship from Ethiopia. Let us not punch each other – let us not become vicious hands for TPLF gangs! Equality to all the people – and the people are:
    – Oromo people
    – Amhara people
    – Tigre People
    – all other ethnic groups i did not mention here.

    Ethiopia prevails as a country. Ethiopia will prevail as a nation on the grave of TPLF regime.

    Long live the people!
    Long live Ethiopia!

  19. fekadu moreda, politically you are moron. Please attache some facts when you disagree with somebody. I think from what i have read from your letter, you lack the critical thinking to understand this world politics, especially ethiopians

  20. Dear Ato Befikadu Moreda,

    First of all i would like to remind you that i am someone who strongly believes that anyone should have unreserved right and freedom to express his/her own will (or better to say his/her own view)..but, as you might know, whatever one says is limited to his/her own understanding and it does by no means portray the mind of nations as a whole…. let me remind you again, in case you overlooked or forgot it, What makes unity with in a country of nations that has got variety of cultural and other differences is not their similar thinking- it is neither their similar approach they use to address a problem.. it is only their common purpose.. it is that common destiny all seek to achieve that binds all as one…….. Remember the story of David in Bible…. you don’t need to be a religious person to appreciate stories… you got so much to learn from the story.. just consider it as a story that narrated past events….. David did sin so much (even more than what king Saul did)..But David was so much graceful in front of his God hence his people as well… Do you know what made him so much loved in front of his God and people????? He had a soft heart.. David was always so determined to admit his trespasses.. and God and the people as well love this kind of person… there is no better hero than that one who admits mistakes …… Individuals have their own way of coming to truth.. some wait till others tell them..some feel it and go by themselves..others will be forced by situations till they admit their trespasses…… it doesn’t matter whichever way one comes through…… so long as he holds the banner for our common purpose… so long as he got his real commitment to contribute (in his own way) for the struggle to our freedom …… After all, we all know what makes South Africa better off today…it has not been even two decades since humanity prevailed.. we all know what made Mandela an international hero..let me tell you in case you don’t know, Mandela (who suffered so much during apartheid regime) has a soft heart like king David – that he was so determined to forgive those who committed unthinkable atrocity against himself and his people.. and the people followed his example – because he is so gracious in front of his people… and now, South Africa is better off than those old days…….. You see – the struggle of Ethiopian people is not a political struggle in a sense- i do personally believe that our struggle is for justice, our struggle is to compel those tribal gangs who are destroying Ethiopia to come to a term where they know that all men are created equal and Ethiopia belongs to all equally…. In the course of our struggle to secure justice in Ethiopia, we condemn those ethnic blinded TPLF gangs who are not demonstrating any sign of remorse for their vicious actions…and yet, we are not struggling to condemn .. beware Ato Befekadu Moreda, let me remind you again – Our struggle is not to condemn personalities, rather it is to secure justice and to rebuild Ethiopia…. one way or another we all sin …. Let us all welcome all those sinners (who betrayed their people and country) who demonstrated real remorse for their past wrong doings and who are now committed to help destroy lawlessness and dictatorship from Ethiopia. Let us not punch each other – let us not become vicious hands for TPLF gangs! Equality to all the people – and the people are:
    – Oromo people
    – Amhara people
    – Tigre People
    – all other ethnic groups i did not mention here.

    Ethiopia prevails as a country. Ethiopia will prevail as a nation on the grave of TPLF regime.

    Long live the people!
    Long live Ethiopia!

  21. Mr Fikadu Moreda,

    you couldn’t become articulate and successful by negative and personal hate towards other writers (tesfaye) to prove and tell us that you are better writer or articulate. First and most look at your title. it shows me that you are trying to mimicking Tesfaye. first of all if you are a good writer (which you are not) pick your own subject, gather factual materials that will help you make it believable and try to capture our imagination as tesfaye did. as for me you are just amateur.

  22. I really enjoy your analysis. keep the good work…”The truth shall make you free”. We all have one life to live. It is honorable to live courageous and truthful for ourselves.

Leave a Reply