The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) has sent a communique to the Honorable Guido Westerwelle, Federal Minister for Foreign Affairs of Germany, requesting a diplomatic recognition.
The letter was sent to the Minister by Mikael Endriase, ENTC’s diplomatic representative in Germany.
The letter explains ENTC’s mission, and discusses the worsening political, economic and security crises in Ethiopia, as well as the need for the German government to help with a peaceful transition to democracy.
Diplomacy is one of the primary tasks that the ENTC general assembly assigned to the leadership at the July 2012 conference in Dallas.
For more info: [email protected]
Website: www.etntc.org
ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ
ኢትዮጵያዊያኖች አዲሱን ዓመታቸውን የዘመን መለወጫ በሴፕቴምበር 11 አክብረዋል፡፡ አሁን በኢትዮጵያ 2005 ዓም ነው፡፡ በሴፕተምበር 21 ደግሞ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ተሰጥቷቸዋል፡፡ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ከአዲስ ዓመት መግባት ጋር ተዳምሮ ሲቀርብ እንዴት ደስ ያሰኛል!! ከልብ የመነጨ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክትና መልካም ምኞት ለኢትዮጵያ ሕዝቦች ተገቢ ነው፡፡
በልዩ ጥሪ በተሰበሰበው ፓርላማ መሃል ተገኝቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቃለ መሃላ ፈጸመ፡፡ ሊሆን በሚገባው መልኩ ስርአቱን አሟልቶ ባይከናወንም፤ ቀዝቀዝ ባለ ሂደት ነበር የተከናወነው፡፡ ቱልቱላ አልተነፋም:: ሰልፍ አልተከናወነም:: የሹመት ያዳብር ድግስም አልነበረም:: አነስ ቀዝቀዝ ባለ ቴአትራዊ አካሄድ በተቀረጸ ፕሮግራም ነበር ክንዋኔው፡፡ ከ547ቱ አባላት የተገኙት 375ቱ አባላት ትንፋሻቸውን ውጠው በመቀመጥ የሃይለማርያም ደሳለኝን የሰጠውን ዲስኩር ካዳመጡ በኋላ በጭብጨባ ተቀበሉት፡፡
ካለፈው ሜይ ጀምሮ የሃይለማርያም እንቅስቃሴ ባልለየለት የፖለቲካ ወዠብ ውስጥ ነበረ፡፡ አጠራሩ ሳይቀር ያልለየለት ነበር፡፡ “ዴፒዩቲ” ፤ “አክቲንግ”፤ “ኢንትሪም” በመባል ለአንድ ቦታ ዝብርቅርቅ ያለ ተቀጥላ ነበር ሲለጠፍበት የነበረው፡፡ ያም ሆኖ የመጨረሻዎቹ ሁለቱ ስያሜመዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ውስጥ ያለተጠቀሱ በጀርባ ሹዋሚ ሻሪዎች የተለጠፉ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሌለበት ወቅት የዲፒዩቲው ተግባር ምን መሆን እንዳለበትም በአግባቡ ባለመቀረጹና የመተካካቱ ሂደትም ምን መምሰል እንዳለበት ባለመስፈሩ ጥየቄዎች ያስነሳና ግራ ያጋባ ጉዳይ ነበር፡፡ እነዚህን ሁኔታዎች ችላ ማለት ቢቻልም፤ የሃይለማርያም ደሳለኝ በስርአቸቱ ቃለመሃላ ፈጽሞ ወደ ተግባር የመግቢያው ቀን በተደጋጋሚ አለአንዳች ማስገንዘቢያና ሰበብ ሲተላለፍ ከረመ፡፡ ይህ በራሱ በአመራሩ ውስጥ አለመግባባት መጥፋቱንና በንትርክ ውስጥ ሊሆኑ ይችላሉ የሚለውን መላ ምትም በሰፊው አስነስቷል፡፡ ሁኔታውን የበለጠውን ውዥንብር ውስጥ የከተተው ደግሞ፤ከተቆረጠው የመሃላ መፈጸሚያ ዕለት ቀደም ብሎ ቃለ መሃላው በኦክቶበር መግቢያ ላይ ይከናወናል የሚልም መግለጫ ወጥቶ ነበር፡፡
ሰበቡ ባልታወቀ መነሾም ፓርላማው በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ ጥሪ ተላልፎ፤ የበለጠውን የባለስልጣናነቱን አለመግባባት ጥርጣሬ ሊያባብሰው በሚችል መልኩ የቃለ መሃላው ዕለት ተወስኖ ፓርላማው ተሰበሰበ፡፡ ሃይለማርያም በስተመጨረሻውም በስጋት ደመና በተከበበ ሁነሜታ ስልጣን ተረክባል:: ታዛቢዎች እንደሚሉት ሃይለማርያም ቢሮውን፤ የ “ይስሙላ ሹም”፤ “ግንባር ቀደም ሰው”፤ “መቀመጫ አሟቂ” ለመሆን፤ ለቀሪ ጥቂት የሽግግር ጊዜ ቦታውን የተረከበነው ይሉታል፡፡ ገምጋሚዎች ከሁኔታው ግራ አጋቢነትና አጠራጣሪነት በመነሳት ሃይለማርያም በቅንጣቢ ነጻነት ብቻ በሌሎች ወሳኞችና የሂደት ትልም አፍላቂዎች የጀርባ ጉሽሚያ የሚንቀሳቀስ እንጂ ፖለቲካውን፤ኤኮኖሚውን፤የሚያሽከረክሩት ከበስተጀርባ ያሉት ናቸው ለማለት ችለዋል፡፡ አንዳንዶች እንደሚሉት ደግሞ ሃይለማርያም ቴክኖክራት በመሆኑ እንደዚህ በመርዝ ተለብጦ ባኮፈኮፈ የፖለቲካ መሳርያ ውስጥ ሊቆይ አይችልም ነው፡፡
አንዳንዶቻችን ደሞ ምናልባትስ፤ ቢሆንስ፤ በሚል አስተሳሰብ እስቲ እንሞክረው ቆየት ብለን እንየው እንላለን፡፡ የሃይለማርያም የስልጣን መረከቢያ ዲስኩር በአብዛኛው ያተኮረውና በተደጋጋሚ አጠናክሮ ያሰመረበት፤‹‹መንገዱን ሳንለቅ›› ‹‹ሳይሸራረፍ›› በሚለው ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ ሲያረጋግጠውም በእሱ አመራር የተጀመረውን ፕሮግራምና የተቀየሰውን ፕሮጄክት ጨምሮ ለፍጻሜው መጣር ነው፡፡ ተግባራችንም በተቀየሰው ፈር በመጓዝ በፓርቲያችን ስትራቴጂና መመርያ መሰረት በፈሩ ላይ መቀጠል ነው፡፡ ልማትንና ዴሞክራሲን የተባበረ አመራራችንን በማጠናከርና ሕዝቡንም በማካተት የተጀመረውን ሂደት እንቀጥላለን››፡፡ በመቀጠልም ‹‹የገጠሩን ልማት በዘመናዊ መልክ በማደራጀት የእርሻውን ክፍል ኤኮኖሚ ማሳደግ ቅድመ እቅዳችን ነው፡፡›› የሚመራው መንግስት አለ ‹‹የእርሻውን መሰረተ ልማት ለማሻሻል ቅድሚያ እንደሚሰጠው፤ ስርአተ ትምህርቱንም፤ ከብት እርባታውንና አርቢውንም፤ እንደሚያበረታታን ለተሸለ እድገትም እንደሚጥር ወጣቱንም ወደ ተሸለ የትምህርትና ለአመራር የሚያበቃውን እውቀት ላማስጨበጥ እንደሚተጋ በንግግሩ አካቷል፡፡ ሃገሪቱ በሳይንስ፤ በቴክኖሎጂ፤እና በሂሳብ ላይ ያተኮረ ስርአተ ትምህርት እንደሚያስፈልጋት፤ ጠቅሷል፡፡ሴቶችንም በተመለከተ ለተሻለ ዕድል ተጠቃሚነት የሚያበቃ፤ለጤንነታቸው ትኩረት እንደሚደረግ፤የተሸሻለ የእናቶች ጤና አጠባበቅንም አስፈላጊነት ትኩረት እንደሚሰጠው አስገንዝቧል፡፡ ችግሮችን ለመፍታትም ምሁራን ምርመራቸውንና መፍትሔ በመሻት ላይም ትኩረት እንዲያደርጉና የሙያ ማሕበራትም በዚሁ ላይ ትኩረታቸውን እንዲያደርጉ ጥሪውን አቅርቧል፡፡
‹‹ምኞቴ›› አለ ሃይለማርያም፤‹‹ኢትዮጵያ በሚቀጥለው አስር ዓመት የመሃከለኛ ገቢ ከሚባሉት ሃገሮች እኩል ተሰልፋ ማየት ነው፡፡ይህንንም ግብ ለማድረስ፤በኢንዱስትሪ ላይ የበለጠ መሻሻያ ሊደረግለት ይገባል፡፡ የልማት ማነቆ የሁኑትን ጎታቾች ልዩ ትኩረት ይደረጋል፤ የኤክስፖርት ሃይላችንንም ማጠናከርና ማሻሻል፤በመንግሥትና በግሉ መሃል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር፤ያስፈልጋል፡፡ በአዲስ አበባ ያለውን የቤቶችና የትራንስፖርት ችግር ለማቃለልም ቃል ገብቷል፡፡›› ኤኮኖሚውንም በተመለከተ ምንም እንኳን ግሽበቱ እየቀነሰ ቢሆንም የበለጠ ማውረድና ማስተካከል አስፈላጊ ነው በማለት ተናግሮ፤ ኢትዮጵያውያን ጥርሳችንን ነክሰን፤የታቀደውን የምድር ባቡር፤ ትራንስፖርት፤ሃይድሮ ኤሌክትሪክን ሃይልን፤ ቴሌኮሙኒኬሽንን፤በትክክል በስራ ላይ በአግባቡ መሄዳቸውን ማረጋገጥ ይኖርብናል፡፡ በአባይ ተፋሰስ ላይ የሕዳሴውን ግድብ ከግብ ለማድረስ ቃል ገብቷል፡፡በመሬት አስተዳደር ያለውን ሙስናና የአስተዳደር ስንኩልነት የኪራይና የታክስ አሰባሰብን በተመለከተ፤ ያለውን ብክነትና ስርአት የጎደለውን አካሄድ ለማስተካከል የሕዝቡ ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አንስቷል፡፡በመልካም አስተዳደር ድክመት፤በፖለስ፤ በፍትህ፤በደህንነትም በኩል ያለውን የተበላሸ አሰራር ማስተካከልና መስመር ማስያዝ ማስፈለጉንና መንግሰትም ትኩረት እንደሚያደርግ ሳያነሳ አላለፈም፡፡
ሃይለማርያም የሰብአዊ መብት ጉዳይ እጅጉን አስፈላጊ መሆኑን በማንሳት ፓርላማውም ለመሻሻሉ አስፈላጊውን በሚመለከተው ኮሚቴ በኩል እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል፡፡የኢትዮጵያን ምርጫ ቦርድ፤የሰብአዊ መብት ኮሚሽንን፤የነጻውን ጋዜጦች፤የተቃዋሚዎችን ጉዳይ በሃገሪቱ ያላቸውን ሚናና አስፈላጊነት በተመለከተ ለዘብተኛነት ያለው አመለካከት አሳይቷል፡፡በደፈናው ከሲቪክ ማህበረሰቡ፤ከነጻው ሚዲያ፤እና ከሌሎችም ተዛምዶ ካላቸው ጋር በህብረት እንሰራለን ከማለት ያለፈ አልተናገረም፡፡የውጭ ግንኙነትንም በተመለከተ፤ትኩረቱ የነበረው ሃይማኖታዊ ጉዳዮች፤ኢትዮጵያ ለሰላምና መረጋጋት በሶማልያ ስላደረገችው፤ሁለቱን ሱዳኖች በተመለከተ የነበራትን ሚና አነሳ እንጂ እልፍ አላለም፡፡
ንግግሩ ቴክኖክራት ተብሎ ሊጠቀስና ሃገሪቱን ወጥሮ የያዛትን ችግር ሊፈታ የሚችል ተብሎ ሊተረጎም የሚችል አይደለም፡፡ንግግሩ አጭርና በጥንቃቄ የተዋቀረ ነው፡፡ በሃገሪቱ ላይ ጎልቶ የሚታየውን የኑሮ ችግርና በዚህና በሌላም ሰበብ ምሬቱ ከቀን ወደ ቀን እየባሰ መሄዱን፤ የፖለቲካው ጉዳይ መላ ቅዱሱ ጠፍቶ ተቃዋሚ ተብለው የታወቁና የተፈረጁም እግር ተወርች ታስረው የባሰባቸውም ነፍስን ለማትረፍ ሲሉ ሃገራቸው ጥለው ስለመሰደዳቸውም ሆነ ስለመሰል ችግሮች የተነሳ የለም፡፡ በአጠቃላይ የተጀመረውን ለመጨረስ እጅን ጓንት ሆነን እንሰራለን ለዚህም ሕዝቡ አብሮን እንዲቆም እጠይቃለሁ ብቻ ነው በደፈናው፡፡ የሕዝቡን ኑሮና የስራ ፍላጎት የእድገትንና የልማትና ማፋጠን ዘዴ እንዲህ ነው ብሎ የተላለፈም መልእክት አልተደመጠም፡፡
እርግጥ የሃይለማርያም ንግግር ላለፉት በርካታ ዓመታት ስናዳምጠው ከነበረው በተለያየ መልኩ የተሸለና ለለውጥ የሚበቃ ነው፡፡ የንግግሩ አቀራረብ አክብሮት የታየበት በመሪነት ያለ ሰው ሊያደርገው የሚገባ ነበር፡፡ ዘለፋና ማን አለብኘነት እኔ ብቻ የሚል ስሜትም አልታየበትም፡፡ንግግሩ የተነደፈልንን የሚለው ዛላ ባይደጋገምበት፤ እንዳለፈው ወታደራዊ ሃይልና የኔ ብቻን በአውራው መንገድ ላይ የሚል አዘዥነት የተሞላውም አልነበረም፡፡ እንዳለፈው ቁልፍ የመሸንቆጫ የነበሩትን ኒዎ ኮሎኒያሊዝም፤ ኒዎ ሊብራሊዝም፤እና ኢምፔሪያሊዝም በሚከል የኢትዮጵያ ችግር ሰበብ ሆኖ የዘመቱበት የቃላት ድርድር አልነበረውም:: በሃገር ውስጥ ባሉ ተቃዋሚዎችና በአካባቢ ሃገሮች ላይ የጥላቻ ዘመቻ ጥሪም አልቀረበም፡፡ ብክነትን፤ ሙስናን፤የአስተዳደር ጉድለትን፤ሥልጣንን አለአግባብ መጠቀምን አንስቶ እንኳ ሲናገር ማስፈራራት ጨርሶ ሳይገባበትና አካኪ ዘራፍ ሳይጨመርበት፤ ህጋዊ ተጠያቂነት መኖሩን ብቻ በማሳሰብና ሁሉም ለዚህ ነቅቶና ተግቶ እንዲቆም ከማለት አላለፈም፡፡
ሌላው የሚያስገርመው ነገር፤ንግግሩ እንዳለፈው የፉከራ፤እራስን ማዋደድ እና በድል አድራጊነት ደረት ድለቃም አለመኖሩ ነው፡፡የገዢው ፓርቲም አልበገርም ባይነትና ገናናት አልመንጸባረቁ፤ እራስን ከፍ ከፍ፤እራስን ማዋደድም አልተደመጠበትም፡፡በለስላሳው ተቃዋሚዎችና ሕዝቡም በአንድነት በመስራት ሃገሪቱን ከችግር ማውጣት እንዳለባቸው አሳስቧል፡፡ንግግሩ አዲስ ተስፋና ራዕይ ከማሳየት ይልቅ ባለው ላይ በትጋት እንዲሰራ የሚጠይቅ ነበር፡፡ በጽሁፉ አርቃቂዎች የጎደለውን ሃይለማርያም በቃላት አጣጣሉ፤ በርቱእ አንደበቱ፤ በረጋ ስልቱ አሟልቶ አቅርቦታል፡፡
ያልተባለውስ
ያልተነሱ በርካታ ጉዳዮች አሉ፡፡ምንም እንኳን ሃይለማርያም ስለ ዋጋ መዋዠቅና ስለ ገንዘቡ መውደቅ፤ስላለው የኤኮኖሚ ችግር ቢነሳም ስለመፍትሔው ግን ምንም አልተናገረም፡፡በተደጋጋሚ በተሰመረው መንገድ ላይ እንሂድ ነው ያለው፡፡ብሔራዊ የእርቅን ጉዳይ አሁን ያለው መንግሥት ግንዛቤ የሰጠው ጉዳይ ነው? ስለሽግግሩም ጉዳይ ቢሆን እንዲህ ነው ወይም ይሆናለል የተባለበት ቦታ አልተደመጠም፡፡
ስለታሰሩትም ለቁጥር የታከቱ የፖለቲካ እስረኞች መፈታት ጉዳይ ምንም አልሰማንም፡፡ከዚሁ ጋር በተመሳሳይ አፋኝና ለሰበብ መፈለጊያ ስለተነደፉት አዋጆችና መሻሻል ስለሚገባቸውም ሆነ መለወጥ ስላለባቸው የሽብርተኝነትና የሲቪል ማሕበረሰቡን የሚመለከቱ አዋጆች ምንም የተባለ የተነሳ የለም፡፡ለበርካታ ዓመታት የኢትዮጵያ መንግሠት በሰብአዊ መብትና በዴሞክራሲ ጉዳይ ላይ አላግባብ ዜጎች ስለመታሰራቸው፤የፕሬስ ሕጎች አፋኝነት፤ ስለጋዜጠኞች መታፈንና መታሰር በዓለም ተሟጋቾች እንደተወቀሰና እንደተከሰሰ ነው፡፡ስለዚህም ጉዳይ የተባለ የለም፡፡
ቃልና ተግባር፤ የአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር መጫሚያ አብዛኛውን ጊዜ የፖለቲካ ሰዎችን ከንንግራቸው መገመት አስቸጋሪ ነው፡፡ ዘወትርም ፖለቲከኞች ንግግር ሲያደርጉ ለሕዘቡ የሚጥመውንና በልቡ የቋጠረውን፤ ምኞቱንና ችግሩን የሚያኩለትን በአማሩ ቃላቶች ጠቅልለው ያቀርቡና በትግበራው ወቅት ፍየል ወዲያ ቅዘምዝም ወዲህ ይሆናሉ፡፡ ምንግዜም ቢሆን ተግባር ከቃላት ይበልጥ እውነትነት አለው፡፡ሃይለማርያም በንግግሩ እራሱን፤ ሕዝቡን፤ፓርቲውን በስራ ለማነሳሳት ጥሯል፡፡ ያም ሆኖ ያለበት ሁኔታ በእጅጉ ችግር የተበተበው ነው፡፡ በፍላጎቱና አምኖበት ይሁን አለያም እጁን ተጠምዝዞ ልኩ ያልሆነውን መጫሚያ ግባበት ተብሏል፡፡ ለዚህም ነው በተነጠፈለት የካባ መንገድ ላይ መራመድ እንዳለበት ግልጽ አድረጓል፡፡ እዚህ ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ ለአንዱ በልክ የተሰራው መጫሚያ በውሰት ወይም ያለልኩ ልሞክረው በሚል ሰው እግር ሲገባ መላላጡ አይቀሬ መሆኑ ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት መጫሚያ ሳይሆን ቡት ጫማ: ነበር የተደረገው:: ቡት ጫማ: የኢትዮጵያን ገጽታ ጨፍልቆ ጨፈላልቆ አበላሽቶታል፡፡ከባድ ጫማ አድርጎ መሬቱን ሁሉ በረገጠው ቁጥር መልኩን ሲያጠፋ ኖሮ አሁን አዲስ ተላባሽ ልሁን ማለት ለመመላለጥ ነውና የሚለወጠው ጫማው ነው ወይስ እግሩ? በጊዜ ብዛት ምናልባት ሃይለማርያምም በዚያ ጫማ ሳይሆን በተለመደው ሕዝባዊ የኢትዮጵያ ጫማ መራመድ ይለምድ ይሆናል፡፡እነዚያ ልካቸው የበዛበት ጫማዎች ጊዜያቸው ያለፈ የውስጥ ቆዳቸው (ሶላቸው) የተበሳሳ ናቸው፡፡ በነዚህ ጫማዎች አንድ ማይል ከተራመደ በኋላ ምናልባትም ኢትዮጵያዊያን በሙሉ አዲስ ጫማ እንደሚያስፈልጋቸው ይረዳ ይሆናል፡፡በዚህም ሃይለማርያምን የሚያደክመው ከፊት ለፊት ያለው ተራራ ሳይሆን በመጫሚያው ውስጥ የተሰገሰገው አሸዋ መሆኑን ይረዳል፡፡ ሁላችንም አዳዲስ ጫማ የምንፈልግበት ወቅት ሩቅ አይደለም፡፡ያ ጊዜ አሁን ነው፡፡ለረጂሙ የዴሞክራሲ፤ የሰብአዊ መብት ጉዞ የሚሆነን አዳዲስ ጫማ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ያስፈልገናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም የአውርዱልኝ ጫማ አያስፈልገውም፡፡ በራሱ ልክ የተሰራና ለረጂሙና አድካሚው መንገድ ምቹ የሆነ መጫሚያ ነው የሚያስፈልገው፡፡
ሃይለማርያም የተከሸነና ጥሩ ብቃት ያለው ንግግር አድርጓል፡፡ ቢሆንም ግን ለጥቅስ የሚበቁ ቃላት አልነበረባቸውም፤ አለያም ጥልቀትና ራዕይን የሚጠቁሙ መስመሮችም አላካተተምና ለመጪው ጊዜያት ሊታወስ አይችልም ሊጠቀስም ብቃት ያንሰዋል፡፡ ንግግሩ አንድ በፓርላማው ፊት ቀርቦ ቃለ መሃላ ለፈጸመ ሰው የሚበቃ ነው፡፡ ለረጂም ጊዜ ድባብ አጥልቶበት ለነበረው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ በተምሳሌትነት ቀርቦ ቃለመሃላ ፈጽሟል፡፡ ማንም በጣም አናሳ ቁጥር ካለው ብሔር እንዲህ ያለ ደረጃ ላይ ሊደርስ የሚችል ሰው ይወጣል ብሎ ያሰበ ያለ አይመስልም፡፡ በስሌትም ይሁን በአጋጣሚ፤ወይም በድንገት ባልታሰበ ሁኔታ ለዚህ የበቃው ሃይለማርያም ቃለመሃላም አደረገ አላደረገ ንግግር አደረገ አላደረገ ቢሮውን መረከቡ፤በኢትዮጵያ ምንም ይሁን መቼም የማይቀረውንና ማንም ሊያቆመውና ሕዝቡን አሻፈረኝ በማለት የማይገታውን የዴሞክራሲ ሽግግር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያበሰረ ነው፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ የሃይለማርያም ለዚህ መብቃት ማንም ኢትዮጵያዊ ወጣትና ክፉና ደጉን የለየ ዜጋ ከየትም ይሁን ከየት ዘር አካባ ሳይወስነው በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ከፍተኛ ስልጣን ደረጃ ለመውጣት መንገዱ በድርበቡ የተንገረበበና በቅርቡም በቂ ሆኖ እንደሚከፈት ተስፋ የሚያሳይ እውነታ ነው፡፡
የሃይለማርያምን የቃለማሃላ ዲስኩር እንደ ጨዋታ ለዋጭ አድርጎ ታሪክ ያስታውሰው አያስታውሰው እርግጠኛ አላውቅም፡፡ ታሪክ የሚያስታውሰው በንግገሩ ሳይሆን አለያም በቃለማሃላውም ሳይሆን ስልጣኑን ከተረከበና ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ ቢሮውን ከያዘ በኋላ በሚያደርገው እንቅስቃሴና በሚያስገኘው ውጤት ብቻ ነው፡፡ አሁን ግምት መስጠት ጊዜው አይደለም፡፡ቃላቶቹን በጥንቃቄ መምረጡን፤ እንደሃገር መሪ ሰክኖ መናገሩን፤ በተጨባጩ እውነታ ላይ በማትኮሩና እራሱንም እንደአንድ የሥራ ሰው አድርጎ መቅረቡን ወድጄለታለሁ፡፡ ኢትዮጵያን ወደ መሃከለኛ ገቢ ወዳላቸው ሃገሮች ለማድረስ ነው ጥረቴ ያለውን አደንቃለሁ፡፡ ችግሮች እንደሚኖሩና ግን እንቅስቃሴውን እንደማያቋርጥ መናገሩ እውነትነት ያለው ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር፤መሆን ፤ወይም አለመሆን
‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን የብቸኝነት ስራ ነው››፡በማለት ማጊ ታቸር የታላቋ ብሪታንያ ቀዳሚ እንስት ጠቅላይ ሚኒስትር ጽፋ ነበር፡፡ ለሃይለማርያም በቅድሚያ በቁጥር አነስተኛ ከሆነው በሔር ወጥቶ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን፤የብቸኛ ስራ ብቻ ሳይሆን በእጅጉም አስቸጋሪ ነው፡፡ ምን ይደረግ አንድ ሰው ሊያደርገው የግድ ነው፡፡ ለሃይለማርያም ምን ማድረግ እንዳለበት ቀድሞ የተቀረጸለት በመሆኑ ፈታኝ ፈተና ከአካባቢውም ከውስጥም፤በበለጠም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት የተነሳ ይደርስበታል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዊንስተን ቸርችል በዚያ የመከራ ወቅት ለሕዝቡ ያሰሙትን መልእክት በመጠቀስ ለሃይለማርያም መልካሙን ሁሉ እመኝለታለሁ፡፡
‹‹ከዚህ መንግሥት ጋር ለቆሙት እንዳልኩት ሁሉ ለቤቱም ያንኑ እደግመዋለሁ፡፡ከደም ከከባድ ሥራ እና ከላብ በስተቀር የማካፍለው የለኝም፡፡ ከፊት ለፊታችን እጅጉን ከባድና አስቸጋሪ የሆነ ፈተና አለብን፡፡ ከፊት ለፊታችን በርካታ ብዙ እጅግ ብዙ ትግልና መከራ ይጠብቀናል፡፡ዓላማችን ምንድን ነው ብላችሁ ትጠይቃላችሁ? ይህን በአንዲት ቃል እመልሰዋለሁ፡፡ዴሞክራሲ፡፡ በማንኛውም የከበደና ፈታኝ ክፍያ ዴሞክራሲ፡፡ከሽብርና ችግር መከራን በደል ምትክ፤ ዴሞክራሲ፡፡ መንገዱ የቱንም ያህል ረጂምና ፈታኝ ቢሆንም፤ዴሞክራሲ፡፡ ያለዴምክራሲ ኑሮ ሊታሰብ አይቻልምና!››
ኢትዮጵያ ኖራ የምታብበውና ወደ ዴሞክራሲ የምታደርገውም ሽግግር የማይቆም የማይቀለበስ፤ተፈጻሚነቱም የተረጋገጠ ነው!
በግል አስተያየቴም ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም አላስፈላጊ ቢመስልም አንድ ምክር ላካፍል እሻለሁ፡፡ትንሽ ፈገግ ይበሉ፤ ፈገግ ሲሉም መላ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን መላው ዓለም አብሮዎት ፈገግ ይላልና!
የተቶርገመው ጽሁፍ (translated from):
http://open.salon.com/blog/almariam/2012/09/23/ethiopia_a_new_prime_minister_in_a_new_year
(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::)
ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::
http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic
http://ethioforum.org/?cat=24
By Selam Beyene, PhD
The eulogy delivered in Ethiopia’s capital Addis Ababa by Susan Rice, the U.S. Ambassador to the United Nations, on the occasion of the funeral and mysterious death of dictator Meles Zenawi will probably go down in the annals of US diplomacy as one of the most inauspicious moments in which an opportunity was missed to assert the values of this great country.
To the dismay of the people of Ethiopia, the Ambassador failed to seize the moment to send an unwavering message of America’s commitment to democracy and the rule of law to a captive audience that included TPLF cadres and some of the most notorious African dictators, and instead chose to join the likes of Omar al-Bashir of Sudan in profiling a larger-than-life portrait of the deceased despot, who had ruled that poor African nation with an iron fist for over two decades.
In complete ignorance of her own State Department report on the abysmal human rights records of Zenawi, Rice gave credence to the outlandish fanfare the TPLF cadres had orchestrated, in a brazen imitation of the Kim of North Korea, to idolize the “Great Leader”, and added her voice to the ululation the inhabitants of Addis were dictated to wail under deplorable duress.
For a seasoned diplomat, that moment was a golden opportunity to reiterate to the cadres of the TPLF and other African dictators in attendance the timeless message of Barack Obama in which he perceptively counseled:
“…. there are some who advocate for democracy only when they’re out of power; once in power, they are ruthless in suppressing the rights of others. So no matter where it takes hold, government of the people and by the people sets a single standard for all who would hold power: You must maintain your power through consent, not coercion; you must respect the rights of minorities, and participate with a spirit of tolerance and compromise; you must place the interests of your people and the legitimate workings of the political process above your party. Without these ingredients, elections alone do not make true democracy. “
In point of fact, diplomats do not often get a second chance to redeem themselves from catastrophic missteps. Fortunately for Rice there is a second chance to make nice with the Ethiopian people and to discharge her diplomatic responsibilities with prudence by engaging the Ethiopian delegation on what is expected of good governance, when they come to New York to attend the U.N. General Assembly on September 28, 2012.
Recognizing Ethiopia is at a crossroads, the Ambassador should exercise discreet diplomacy and send a strong message to the EPRDF kingmakers that the time to play ethnic politics is over; and that leaders who do not play by the rule of law, who consider themselves above the law and who deny their people basic human rights and the freedom to choose their own government, will be disallowed membership to the community of civilized nations and denied access to much-needed loans and financial assistance.
More importantly, the Ambassador should take to heart and reinforce Barack Obama’s direction:
“… Governments that protect these rights are ultimately more stable, successful and secure. Suppressing ideas never succeeds in making them go away. America respects the right of all peaceful and law-abiding voices to be heard around the world, even if we disagree with them. And we will welcome all elected, peaceful governments– provided they govern with respect for all their people.”
Following the unexpected demise of Meles Zenawi, leaders of his ethnic-based party, the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF), and the umbrella front, the EPRDF, have on many occasions expressed their determination to continue his repressive policies by other means, without regard to the rights and aspirations of the people of Ethiopia for a free and all-inclusive representative government.
Many peace and freedom loving Ethiopians hope that the recent announcement by the regime’s propaganda chief, Bereket Simon, concerning the appointments of Hailemariam Dessalegn, a Southerner, as chairman and Demeke Mekonnen, an Amhara, as vice-chairman, of the EPRDF, is not a window-dressing move intended to enable the perpetuation of the ethnocentric dictatorship of the TPLF, that still is in full control of the vital economic, military and security institutions of the country.
Ethiopians at home and in the Diaspora anxiously pray that the EPRDF cadres are not succumbing to an age-old trick of dictators who appoint figureheads and hold sham elections in order to buy time to eliminate opponents and entrench themselves in power. They painfully remember all too well how Mengistu HaileMariam deceptively used this ruse when he placed Aman Andom, an Eritrean, and later Teferi Banti, an Oromo, as heads of state, before he conveniently eliminated them and imposed his brand of brutal dictatorship.
With the vast majority of the army generals still hailing from the minority Tigrai ethnic group, TPLF affiliated conglomerates controlling the vital economic activities in the country, journalists and other dissenting members of the society languishing in prison in thousands, major opposition groups completely shut out from the political process, and all relevant mediums of communication controlled by the ruling party, many genuine Ethiopians wait to be convinced that it is not a charade for the EPRDF cadres to pretend they have a change of heart in naming members of other ethnic groups to leadership positions.
The Ambassador and the US government have a historic opportunity to impress on the EPRDF cadres to establish a strong Ethiopia and leave a lasting legacy by abandoning the destructive ethnic policy of the late dictator, and opening the door for genuine dialogue and discourse on the way forward to building a better Ethiopia – an Ethiopia in which individual rights will be respected; everyone will have the right to life, liberty and the pursuit of happiness; and no individual or group will be above the law.
All internal and external players should understand the bitter fact that a minority member of a society cannot continue to rule, repress, exploit and deny the basic rights of the vast majority through force, repression, subterfuge and espionage. History has shown time and again, be it in Apartheid South Africa or Ian Smiths’ Rhodesia, that repression and exploitation by a minority ethnic group would inevitably fade away. Failure to understand this historical verity has drastic consequences; and as John F. Kennedy famously said: “Those who make peaceful evolution impossible will make violent revolution inevitable”.
In case the EPRDF leaders and their sponsors find it necessary to be reminded, the following are prudent measures, embraced by all freedom and peace loving Ethiopians, that should be implemented immediately as a demonstration of goodwill and readiness to change :
- Release, unconditionally, all political prisoners, including such journalists as Eskinder Nega.
- Annul all repressive laws promulgated in the name of “war on terror” but intended to harass, intimidate and incarcerate opposition groups and individuals.
- Invite all opposition groups inside and outside of Ethiopia who fight for the establishment of rule of law and democracy in Ethiopia, and form a consensus on a framework for establishing democracy in the country.
- Permit unfettered freedom of speech and expression.
- Desist from implementing irresponsible economic and fiscal policies, abandon the current campaign of land grabs, and foster a market economy where all citizens participate in business opportunities without regard to political, religious or ethnic affiliations.
- Diversify the monolithic army leadership through active recruitment of talents from all ethnic groups that constitute the Ethiopian mosaic.
(The writer can be reached at Selam Beyene, Ph.D. [email protected])
By Nicolas Beger | New Europe Online
On 25 July, the European Union adopted its strategic framework on human rights and democracy and appointed Stavros Lambrinidis its first special representative for human rights, seeking to “enhance the effectiveness and visibility of EU human rights policy”. It’s now time to translate policy into action. Ethiopia is a prime example, with its deteriorating human rights record. The recent death of former Prime Minister Meles Zenawi, whose leadership was characterised by cracking down on dissidents and dismantling the independent media, provides the EU with an excellent opportunity to change its policy on Ethiopia.
What should the EU do? First, it is inconsistent for it to prioritise the UN’s millennium development goals, which target poverty, while ignoring Ethiopia’s widespread violations of civil and political rights. At a joint hearing of the European Parliament’s Committee on Foreign Affairs and Subcommittee on Human Rights, Baroness Ashton’s External Action Service didn’t rise to the human rights challenge. Under Ethiopia’s late Prime Minister, this EU policy has completely failed to improve the country’s human rights record, which has taken a turn for the worse over the past seven years.
Restrictions on freedom of expression and association have severely limited Ethiopians’ ability to scrutinise their country’s human rights performance. A climate of silence and impunity are the norm. Torture, arbitrary detention and forced eviction are widespread and seriously under-reported. Those who commit the violations are rarely held to account and victims of violations seldom receive support.
In 2009 Ethiopia passed a charities and societies proclamation, which dramatically curbs human rights work. Its measures include preventing NGOs which work on these issues from receiving more than ten percent of their funding from abroad. It also establishes a government agency with broad powers over NGOs, including surveillance and direct involvement in their running.
The law has devastated human rights work, through practical obstacles and by exacerbating a climate of fear. Many fled the country when the law was passed. Those who continue to work on the issue have been forced to reduce their operations. There are now almost no domestic human rights organisations to monitor violations.
Freedom of expression in Ethiopia also suffered a sustained attack in Ethiopia last year. While members of the independent media have long been targeted, in 2011 and 2012 the pretext of ‘counter-terrorism’ has been used to silence dissenting media voices. Over this time, more than 100 journalists and members of the political opposition have been arrested and prosecuted for terrorism and other offences, including treason, and exercising their rights to freedom of expression and association. Their ‘offences’ included writing articles criticising the government and reporting on peaceful protests.
It’s time for the EU to act on its commitment to “place human rights at the centre of its relations with all third countries“. Ethiopia is a potential litmus test. It should protest more vocally against Ethiopia’s continuing human rights violations. It should urge the government to allow human rights organisations and independent journalists to defend human rights and remove restrictions on press freedom, freedom of expression, association and peaceful assembly. Ethiopians deserve strong advocates. And the EU must be one of them.
(http://www.neurope.eu)