Skip to content

ENTC to convene its general assembly on Feb. 22 in Washington DC

The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) announced that it will hold its mid-term general assembly in Washington DC from Feb. 22 – 24, 2013. The meeting will evaluate ENTC’s activities of the past six months and will make necessary adjustments, its news release said.

Representatives of ENTC chapters and local councils from several cities and countries around the world are expected to participate in the 3-day meeting that will be held inside its headquarters in Washington DC.

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሽግግር ም/ቤት ጠቅላላ ጉባኤ በዋሽንግተን ዲሲ በፊታችን የካቲት (ፌብሪዋሪ) ወር ይከናወናል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ም/ቤት ላለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ሲያከናዉን ቆይቷል። ከም/ቤቱ ምስረታ በኋላ የአካባቢ ምክር ቤቶችን (ቻፕተሮችን) በተለያዩ አገሮች በማቋቋም፤ ድርጅታዊ አቅምን በማጎልበት፤ የትግል ሂደት አቅጣጫን በመቀየስ፤ ከሌሎች ድርጅቶች ጋረ ትብብር በመፍጠርና እንዲሁም አቅሙንና የትኩረት አቅጣጫውን ኢትዮጵያ ውስጥ በማድረግ በርካታ ስራዎችን አከናውኗል። የም/ቤቱ ጠቅላላ ጉባኤ በዳላስ ቴክሳስ የምስረታ ስብሰባው ላይ በወሰነው መሰረት የስድስት ወራቱን የስራ እንቅስቃሴ ለመገምገምና ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ቀጣይ እቅዶችን ለመንደፍ በአሜሪካን ዋና ከተማ በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ጽ/ቤቱ ከፌብርዋሪ 22 እስከ 24 ቀን 2013 እኤአ ያካሂዳል። በተለያዩ ሀገሮችና ከተማዎች ቀደም ብለው የተቋቋሙና በመቋቋም ላይ ያሉ የአካባቢ ምክርቤቶች (ቻፕተሮች) ተወካዮች በጠቅላላ ጉባኤው ላይ ይሳተፋሉ። ስብሰባውም በስድስት ወራቱ ውስጥ የታዩትን ጠንካራና ደካማ ጎኖች በመገምገም የሚቀጥሉት ስድስት ወራት አካሄድን በተመለከተ የተለያዩ የፖሊሲና የተግባር ውሳኔዎችን ያስተላልፋል። በስብሰባውም መዝጊያ ዕለት በፌብርዋሪ 24 ቀን 2013 (እኤአ) ህዝባዊ ስብሰባ በማዘጋጀት በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ላይና መወሰድ ስለሚገባቸው ፈጣን እርምጃዎች ህዝባዊ ውይይት ያደርጋል። በዚህ ህዝባዊ ስብሰባ ላይ መላው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ሁሉ እንዲገኙ እየጋበዝን ወደፊት ስለስብሰባው ቦታና ፕሮግራም ዝርዝር መረጃዎችን የምናወጣ መሆኑን እንገልጻለን።

የሽግግር ም/ቤቱ አመራር

Leave a Reply