Skip to content

Year: 2012

የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፖለቲካ የደሞክራሲ ጮራ ሰትወጣ

ከፕሮፌሰር  ዓለማየሁ  ገብረማርያም

ትርጉም  ከነጻነት ለሃገሬ

በድጋሚ እውነት፤ሃይልን ለተነፈጉ

ላለፉት በርካታ ዓመታት ስለሥልጣን ተጠቃሚዎች ዕውነትን ስናገር ነበር፡፡ የጦማሬ ገጼ መግቢያ መስመሩ ‹‹ለሰብአዊ መብት ተሟገት፡፡ ስለሥልጣን ተጠቃሚዎች እውነትን መስክር›› ነው የሚለው፡፡ ይህ ደሞ ልዩ ትርጉም ያለው፤ ጠንካራ ሞራልና ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ አላግባብ የሚጠቀሙበትን፤ ከመጠን በላይ ለሚተማመኑበት ኢሰብአዊ ድርጊት ማስገንዘቢያ የሆነ ስንኝ ነው፡፡ ለባለስልጣናት ነን ባዮች እውነትን መናገር፤ተናጋሪው በነዚህ ባለስልጣናት ላይ ስልጣናቸው የተዘረጋው በሃሰት ላይ መሆኑን ምስክርነቱን ያረጋግጣል፡፡ አልፎ አልፎም ሃቅን መናገር የስልጣን ሰለባ ለሆኑትም አስፈላጊ ነው፡፡ ስልጣን አልባዎች በምንም መልኩ ስልጣንን ሊያዛቡ የሚችሉበት ሁኔታ የለም፡፡ ስህተታቸው ግን የስልጣናቸውን እውነተኛ መብት አለማወቃቸው ነው፡፡ ሥልጣንን መከታ በማድረግ ግፍ የሚፈጽሙት ጉልበተኛ ሆነው ቢታዩም፤የስልጣን ተነፋጊዎች ደግሞ የሥልጣን ባለቤትነት መብት አላቸው፡፡ የሥልጣንን  እውነታነትና መብትን ነው የሥልጣን ተነፋጊዎች በትግላቸው ሂደት ሊጠቀሙበትና ለድል የሚያበቃቸውን መንገድ ሊከተሉ የሚገባቸው፡፡ ዶር ማርቲን ሉተር ኪንግ ይህን አስመልክተው፤ ‹‹ለጊዜው ትክክለኛነት ቢሸነፍም፤ ከሰይጣናዊና እኩይ ድል የበለጠ ነው›› ብለዋል፡፡

በጁን 2010፤ ‹‹እውነትን ስልጣን ለተነፈጉ መናገር›› የሚል ጦማር ጽፌ ነበር፡፡ በዚያም ጦማሬ ላይ በሜይ 2010፤ ቀን በቀን በገዢው ፓርቲ የተሰረቀውንና ድሌ 99.6 ነው በማለት ፓርላማውን የተቆጣጠረበትን የምርጫ ውጤት በተመለከተ ፤የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ የፖለቲካ መሽመድመድ የታየበትና አንዳችም ተግባር ያልተከወነበት ሂደት እንደነበር አሳስቤ ነበር፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በጥንቃቄ ትኩረት ሰጥተው ራሳቸውን ማስተካከያ መንገድ እንዲፈልጉም አሳስቤ ነበር፡፡ ‹ዓላማዬ ዲስኩር ለማድረግ ወይም ተቃዋሚዎችን ለመኮርኮም ሳይሆን ሃሳባችንን በማጽዳት ቆሻሻውን አውጥተን በመጣልና ወደ ዴሞክራሲ የሚያደርሰንን ረጂሙን መንገድ ቀና ለማድረግ ለመርዳት መሆኑን በውቅቱ አስረድቻለሁ፡፡ ‹‹እውነት ይጎዳል›› ቢባልም እኔ አልስማማበትም፡፡ ‹‹እውነት ለማገገም ይረዳል፤ ሃይል ይሰጣል፤ ታጋዮችንም ነጻ ያወጣል፡፡››

የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ሃይሎች በገዢው ፓርቲ እይታ

የ2010ን ምርጫ ተከትሎ እንደተቃዋሚ ፓሪቲዎች፤ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በገዢው ፓርቲ የሚደርስባቸውን ሰቆቃ በተመለከተ የገዢው አመራሮች አገኘን ስለሚሉት ድልና የምርጫ ውጤት ስለተቃዋሚ ፓርቲዎች (ስለሕዝቡ) ያላቸው ግንዛቤና አመለካከት ያስገርመኛል፡፡ ያን ጊዜም አሁን እንደማስበው፤ በገዢው ባለስልጣናት እይታ ተቃዋሚዎችን መመልከት፤ተቃዋሚዎችን በተለይም የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ያለውን ሁኔታ በማገናዘብ ሊከተሉት የሚገባውን መንገድ ያመላክታል ብዬ አምናለሁ፡፡

……..መለስ ተቃዋሚዎች እራሳቸውን ለክተው እንደማያውቁ ያውቃል፡፡ በሚገባ አጥነቷቸዋል፤ አስጠንቷቸዋልና ስራቸውን እንዴት እንደሚያከናውኑ (እንደማያከናውኑ) ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ በጥንቃቄ የተበጠሩት  ሕዝባዊ ዲስኩሮቹ ላይ ዘወትር የማይለወጥና መጥፎ አመለካከቱን ያሳያል፡፡ ተቃዋሚዎችን በችሎታቸውም በእወቀትም የበታቾቹ አድርጎ አስቀምጧቸዋልና በፈለገው ሰአትና ወቅት በአስተሳሰብ እንደሚበልጣቸው፤ በአመለካከት እንደሚያልፋቸው፤በተንኮል እንደማይደርሱበት፤ በእኩይ አስተሳሰብ እንደማይስተካከሉትና ባሻው ጊዜ ድል እንደሚያደርጋቸው ያምናል፡፡ በመለስ አስተሳሰብ፤እንቅስቃሴያቸው ድውይ፤የማያድጉና ያልበሰሉ፤ አድሮ ጥጃ፤ በመሆናቸው ሥልጣኑን የሚያሰጉት እንዳልሆኑ አረጋግጧል፡፡ በንግግሮቹ ሁሉ ተቃዋሚዎች ላይ ያለውን ንቀትና ጥላቻ ብቻ ነው የሚያንጸባርቀው፡፡ እድገታቸውን እንዳልጨረሱ ሕጻናት እለት ተእለት ክትትል የሚያስፈልጋቸውና ስርአት እንዲኖራቸውም የዲሲፕሊን ሽንቆጣ እንደሚያስፈልጋቸው ነው የሚደሰኩረው፡፡ ልክ ሕጻናትን እንደማታለል አይነት፤ ለአንዳንዶች፤ስኳር ያልሳቸዋል፤ በሥራ፤ በመኪና ችሮታ፤ በቤት ስጦታ፤ እና አፋቸውን ሊያፍን የሚያስችለውን ሁሉ ያደርግላቸዋል፡፡በዚህ ሊደልላቸው የማይችላቸውን ደሞ በመከታተልና ሲገቡ ሲወጡ በመተንኮስ፤በስለላ አባላት በማስጨነቅ በመጨረሻውም አስሮ ይፈርድባቸዋል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ተቃዋሚዎችን ያታልላቸዋል፤ይቀልድባቸዋል፡፡ ሽማግሌዎችን ለእርቅ በመላክ፤ ጊዜ እየገዛ የቆሙበትን መሰረት ያሳጣና፤ድርድር በሚል ዘዴ እያታለለ የራሱን ድል ይገነባል፡፡ የተለመደ አስማታዊ የሆነውን የተንኮል ጠበል ይረጭና ያንኑ ውጤት አልባ የሆነውን ጨዋታውን ጀምሮ በመጨረሻው እንቅልፍ አስወስዷቸው በድሉ ደወል ሲነቁ ማርፈዱን ይገነዘባሉ፡፡ በዚህም ተቃዋሚዎች የጨበጡትን ሁሉ ለቀው ተሸናፊ ሆነው ይሰለፋሉ::

በኢትዮጵያ ተቃዋሚው ሃይል ማነው?

ይህ ጥያቄ ምናልባትም አወዛጋቢና እንዲያውም ቁርጥ ያለ መልስም ሊገኝለት የማይችል ይሆናል፡፡ አሁን በሃገሪቱ ውስጥ የተጠናከረና ጉልበት ኖሮት የተዋቀረም ፓርቲ አለ ማለት ያስቸግራል፡፡ በዚህም የተነሳ ተቀናጅተውና ሃይላቸውንና አቋማቸውን አስተባብረው ገዢውን ፓርቲ ሊሞግቱና ገዢውን ፓርቲ ሊቋቋሙት ብቃት ያላቸው ፓርቲዎች ውህደት አይታይም፡፡ በምሁራንም የተጠናከረና የተዘጋጀ ተቃዋሚ የለም፡፡ ከሲቪል ማህበረሰቡም፤ከማህበራት፤የተዋቀረ የተቃዋሚ ፓርቲም የለም፡፡ የህብረተሰቡን ሃይል ያካተተም እንቅስቃሴም ሆነ ተቃዋሚ ሃይል የለም፡፡ በኢትዮጵያ  ያለው የፖለቲካ ተቃዋሚዎች ችግር ከ1960ዎቹ  ጀምሮ የኖረው ያአፍሪካ ያረጀው ችግር ነው፡፡ በአፍሪካ አንድ ሰው አንድ ፓርቲ በማለት በጋና በክዋሚ ንክሩማ ዘመን የተፈጠረ ሂደት ነው፡፡ ንክሩማ ተቃዋሚዎቹን፤አጠፋ፤ አጋዘ፤ ለፍርድ አቅርቦ ያለአግባብ አስፈረደባቸው፡፡ በዚህም ሂደት ውስጥ ዳኞች፤ የማህበራት መሪዎች፤ተካተዋል፡፡ ባለፈው ግማሽ ምዕተ ዓመት ውስጥ፤በኢትዮጵያ በጉልበት በስልጣን የወጡትን ገዢዎች የተቃወመ ሁሉ፤በፖለቲካው መድረክ መወቀስና መወገዝ ብቻ ሳይሆን፤ያለአግባብ በፍርድ ስም መሰቃየትና ከዚያም አልፎ ለሞት መዳረግ የታየበት ዘመን ነው፡፡ የኢትዮጵያን የተቃዋሚ ሃይላት ምንነትና ሁኔታ እንዲህ ነው ለማለት እቸገራለሁ፡፡ ከሜይ 2010 ምርጫ በኋላ ባቀረብኩት ጦማሬ ላይ አንስቼው እንደነበረው፤ ‹‹ያ ተስፋ የቆረጥንበት ተቃዋሚ ሃይል፤ የተከፋፈለ፤ያ በነጋ በመሸ ቁጥር በረባ ባልረባው ጉረሮ ለጉረሮ የሚተናነቀውና ዋናውን ሊታገሉት የሚገባውን ሃይል የዘነጉት ናቸው አሁንም ተቃዋሚ ናቸው የምንላቸው? ወይስ እነዚያ በደካማው የሚንቀሳቀሱትን  እንደአመቺነቱ ብቅ ጥልቅ የሚሉትን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፤ የስቪክ ማህበረሰቡ አሰባሳቢዎች፤ጋዜጠኞች፤ እና ሌሎቹን የሚዲያ ባለሙያዎችና ምሁራኑን ናቸው? ወይስ ለመሳርያ ትግል ታጥቀውና ቆርጠው የተነሱትንና ገዢውን ፓርቲና  አፋኝና ጨቋኝ ስርአቱን ለማጥፋት የተነሱትን ነናቸው ተቃዋሚ የምንላቸው?

ሁሉም ናቸው ወይስ ሁሉም አይደሉም?

በኢትዮጵያ ትክክለኛው የ‹‹ተቃዋሚዎች›› ተግባር ምንድን ነው?

የፖሊስ ጭቆናዊ አስተዳደር በተንሰራፋበት ሃገር ውስጥ በተቀቃዋሚነት መቆም እጅጉን አስቸጋሪና አደገኛም ነው፡፡ የሜይ 2005ቱን ምርጫ ተከትሎ ሁሉም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፤በርካታ የሲቪክ ማሕበረሰቡ አመራሮች፤የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፤የነጻው ፕሬስ አባላት፤ከያሉበት በመታደን ለሁለት ዓመታት ያህል ወህኒ ተጥለው ነበር፡፡ ላለፈው 6 ዓመታት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ማንኛውንም እንቅስቃሴ ተነፍገውና ታግደው፤በጠበበው የፖለቲካ መድረክ ውስጥ እንዲሹለከለኩ ብቻ  ነበር የተፈቀደላቸው፡፡ ከዚያ ባለፈ ግን ተቃዋሚ የሆኑትን የነጻው ጋዜጣ ባለቤቶችና አባሎቻቸው፤ ሌሊችም የተቃዋሚ ደጋፊዎችና አባላት እየተገፉና ከመስመር እንዲወጡ ጫና እየተደረገባቸው፤ በገዢው ጭቆናዊ አመራር እየተሰቃዩ፤እየታሰሩ፤ ከሕብረተሰቡ ጋር እንዳይገናኙ እየተደረገ፤እነዚህ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ተዳክመው፤ ሕዝባዊ ግንኙነታቸው እንዲቋረጥ አድርገውባቸው፤ ከገዢው ፓርቲ ጨቋኝ ስርአት የተለየ እንዳለና ተቃዋሚዎችም ለዚህ የቆሙ መሆናቸውን የሚያሳወቁበት መንገድ ባለመኖሩ ተዳክመዋል፡፡ በሌላም ወገን  አንዳንዶቹ ተቃዋሚዎች ተጠያቂነትን በመዘንጋት፤ግልጽነትን በመሸሽ ከአባሎቻቸው ጋር ተቃቅረዋል፡፡ ሌሎች ደግሞ ተቃዋሚ ነን እያሉ በውስጣቸው ግን ዴሞክራሲያዊነትን መቀበልና መተግበርን ስለሚፈሩት አቅቷቸዋል፡፡ ከዚያም አልፎ እራሰቸውን እንደሚቃወሙት ገዢ ፓርቲ ፈላጭ ቆራጭ በማድረግ የራሳቸውን የበላይነት ለማስጠበቅ ሲሉ በፓርቲው አባላት መሃል፤ ግጭትንና አለመግባባትን መቃቃርን ፈጥረዋል፡፡

በኢትዮጵያ ያሉትን ተቃዋሚዎች በምንም መልክ ይፈረጁ በምንም ፤በገዢው ፓርቲ አሸናፊ ነኝ አበባል የተጠቀሰው የ99.6 የምርጫ ውጤት ከ2005ቱ የተቃዋሚ ድርጅቶች አሸናፊነት ከተመዘገበው ሃገር አቀፍ ከፍተኛ ድል ጋር ሲተያይ እጅጉን የተለየና የውነትና የሃሰት ድል የታየበት የተቃዋሚዎች ብርታትም የተመሰከረበት ለመሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ካለፈው የ6 ዓመት ሁኔታ የተቃዋሚው ፓርቲ አባላት ሊማሩና ሊያውቁ የሚገበቸው ጉዳይ ቢኖር ዝም ብሎ “መቃወም መቃወም፤ደሞም መቃወም”፤ ለመቃወም ብቻ ሊሆን አይገባም፡፡ የተቃዋሚዎች ሁኔታ ገዢውን ፖርቲና ፖለቲካዊ ዝግመቱንና ያለፈበትነትን መቃወም ብቻ ሳይሆን፤ከዚያም ባሻገር ማሰብ ይገባቸዋል፡፡ዋናው ዓላማቸው ለሃገራችን ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን እስከመዘርጋት ሊጓዝ የግድ ነው፡፡ ዘወትራዊ ተግባራቸው ሳይሰለቹና ሳይደክሙ ሊያከሂዱት የሚገባ ትግላቸው ግልጽነትንና ተጠያቂነትን አበክረው መጠየቅና ለዚያ መታገል ሊሆን ይገባል፡፡ የገዢውን ፓርቲ እለታዊ እንቅስቃሴ በማጤን አግባብነት የሌለውን በመጠየቅ ለመስተካከሉ መቆም፤ መታገል፤ ሂስ ማድረግና መተቸት፤ ያንንም ይፋ ማድረግ ሲኖርባቸው ከገዢው ፓርቲ የተሻለ አመለካከትና መመርያም በማውጣት ለሕዝቡ እያቀረቡ ብቃታቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተቃዋሚዎች የገዢውን ፓርቲ ድክመት ብቻ እያነሱ ያንን መኮንን ብቻ ሳይሆን የነሱን የተሻለ ሃሳብም ማሰማት ይገባቸዋል፡፡

ገዢውን ፓርቲና አመራሮቹን በስድብ ክምር ማጥላላትን፤ጥርስን በመንከስ ማንኳሰስ የተቃዋሚውን ፓርቲ አስተሳሰብ ከፍተኛነት ከማቅለሉ ባሻገር ምንም ፋይዳ የለውም:: ተቃዋሚዎች ለተጠያቂነትና ለመልካም አስተዳደር ያላቸውን ሃሳብና ራዕይ ያዛንፍባቸዋል እንጂ የሚየስገኝላቸው ጠቀሜታም ሆነ ትርፍ የለውም፡፡ አብዛኛዎቹ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት በስልጣን ላይ ስላለው ገዢ ሃይል የሚጠቀሙበት ቋንቋ ቁጣ፤ፍርሃት፤የበታችነት ስሜትን የሚያሳይ፤ነው፡፡ ጥቂቶች ብቻ ናቸው እውነትን ይዘው በቆራጥነትና በሎጂክ የሚናገሩትና የሚሟገቱት፡፡ የገዢውን ፖሊሲዎች፤ፕሮግራሞችና ፕሮጄክቶች፤በሰከነ ጥናትና ግምገማ፤ በምርምር አቅርበው የሚናገሩና በምትኩም የተሸለ ጥናት የሚያቀርቡ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ለምሳሌ ገዢው ፓርቲ የሃገሪቱን ለም መሬቶች በሽርፍራፊ ዋጋ ለውጭ ዜጎች መሸጡን ይፋ ያወጡትና ሕዝቡ እንዲያውቅ ያደረጉት ሃገራዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሳይሆኑ መንግሥታዊ ያልሆኑ የዉጭ አገር ድርጅቶችና ተመራማሪዎች ናቸው፡፡ በተለያዩ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ግድቦች ሳቢያ የሚከሰተውን የአካባቢን ችግር በተመለከተም ጉዳዩን ይፋ ያደረጉት የውጭ አገር ተመራማሪዎች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያን የኤኮኖሚ ፖሊሲውን ግምገማ፤ ምንነትና ድክመቱንም በተመለከተ ይፋ እያወጡ ጥናታቸውን ያቀረቡት የውጪ አበዳሪ አካላት ሲሆን ጥቅምን ከመጠበቅ አኳያ ጥናታቸው አጠያያቂ ነውና እውነታው ይፋ የሚሆነው በታወቁ የሚዲያ አጥኚዎች ነው፡፡ ገዢውን ፓርቲ በተጨባጭና በሃቅ ላይ በተመሰረተ የፖሊስና የፕሮግራም አቀራረጹን መተቸት ባለመቻላቸው ተቃዋሚዎቹ በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነትን ወደማጣቱ ደርሰዋል፡፡ የሚያስፈልገው የቃላት ውግዘት አይደለም፡፡ የሚያስፈልገው ክሪቲካል የሆነ ሚዛን የሚያነሳ ግምገማና የገዢውን ፓርቲ የፕሮግራሙን፤ የፖሊሲውን መክሸፍ በተጨባጭ ማሳየትና ለዚያም ማስረጃዎችንና ጥናቶችን በተገቢው ማቅረብ ነው፡፡ በዚህም ነው ሕብረተሰቡ  ከገዢው ፈላጭ ቆርጭ የተሸለና የተለየ ራዕይ ከተቃዋሚዎች ሊጠብቅና ሊያልም የሚችለው፡፡

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለምርጫ ውድድር  ከመዘጋጀት ባሻገር  ብዙ ሊጫወቷቸው የምችሏቸው ሚናዎች አሏቸው፡፡ የአባሎቻችውን የደጋፊዎቻቸውንና የጠቅላላውን ሕብረተሰብ ንቃተ ሕሊና ማዳበርና ለትግሉም ማዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ፖሊሲያቸውን በሚገባ በማዳረስና በማስረዳት ሕብረተሰቡን ማስተማር አለባቸው፡፡ ክርክርና ውይይት በማዘጋጀት፤በአስፈላጊ ርእሶች ላይ በመነጋገርና ሕዝቡንም ተሳታፊ ማድረግ ሁኔታዎችን እያነሱ ችግሮችን በማንሳትና መፍትሔዎችን በመጠቆም የሃገሪቱን የወደፊት ራዕይ መጠቆም አለባቸው፡፡ ሁኔታዎችን በማስተካከል የዴሞክራሲ ባሕል የሚዳብርበትን መንገድ ቀያሽ ሊሆኑ ይገባል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስኬታማ መሆን የሚችሉት ለወጣቱና ለሴቶች አስፈላጊውን የአመራር ስልጠና ለመስጠት ማቀድና መተግበር ይኖርባቸዋል፡፡ የብዙዎቹ  ተቃዋሚ ድርጅቶች አመራሮች ሃምሳውን ዓመት የዘለሉ ሲሆኑ በአመራሩ ላይ ያሉትም የሴቶች ቁጥር አናሳ ነው፡፡ ‹‹ዕድሜ ቁጥር እንጂ ሌላ አይደለም›› በወጣቱና በዕድሜ ጠገብ ፖለቲካ መሃል ግልጽ የሆነ ልዩነት አለ፡፡ ወጣቱ ትውልድ ታላቅ የመነሳሳት ፍላጎት፤ ቅልጥፍና፤ቆራጥነት፤ በዓላማው ላይ መራመድን ይቀይሳል:: ያንንም ተግባራዊ ለማድረግ ፈጣንና ቆራጥ ነው፡፡ ያደርገዋል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከሚዲያውና ከሲቪል ማህበረሰቡ ጋር በመሆን ተቀናጅተው ወደ ሕዝቡ መድረስ አለባቸው፡፡

አልፎ አልፎም ተቃዋሚዎች በስልጣን ላይ ካለውም ሃይል ጋር በትክክለኛው ጉዳይ ላይ በመስማማት የሕብረተሰቡን ፍላጎት ማሟላት ይችላሉ፡፡ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በ2007 ላይ ሃሳባቸውን ሲገልጹ ‹‹ሃሳባቸው ኢትዮጵያን ከተዘፈቀችበት የችግር አረንቋ ማውጣት ብቻ ሳይሆን ›› በ “መልካም አስተዳደርና በዴሞክራሲ ግንባታም ላይ” ያተኮረ እንደነበር ተናግረዋል፡፡አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም የመለስን ራዕይ ተግባራዊ ለማድረግ መነሳታቸውንና ያም ዓላማቸው እንደሆነ በግላጭ ደጋግመው ቃል ገብተዋል፡፡ ሃይለማርያም የመለስን ራዕይ ለመተግበር ለመልካም አስተዳደርና ለዴሞክራሲ ግንባታ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ አብሮ መሰለፍ ጉዳት የለውም፡፡ መልካም አስተዳደርን ለመገንባት፤ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱም ሰፊ የዴሞክራሲ ግናባታም እንዲሰፍን በማድረጉ በኩል ተቃዋሚዎች ሃይለማርያምን ተጠያቂ በማድረግ መንቀሳቀስ አለባቸው፡፡

ምን አይነት ተቃዋሚ ነው አሁን የሚያስፈልገው?   የገዢው መንግስት መኖርና የበላይነት የተረጋገጠለት በኢትዮጵያ ያሉት ተቃዋሚ ሃይላት ስምምነት ማጣትና ዘወትር እርስ በርስ መናቆር የተነሳ ነው፡፡ ተቃዋሚዎች ተካፋፍለውና የጎሪጥ በመተያየት በየፊናቸው ባይረግጡ ኖሮ ገዢው ፓርቲ እንደዚህ ተጠናክሮ ሕጉን እንዳሻው በማውጣትና በመለወጥ ሊዘባነን ባልቻለ ነበር፡፡ ስለዚህ ታዲያ ምን ዓይነት ተቃዋሚ ነው የሚያስፈልገው?

ታማኝ ተቃዋሚ? በአንዳንድ የፓርላማ ስርአት ውስጥ “ታማኝ ተቃዋሚ” የሚባለው በህግ አውጨው አካል አስተዳደራዊ ተግባር ውስጥ ያልተካተቱትን ለማለት ነው፡፡ በተግባራዊው የዴሞክራሲያዊ ፓርላማ ስርአት ውስጥ ግን የገዢውን ፓርቲ ፕሮግራምና ፖሊሲ ያለአንዳች ፍርሃትና ይሉኝታ፤መሳቀቅ በነጻነት እየተከታተለ በትክክሉ በማስተግበር በኩል ከፍተኛውን ሚና የሚጫወት ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ግን ገዢው ፓርቲ የፓርላማውን ወነንበር 99.6ቱን ተቆጣጥሬያለሁ በሚልበት ሁኔታ ውስጥ ታማኝ ተቃዋሚ ጨርሶ ሊኖር አይችልም፡፡ የአንድ ብቸኛ ሰው ታማኝ ተቃዋሚ ሊኖር አይችልም፡፡

ጸጥተኛ ወይም የታፈነ ተቃዋሚ? በገዢው ክፍል ውስጥ ብዙ ዝም ያለ ወይም የታፈነ ተቃዋሚ አለ፡፡ የሚያስከትለውን ሁኔታ በመፍራት ብዙሃኑ የህብረተሰብ አባላት ለገዢው አካል ያላቸውን ተቃውሞ ከማንሳት ተቆጥበው አሉ፡፡ ገዢውን ፓርቲም ሆነ ወይም በውስጡ ያሉትን አመራሮች ላይ ተቃውሞ ቢያሰሙ ወይም አቃቂራቸውን ቢያመላክቱ ሥራቸውን ሊያጡ፤ከትምሕርት ገበታቸው ሊባረሩ፤የኢኮኖሚ ጫና ሊደርስባቸው አለያም ለባሰ መከራና ሰቆቃ ሊዳረጉ ይችላሉ፡፡ ሰዎች ገዢውን ፓርቲ እንቃወማለን በማለታቸው ብቻ ለእስር ይዳረጋሉ፡፡ በጣም በሚያስደንቅ ሁኔታ በቅርቡ አራት ሰዎች ‹‹እንኳንም መለስ ሞተ፤ ግልግል፤ በመሞቱ አላዘንም፤ መንግስት ሞቷል፤መንግስት የለም፤›› ብለው በአደባባይ በመናገራቸው ለእስር ተዳርገዋል:: (የነዚህን ሰዎች የክስ ሰነድ ለመመልከት (እዚህ ይጫኑ):: በጣም ብዙዎች በግላቸው ተቃዋሟቸውን የሚያሳዩ አሉ በአደባባይ ወጥቶ በይፋ ለመናገር ግን ክስንና እስራትን በመፍራት ታፍነዋል፡፡

ያልተደራጀ ተቃዋሚ? ማንዘራሽ፤ ያልተደራጀና ግልፍተኛ ተቃዋሚ በገዢው ፓርቲ ላይ አንዳችም ተጽእኖ ሊያሳድር አይችልም፡፡ የዚህን የመሰሉ ተቃዋሚ ምንም እቅድ ስለሌለውና ብቃቱም ስላመይኖረው ፖሊሲ የመንደፍም ችሎታ ስለማያገኝ ሕዝቡን አስተባብሮ ለማነሳሳት ጨርሶ ተቀባይነት የለውም::

የተከፋፈለ ተቃዋሚ?  የተከፋፈለ ተቃዋሚ ግልጋሎቱ ለገዢው ፓርቲ የመኖር ሕልውና መሆን ነው፡፡ የገዢው ፓርቲ ሃይልም ሆነ ተቃዋሚውን አሳንሶ ማየትና እንዳሻው መሆን ዋናው መሳርያና ምክንያት የተከፋፈለ ተቃዋሚ ነው፡፡

የተባበረ፤አቋሙ የተስተካከለ፤ዴሞክራሲያዊ ተቃዋሚ? ለኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ይሄ ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ ተቃዋሚ ታዲያ በመቻቻል በስምምነት በመግባባት ላይ መሰረቱን ያዋቀረ የተባበረና የብዙሃኑን ፍላጎትና ራዕይ መሰረት ያደረገ ተቃዋሚ ሃይል ነው፡፡ ሕብረቱ በሕዝቡ ፍላጎትና እምነት ላይ መሰረቱን ያደረገ ሲሆን ሂደቱ ለምርጫ ውድድር መዘጋጀት ብቻ ሳይሆን ሰፊ ምህዳር ያለው ፖሊሲ በመቅረጽ የሰፋ ውክልና ሊኖረው የሚችልና ለምርጫውም ቢሆን ሰፊ ድጋፍ የሚቸረው ሕዝባዊ ተቀባይነትና አመኔታ የተጣለበት አለኝታ ይሆናል፡፡ በሕብረት ውስጥ ሰፊ የሆነ ሃሳብና እቅድ የሚቀርብ በመሆኑ ይህንንም ወደ ተግባር ለመለወጥ የከረረ ውይይትና እሰጥ አገባ ተካሂዶበት ወደ ዴሞክራሲያዊ ውሳኔ ስለሚደርስ የአብዛኛውን ሕዝብ ፍላጎት የሚያካትት ዓላማቸውን የሚያስፈጽም በመሆኑ ሊፈጠር የሚችለውን አለመግባባት ሁሉ በውይይት ፈትቶ ለውሳኔ ይደርሳል፡፡ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲ እራሱን በሕብረት በሚያጣምር ፖሊሲ ላይ በማጠናከር መቆም ሲችልና በአንድነት አንድ ሆነው ሲንቀሳቀሱ ገዢውን ፓርቲና ፖሊሲዎቹን ለመሞገት ብቃት ይኖረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ተግባሩ ምን ሊሆን ይገባል? የ2010ን ምርጫ አስከትዬ የምክር ሃሳቤን ለኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች አቅርቤ ነበር::  በወቅቱ ምክሬ አንድም ተቀባይ ያገኘ አይመስለኝም፡፡ እኔ ደግሞ ያመንኩበትን በይሉኝታ ለመቀልበስ ዝግጁ አይደለሁም፤እና አሁንም ደግሜ ያንኑ ምክሬን በማጠናከር የፖለቲካ ጨዋታው መለወጡን እየጠቆምኩ የገዢው ፓርቲ ግን ተደጋጋሚ የማስመሰያ ቃላት ከመሰንዘር ባለፈ ምንም ለውጥ ያለሳዩ ናቸውና እንደነበሩት ለመቀጠል ነው ሃሳባቸው፡፡ ባልታሰበ መንገድ ሁኔታዎች መለወጥ ጀምረዋል:: ይህ ጅማሮም በፈጠነ ሂደት ላይ መጓዙን አጠናክሮ ከፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲ ለውጥ ጉዞውን መቀጠሉ ማቆሚያ የሌለው ነው፡፡ በምድር ላይ ምንም አይነት ሃይል ይህን የለውጥ ጅማሬ ሊያቆመው ጨርሶ አይችልም፡፡ በስላጣን ላይ ያሉት ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች ባሻቸው መንገድ ሊያከሽፉትና ለራሳቸው እንዲመች ለማድረግ ቢጥሩ ከፈላጭ ቆራጭ ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ለውጡን ማቆም ምኞት እንጂ ተግባራዊ ሊሆንላቸው አይችልም፡፡ አሁን የቀረውና መልስ የሚፈልገው አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፡፡ እገሌ እገሌ ተገሌ ሳይባል ሁሉም በገዢው ፓርቲ የተጨቆኑና የግፍ ሰለባ የሆኑ ተቃዋሚ ሃይላት ማሕበራት፤ የሰብአዊ መበት ተሟጋቾች፤ የዴሞክራሲ ናፋቂዎች፤ ሁሉም በአንድነት ከግፍ አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት በኢትዮጵያ ለሚደረገው ሂደት ምን ማድረግ ይጠበቅባቸዋል?

ከሕዝቡ ጋር ይቅር ለእግዚአብሔር ተባብሎ እርቅ መመስረት ፤ በ2005 በተካሄደው ምርጫ የተሳተፉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች ሁሉም ወደ ሕዝቡ ተመልሰው፤ ባለፈው  ተስፋውን፤ ሕልሙን፤መነሳሳቱን ያጨለሙበትን ሕዝብ ይቅርታ በመጠየቅ እርቅ ሊያደርጉ ተገቢ ነው፡፡ ለሕዝቡም ያለምንም ይሉኝታ ‹‹ባለፈው አሳዝነናችኋል፤ በዚያም በምር አዝነናል፤ ከናንተም ያጣነውን አመኔታና ድጋፍ ለማግኘት እንድንችል ጠንክረንና ካለፈው ተምረን እንክሳችኋለን›› ለማለት ብቃቱና ወኔው ሊኖረን የግድ ነው፡፡ ሕዝቡ ከተቃዋሚ መሪዎች ቅጥ ያለው ይቅርታ ይገባዋል፡፡ ይህንንም ቢያደርጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጨዋ፤ ይቅር ባይ፤መሃሪ፤ አዛኝ ነውና ይቅር ይላቸዋል፡፡

ካለፈው ስህተት መማር፤ ካለፈው ስህተታቸው መማር የማይችሉና ፍቃደኝነቱም የሌላቸው ያንኑ ያለፈውን ስህትታቸውን መድገማቸው አይቀሬ ነው፡፡ ባለፈው በተቃዋሚዎች በርካታ ስህተቶችና ወድቀቶች ተከናውነዋል፡፡ እነዚህ ስህተቶች ተነቅሰው ሊወጡ ይገባል፡፡ ከነዚህም ስህተቶች በመነሳት ላይደገሙ ትምህርት ሊወሰድባቸውና ዳግም እንዳይመጡም ሊገቱ ተገቢ ነው፡፡

የተቃዋሚውን ተቃዋሚዎች ማወቅ፤ የተቃዋሚዎች ተቃዋሚዎች ቸል ሊባሉ አይገባም፡፡ ሃይላቸው ከፋፍሎ በመግዛትና በብሔር በማለያየት ድብ ድብ ጨዋታ ነው፡፡ ተቃዋሚዎች ተሰባስበውና ተባብረው አንድ ቢሆኑባቸውና አንድ የጋራ አጀንዳ ቢኖራቸው ገዢዎቹ የተቃዋሚ ተቃዋሚዎች አቅመቢስ ልፍስፍስ ናቸው፡፡

ተጎጂነትን ማቆም፤ ከተቃዋሚዎች ጥቂቶቹ ‹‹የተጎጂነት አስተሳሰብ›› ይዘዋል፡፡ ማንም ሰው የተጎጂነት ስሜት ሲያድርበት ከተግባርና ከሃላፊነት ይርቃል፡፡ ስለታሰሩት ጋዜጠኞች በቅርቡ ለተደረገለት ቃለመጠይቅ በሰጠው ይፋ መግለጫ ላይ ሃይለማርያም መልስ ሰጥቶ ነበር፡፡ ለአሜሪካን ድምጽ በሰጠው ምላሽ ላይ በሃገሪቱ ያሉት የፖለቲካ እስረኞች ‹‹ሽብርተኞች›› ና ከተወገዙ ድርጅቶች ጋር ሁለት ባርሜጣ አድርገው የሚሰሩ ናቸው፡፡ አንደኛው ‹‹ሕጋዊ›› ሌላው ደግሞ ‹‹ሕገወጥ››፡፡ የፖለቲካውን መድረክ ለመክፈትና ለማረጋጋት ስላለው ሃሳብ ምንም አላለም፡፡ ያም ሆነ ይህ ሃይለማርያምም ሆነ ገዢው ፓርቲ ያሻቸውን ይበሉም፤አይበሉም ተቃዋሚዎች ሳይደክሙና ሳያስተጓጉሉ አበክረው ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ መጠየቃቸውን መቀጠል አለባቸው፡፡ ተጠያቂነት ማለትም ይሄው ነው፡፡ ተቃዋሚው ሁል ጊዜ ለትክክለኛው ጉዳይ መቆም አለበት፡፡ የፖለቲካ ሰዎችን ከወህኒ መልቀቅ ትክክል ነው፤  በወህኒ ማጎር ግን ስህተት ነው፡፡

በመንስኤዎችና በጉዳዮች ላይ የጋራ አጀንዳ ማዘጋጀት፤ በሁሉም ተቃዋሚዎች ተቀባይነት ያለው የዴሞክራሲ፤የሰብአዊ መብት፤የሕግ የበላይነት፤የሕዝቦች አንድነት፤የኢትዮጵያ ሕዝቦች ጥምረት ነው ማዕከሉ፡፡ እነዚህን ጉዳዮች ለማገዝና ለማራመድ የሚሆን አጀንዳ በጋራ መቅረጽ ምን ችግር አለው?

ከስምምነቱ ሳይርቁ ላለመስማማት መስማማት፤ ይሄን ‹‹ከኔ ሃሳብ ጋር መቶ በመቶ ካልተስማማህ ጠላቴ ነህ›› የሚለውን ጎጂ እምነት የተቃዋሚ አመራሮችና ደጋፊዎቻቸው፤ጨርሰው ማጥፋት አለባቸው፡፡ ከህሊናቸው ጋር ያሉ ሰዎች በሃሳብ ባይስማሙ ምንም ማለት አይደልም ጉዳትም የለውም፡፡ እነዚህ ደግሞ የዴሞክራሲ ባህሪ ናቸው፡፡ ተቃዋሚው በውስጡ የሃሳብ ልዩነትን ሳይቀበል የገዢውን ፓርቲ መቻቻልን አለመቀበል ሊያወግዝ ተገቢ ነው?

ግለሰብተኝነት ተመላኪነትን መከላከል፤ በኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ሂደት ውስጥ በጣም አስቸጋሪው ጉዳይ የሆነው የግለሰቦች ተመላኪነት ነው፡፡ በተለያየ ጊዜ በተደጋጋሚ ተቃዋሚው ጀግኖችን በመፍጠር እነሱን ከምንም በላይ አድርጎ በመመልከትና ለማመን በሚያስቸግር ሁኔታ እያሞካሸና እያሞገሳቸው ከማምለክ ባልተናነሰ መጠን ከበሬታ ሰጥቷቸዋል፡፡ ይህንን ባደረግን ቁጥር ደግሞ የወደፊት ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች እያሳደግን መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡

ዘወትር በቀናነት መንቀሳቀስ፤ ተቃዋሚዎችም ሆኑ አብረዋቸው የተሰለፉት ሁሉ በቀና መንገድ መጓዝን መልመድ አለባቸው፡፡ ግለሰባዊም ሆነ ድርጅታዊ ግንኙነታቸው በቀናነት የተመሰረተ ሊሆን ይገባል፡፡ የምንለውን መሆንና የምንሆነውን ማለት ይገባናል፡፡ የአንድ ሰው ግለኛ የበላይነት ከማያስፈልግ ደሴት ውስጥ ያስቀምጠናል::

በጥቅሉ እያሰብን፤ተግባራችን ወቅታዊ፤ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ የሚደረግ ትግል ምርጫን ማሸነፍ አለያም የስልጣን እርካብን ረግጦ ለሕዝባዊ ቢሮ መብቃት ብቻ አይደለም፡፡ ትግሉ ለታላላቅ ጉዳዮች ነው፡፡ ዘላቂነት ያለው ዴሞክራሲያዊ መሰረት ለመዘርጋት፤በኢትዮጵያ ሰብአዊነትን ማክበርና መጠበቅ እንዲሁም ተጠያቂነትንና የሕግን የበላይነት በአግባቡ አክብሮ ማስከበር፡፡ ይህንን እውነታ አምነን ከተቀበልንም ትግሉ አሁን ላለነው ለኛ ብቻ ሳይሆን፤ለሚመጣው ትውልድም ጭምር ነው፡፡ የምናደርገው ሁሉ ከኛ አልፎ ለተተኪዎቹ ልጅ ልጆቻችን የሚተላለፍ ኢትዮጵያችን ውድና የምትናፈቅ፤ ኖረንባት የማንጠግባት እንድትሆን በማድረግ ነው፡፡

ወጣቱ ትውልድ ለመሪነት እንዲበቃ ዕድሉን መስጠት፤  በተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ ያለን የእድሜ ባለጸጎች ብዙዎቻችን ለመቀበል የሚያስቸገረን  ጉዳይ አለ፡፡ ያም ችግራችን ቦታውን መልቀቅና ለወጣቱ ማስረከብን መማርና መቀበል አለብን፡፡ ለወጣቱ አመራሩን እንዲይዝ ዕድሉን እንስጠው፡፡ ወደድንም ጠላንም መጪው ዘመን የእነሱ ነው፡፡ ከኛ ስህተቶች እንዲማሩ ብናግዛቸውና ወደበለጠ አስተሳሰብና ዘዴ እንዲዘልቁ ብናደርግ በእጅጉ ተጠቃሚዎች እንሆናለን፡፡ በዓለም አቀፍ ተቀባይነትን ያገኘው ወጣቶችን የሚመለከት አንድ እውነታ ቢኖር፤ ከምንም በላይ ነጻነትን መውደዳቸው ነው፡፡ የመጀመርያዋ የሴት ፖለቲካ መሪ የሆነችው ብርቱካን ሚዴቅሳ ትለው እንደነበረው፤ የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑት መሪዎቻችን እኛ ተማሪዎቻቸውና ተረካቢዎቻቸው ለምንገነባት ‹‹የወደፊቷ ሃገር ኢትዮጵያ›› እነሱ ውሃውን ያቀብሉን እኛ ከዚያ ባሻገር ያለውን ሁሉ እያደረግን ሃገርን እንገንባ፡፡

ሃሳባችን እንደ ድል አድራጊ እንጂ እንደ ተሸናፊ አይሁን፤ ድል፤ ድል አድራጊዎች እንደሚያስቡት፤ ሽንፈትም ተሸናፊዎች እንደሚያስቡት አይደለም፡፡ በድል ውስጥ ሽንፈት እንዳለ ሁሉ በሽንፈት ውስጥም ድል ይገኛል፡፡ በ99.6 ምርጫውን ድል ያደረጉት በገጽታቸው ላይ የአሸናፊነት ምስል ይታይባቸዋል፡፡ የተገኘው ድል ግን በተንኮልና በቅሚያ፤ በእፍርታምነት የተገኘ መሆኑን አስረግጠን እናውቃለን፡፡ ዋናው ቁም ነገር ግን ተቃዋሚዎች እንደ አሸናፊ ስብስብ ወይም ተሸናፊ መመልከቱ ላይ ነው፡፡ አሸናፊዎች እንደአሸናፊ ያስባሉ ተሸናፊዎችም በተቃራኒው፡፡

የተቃዋሚው ጎራ እራሱን እንደገና መፍጠር አለበት፤ ገዢው ፓርቲ ምንም እንኳን የለውጥ ፍንጣቂም ባያሳይ ደጋግሞ ግን በየሕዝባዊ ንግግሩ፤እራሴን እንደገና እያደስኩ ነው ይላል፡፡ ያም ሆኖ ግን ‹‹ምንም የሚለወጥ የለም›› ማለታቸውን ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ጊዜ ካለው ሁኔታ አሁን ምንም ለውጥ አይኖርም ነው የሚሉት:: ተቃዋሚዎችም ቢሆኑ እራሳቸውን እንደገና መፍጠር አለባቸው፡፡ ለውጣቸውም እራሳቸውን ለዴሞክራሲያዊ እውነታ በማሰገዛት፤ሕዝቡንም በጠራ አመለካከት ላይ በማሰለፍ ሕብረትና አንድነት፤ መግባባትና መተሳሰብ ጠቀሜታው ታላቅ እንደሆነ ተገንዝቦ በማስገንዘብ፤ ድርጅታዊ ሃላፊነቱም በሕዝቡ ፈቃደኛነት ላይ የተገነባ መሆኑን በማረጋገጥና ሁል ጊዜም ዓላማቸው ለትክክለኛው ሁኔታ በመቆም በሃይል የሚደረገውንና አድራጊውንም ለመዋጋት መቆማቸውን በማረጋገጥ ላይ ሊሆን ይገባል፡፡

ተቃዋሚው ጨርሶ ተስፋ መቁረጥ አይገባውም፤ ሰር ዊንሰተን ቸርችል ‹‹ፈጽሞ እጃችሁን አትስጡ:: ፈጽሞ ፈጽሞ ፈጽሞ በምንም መልኩ ቢሆን::  በትልቅም ይሁን ትንሽ ፈጽሞ ፈጽሞ እጃችሁን አትስጡ!! ለክብርና ለመልካም ስሜት በታማኘነት ካልሆነ በስተቀር ፈጽሞ ፈጽሞ!! ሃይል አለኝ ለሚለው አትንበርከኩ:: ከአፍ እስከ ገደፉ ለታጠቀው ጠላትና አብረውት ሽር ጉድ ለሚሉት ሾካኮች ፈጽሞ እጅ አትስጡ!!››  የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ይህን ስልት ነው መከተል ያለባቸው እንጂ ለገዢው ፓርቲ አካኪ ዘራፍና የግፍ አፈና ሊሸነፉ አይገባም፡፡ ፈጽሞ ፈጽሞ ፈጽሞ!! ድል አድራጊዎች መንገዳቸው ይሄ ብቻ ነው፡፡

የተቶረገመው ጽሁፍ (translated from):

http://open.salon.com/blog/almariam/2012/09/30/ethiopias_opposition_at_the_dawn_of_democracy

(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::)

ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን  ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24

‘Person of the Year’ nomination

The year 2012 is coming to an end in about two months and so it is time for Ethiopian Review to start the process of selecting its Person of the Year. As a long running Ethiopian Review tradition, we take the Person of the Year selection seriously. Please share with us your choice with convincing argument. The selection criteria is: Who made the impost important contribution to the freedom and betterment of Ethiopian since the starting of 2012?

ESAT is back on air Ethiopia

Addis Ababa residents confirmed to Ethiopian Review that ESAT is back on air. ESAT also issued the following press release:

ESAT has finalizing testing and is back on air in Ethiopia through New Horn TV.

ESAT Management would like to announce that it has resumed its satellite TV program transmission to
Ethiopia and neighbouring countries thru New Horn TV.

For the past few days the signal has been successfully tested. The details are as follows:

NEW HORN TV Satellite
Eutelsat 7 West
Frequency: 10815 MHz
Polarity: Horizontal
Symbol Rate: 27.5 MB or 27500
FEC 5/6

ESAT Management would like to encourage all viewers and ESAT supporters all around the world to
send the information to friends and family in Ethiopia as well as provide feedback on the quality of the
transmission and reception. @ +15713051637.

ESAT Management
[email protected]

ENTC calls for public discussion on transitional government

The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) has presented a proposal to Ethiopian opposition groups to come together and form a transitional government. ENTC is also calling for public discussion on the process of transitioning Ethiopia to a multiparty democracy. The fact that Ethiopia has a new prime minister is a positive development, but no one should have an illusion that the ruling party, EPRDF, will open up the political space in the country, unless it is forced to do so. The creation of a transitional government can play a major role in forcing EPRDF to come to the negotiation table. Click here to read ENTC’s statement that was issued on Sunday.

Ethiopia’s Opposition at the Dawn of Democracy?

By Alemayehu G Mariam

demRespeaking Truth to the Powerless

For several years now, I have been “speaking truth to power”. In fact, the tag line for my blog page is “Defend Human Rights. Speak Truth to Power.” It is a special phrase which asserts a defiant moral and ethical position against those who abuse, misuse and overuse their powers. By speaking truth to power, the speaker bears witness against those whose power lies in lies. But speaking truth to the powerless is sometimes also necessary. The powerless have no power to abuse, but their fault lies in not knowing their true power. While the abusers of power have might, the powerless who are abused have the power of right. It is the power of right that the powerless must use in their struggle against the abusers of power in achieving their ultimate victory because, as Dr. Martin Luther King said, “Right, temporarily defeated, is stronger than evil triumphant.”

In June 2010, I wrote a weekly commentary entitled “Speaking Truth to the Powerless”.  I expressed deep concern over what I perceived to be manifest political paralysis and inaction in the Ethiopian opposition following the daylight theft of the May 2010 election in which the ruling party claimed to have won 99.6 percent of the seats in parliament. I urged the Ethiopian “opposition” to take a hard look at itself and take corrective action. I explained that  “my aim is not to lecture or to bash” but   merely to help “clean out the closet  so that we could begin afresh on the long walk to democracy. It is said that the ‘truth hurts’, but I disagree. I believe the truth heals, empowers and liberates its defenders.”

Ethiopia’s Opposition Through the Eyes of the Ruling Party

As opposition parties, journalists and dissidents faced unrelenting persecution by the ruling party and underwent apparent disarray following the 2010 election, I wondered what the party bosses of the ruling party really thought of the opposition (and the people) in making their outrageously absurd and audacious claim of total electoral victory. I thought then, as I do now, that looking at the “opposition” through the eyes of the ruling party bosses might give the opposition, particularly opposition parties, some insights into what courses of action they ought to take as the political situation evolves given recent changes:

… Zenawi knows the opposition like the opposition does not know itself. He has studied them and understands how they (do not) work. Careful analysis of his public statements on the opposition over the years suggests a rather unflattering view. He considers opposition leaders to be his intellectual inferiors; he can outwit, outthink, outsmart, outplay, outfox and outmaneuver them any day of the week. He believes they are dysfunctional, shiftless and inconsequential, and will never be able to pose a real challenge to his power. In his speeches and public comments, he shows nothing but contempt and hatred for them. At best, he sees them as wayward children who need constant supervision, discipline and punishment to keep them in line. Like children, he will offer some of them candy — jobs, cars, houses and whatever else it takes to buy their silence. Those he cannot buy, he will intimidate, place under continuous surveillance and persecute. Mostly, he tries to fool and trick the opposition. He will send “elders” to talk to them and lullaby them to sleep while he drags out “negotiations” to buy just enough time to pull the rug from underneath them. He casts a magical spell on them so that they forget he is the master of the zero-sum game (which means he always wins and his opposition always loses)…

Who is the “Opposition”?

Who is the Ethiopian “opposition”? That is an intriguing question for which there is probably not a definitive answer. There is certainly not a monolithic opposition in the form of a well-organized party. There is no strong and functional coalition of political parties that could effectively challenge both the power and ideology of the ruling party. There is not an opposition in the form of an organized vanguard of intellectuals.  There is not an opposition composed of an aggregation of civil society institutions including unions and religious institutions, rights advocates and dissident groups. There is not an opposition in the form of popular mass based political or social movements. The problems of “opposition politics” in Ethiopia is the age old  problem that has plagued African opposition politics following the “invention” of the one-man, one-party state in Africa by Kwame Nkrumah in Ghana in the early 1960s. Nkrumah crushed, suppressed and persecuted his opposition, including political parties, judges, union leaders, dissidents. Over the past one-half century, those who opposed the incumbent regimes in Ethiopia have been victims of not only legal and political restrictions but also all forms of persecution including imprisonments and extrajudicial killings.  I find it difficult to fully characterize or quantify the Ethiopian opposition. As I asked in my commentary after the May 2010 election: “Is the opposition that amorphous aggregation of weak, divided, squabbling, factionalized and fragmented parties and groups that are constantly at each other’s throats? Or is it the grumbling aggregation of human rights advocates, civic society organizers, journalists and other media professionals and academics? Or are the groups committed to armed struggle and toppling the dictatorship by force the opposition?

Or is it all or none of the above?

What is the Proper Role for the “Opposition” in the Ethiopia?

Playing the role of opposition in a police state is not only difficult but also extremely risky. Following the May 2005 election, nearly all of the opposition party leaders, numerous civic society leaders, human rights advocates and journalists were rounded up and jailed for nearly two years. Over the past six years, opposition parties have been denied any meaningful political space and their leaders, along with an ever growing number of journalists and dissidents have been harassed, intimidated, imprisoned, exiled or worse. But the opposition, particularly the opposition parties, have also been severely weakened and suffered erosion of public credibility by failing to develop a coherent set of policies, programs and ideology that are different from the ruling party’s. Some parties and party leaders have lacked accountability and transparency in their actions and omissions. Others have resisted internal democracy within their organizations. Still others have promoted a cult of leadership around a single individual or small group of individuals who themselves have manifested dictatorial tendencies and engaged in factional struggles within their organizations to consolidate their power.

Regardless of how one might define the “opposition” in Ethiopia, there is no question that the ruling party’s  claim of electoral victory of 99.6 percent stands in stark contrast to the fact that in 2005 opposition parties routed the ruling party’s candidates in landslide victories throughout the country. The principal lesson the Ethiopian “opposition” needs to learn from the experiences of the past six years is that the opposition’s role is not simply to “oppose, oppose and oppose” for the sake of opposing. The opposition’s role and duty goes well beyond simply opposing the ruling party and its policies. Their role goes to the heart of democratic governance of the country. Their principal role is to relentlessly demand accountability and transparency in governance. They should always question the actions and omissions of the ruling party in a principled and honest manner, challenge, analyze, criticize, dice and slice the ruling party’s policies, ideas and programs and offer better, different and stronger alternatives. It is not sufficient for the opposition to champion the failures of the ruling party and make broad claims that they can do better.

Heaping insults, gnashing teeth and denigrating the ruling party and its leaders not only erodes the superior  moral position of the opposition, it is also counterproductive  and distractive to the opposition in its role of promoting accountability and transparency in governance. Many in the opposition speak out against those in power in the language of anger, frustration, fear and loathing. Few seem to be prepared to challenge the rulers on the basis of cold hard facts and logic. It is rare to see the opposition undertake a thorough analysis and critique of the ruling party’s policies, programs and projects. That task if often done by foreigners who undertake specialized studies and investigations. For instance, the regime’s policy which allows predatory land grabs by international agro-businesses was exposed not by Ethiopia’s opposition but foreign NGOs and researchers. The disastrous environmental impact of the various hydroelectric dam projects in the country were revealed by foreign researchers, not the opposition. The bulk of the work documenting human rights violations in Ethiopia is done by the various international human rights organizations, not the opposition. Much of the economic analysis on Ethiopia is done either by the various international lending institutions whose review is highly questionable on conflict of interest grounds or economic commentators in the popular media. By failing to challenge the ruling party on substantive policy and programmatic grounds, the effectiveness and credibility of the opposition has been significantly diminished. What is needed is not verbal condemnation, demonization and teeth gnashing against those in power, but critical and systematic analysis of the failures of the regime, its programs, policies and laws followed by well-thought out proposals that offer real alternatives and hope of a better future to the people if the opposition were to hold the reins of power.

The opposition, particularly opposition political parties, can play many vital roles beyond simply preparing to run for elections. They can help build consensus and aggregate the interests of their members and the broader society. They can articulate their policy preferences and choices and educate the wider community. They can promote debate, dialogue and national conversations on issues, problems and the direction of the country. They are best positioned to build and institutionalize  a democratic culture. If opposition parties are to succeed, they must take action to provide leadership training opportunities to the youth and women. Many opposition party leaders are way past the age of fifty and few women are seen at top leadership levels. While “age is nothing but a number”, there is a distinct difference between youth and geriatric politics. The younger generation has greater enthusiasm, dynamism and commitment to carry on with the cause. Opposition parties also need to work closely with media and civil society institutions to reach out to the people.

Sometimes the opposition can also agree with those in power to do the right thing and serve the greater public interest. In 2007, the late Meles Zenawi expressed his “hope that [his] legacy” would be not only “sustained and accelerated development that would pull Ethiopia out of the massive deep poverty” but also “radical improvements in terms of good governance and democracy.” Prime Minster Hailemariam has vowed and pledged publicly numerous times to carry out Meles’ legacy. There is no harm in joining Hailemariam implement Meles’ legacy of “improving good governance and democracy.” The opposition should hold Hailemariam accountable for improving good governance by insisting on the release of political prisoners, repeal of repressive laws, opening up of political space and broader democratization.

What Kind of Opposition is Needed Today?

I believe the ruling party’s dominance and persistence is made possible in significant part by the shambolic (chaotic) state of Ethiopian opposition politics. In other words, if the opposition were not so divided and uncentered, the ruling party would have been far less successful in imposing its arbitrary rule. So, what kind of opposition is needed today?

Loyal Opposition? In some parliamentary systems of government, the term “loyal opposition” is used to describe opposition non-governing parties in the legislature. In a functioning democratic parliamentary system, it is the duty of the loyal opposition to challenge the policies and programs of the governing party without fear of harassment, intimidation or persecution. Obviously, there can be no “loyal opposition” in Ethiopia when the ruling party controls 99.6 percent of the seats in parliament. It is not possible to have a one-person loyal opposition.

Silent or Silenced Opposition? There is much silent and silenced opposition to the ruling class. The majority of the people are afraid to show their opposition to the regime because they are afraid of retaliation or retribution. If they criticize the ruling party or its leaders, they could lose their jobs, be dismissed from school, suffer economic harm or even serious persecution. People are jailed for simply saying they oppose the regime. In an incredible development recently, four individuals were criminally charged for stating in public, “Meles is dead. Good riddance. We are not sorry he is dead. The government is dead. There is no government.” (To see the official charging document, press here.)  There are many who privately express opposition but would not dare to make their views known because of fears of prosecution and persecution.

Disorganized Opposition? An opposition that is floundering, angry and disorganized is unlikely to pose a challenge to the ruling party. A disorganized opposition is unable to formulate viable and appealing policies or convert popular discontent into decisive political action. Neither is it able to convince and mobilize its base or expand its reach and influence.

Divided Opposition? A divided opposition is best guarantee for the dominance of the ruling party. The myth of the supremacy and invincibility of the ruling party and its leaders is built on the foundation of a divided opposition. The ruling regime survives and thrives using a strategy of divide and rule; and when the opposition itself is divided, it is easy for those in power to abuse, mock and denigrate them.

A United Principled Democratic Opposition? That is what Ethiopia needs today. Such an opposition is built on a foundation of the values of tolerance, cooperation and compromise.  A united opposition is consensus based and results in a coalition of divergent interests and groups. The coalition provides a  forum  to work together not only to compete in elections but also in formulating broad based policies, providing broader representation of the electorate and broader representation of the views and demands of the majority. Since a  wide consensus of opinion is necessary in coalitions, policies and actions will be debated and examined thoroughly before being presented to the public. Coalitions provide a basis for good governance because their decisions are made in the interests of a majority of the people. Coalitions may sometimes be fractious but the tendency to  build consensus often overcomes that impulse.  The Ethiopian opposition ought to organize around coalition politics to effectively challenge the ruling party and its policies.

What Is to Be Done by the Ethiopian Opposition?

Following the 2010 election, I offered unsolicited advice to Ethiopia’s opposition. It does not seem there were any takers at the time. But I am a tenacious and steadfast advocate who is not easily deterred. So, I offer the same advice again now that the political game has changed and despite the repetitious litany among the leaders of the regime that nothing has changed and things will continue as before. Things have changed fundamentally and will continue to change even more dramatically in the near future. That irreversible change is from dictatorship to democracy. There is no force on earth that can stop that change. No amount of bluster, swagger, bombast, hubris or imperiousness by those clinging to power can stop the change from dictatorship to democracy. There is only one question left to be answered: What is to be done by opposition parties and the aggregation of civic society and media institutions, human rights advocates, dissidents and others in Ethiopia’s transition from dictatorship to democracy?

Atonement and Reconciliation With the People:  All of the opposition political party leaders who participated in the 2005 election need to go back to the people and ask forgiveness for squandering their hopes, dreams and aspirations. They need to tell the people straight up, “We did let you down. We are deeply sorry. We promise to do our very best to earn back your trust and confidence.” The people deserve an unqualified public apology from opposition leaders. They will be forgiven because the Ethiopian people are decent, understanding and compassionate.

Learn From Past Mistakes: It is said that those who do not learn from past mistakes are doomed to repeat it. Many mistakes and blunders have been committed by opposition leaders in the past. These mistakes need to be  identified, studied and lessons drawn from them so that they will not be repeated again.

Understand the Opposition’s Opposition: The opposition’s opposition should not be underestimated. Their strength is in dividing and ruling and in playing the ethnic card. If the opposition unites and acts around a common agenda, they are powerless.

Stop Playing Victim: Some in the opposition manifest “victim mentality”. When one feels like a victim, one tends not to take action or responsibility. There is some recent criticism of Hailemariam over his public statements concerning the jailed journalists, political prisoners and other issues. Last week, he told the Voice of America that the political prisoners in the country are actually “terrorists” who “work with a violent organization” while “wearing two hats”, one “legal” and the other “illegal”. He gave no indication if he intends to open up the political space. The fact of the matter is that regardless of what Hailemariam and the ruling party say or do not say, the opposition must be relentless in demanding the release of all political prisoners and repeal of oppressive laws. That is what accountability is all about.  The opposition must always stand up for what is right. Releasing political prisoners is right; keeping them imprisoned is wrong.

Develop a Common Agenda in Support of Issues and Causes: The core issues democracy, freedom, human rights, the rule of law and the unity of the people and the physical integrity of the Ethiopian nation are shared by all opposition elements. Why not build collective agenda to advance and support these issues?

Agree to Disagree Without Being Disagreeable: Opposition leaders and supporters must abandon the destructive principle, “If you do not agree with me 100 percent, you are my enemy.” There is nothing wrong with reasonable minds disagreeing. Dissent and disagreement are essential conditions of democracy. If the opposition cannot tolerate dissent within itself, could it justifiably condemn those in power for intolerance?

Guard Against the Cult of Personality: One of the greatest weaknesses in the Ethiopian opposition has been the cult of personality. Time and again, the opposition has created idealized and heroic images of individuals as leaders, showered them with unquestioning flattery and praise and almost worshipped them. Let us remember that every time we do that we are grooming future dictators.

Always Act in Good Faith: Opposition leaders and others in the opposition must always strive to act in good faith and be forthright and direct in their personal and organizational relationships. We must mean what we say and say what we mean. Games of one-upmanship will keep us all stranded on an island of irrelevance.

Think GenerationallyAct Presently: The struggle for genuine democracy is not merely about winning  elections or getting into public office. The struggle is for great causes — establishing a durable democracy, protecting human rights and institutionalizing accountability and the rule of law in Ethiopia. If we believe this to be true, then the struggle is not about us, it is about the generations to come. What we do should always be guided by our desire to make Ethiopia better for our children and grandchildren.

Give Young People a Chance to Lead: There is a hard reality that most of us in the older generation in the opposition have been unable to face. That reality is that we need to learn to get out of the way. Let’s give the younger generation a chance to lead. After all, it is their future. We can be most useful if we help them learn from our mistakes and guide them to greater heights. If there is one thing universally true about young people, it is that they love freedom more than anything else. Let the older generation be water carriers for the young people who will be building the “future country of Ethiopia,” as Birtukan Midekssa, the first female political party leader in Ethiopia, used to say.

Think Like Winners, Not Victims: Victory is not what it seems for the victors, and defeat is not what it feels for the vanquished. There is defeat in victory and victory in defeat. Both victory and defeat are first and foremost states of mind. Those who won the election by a margin of 99.6 percent project an image of being victorious. But we know they have an empty victory secured by force and fraud. The real question is whether the opposition sees itself as a bunch of winners or losers. Winners think and act like winners, likewise for losers.

The Opposition Needs to Reinvent Itself: The ruling party, though its public statements, is trying to  reinvent itself as the same old repressive police state. They say “nothing will change” from the time of their former leader. The opposition also needs to reinvent itself by rededicating itself to democratic principles, articulating the peoples’ aspirations with greater clarity and cogency, creating democratic alliances, strengthening its position as voices of the people and by always standing up for right and against might.

The Opposition Must Never Give Up: Sir  Winston Churchill was right when he said: “Never give in–never, never, never, never, in nothing great or small, large or petty, never give in except to convictions of honor and good sense. Never yield to force; never yield to the apparently overwhelming might of the enemy.” This is a winning strategy the Ethiopian opposition should adopt and practice passionately!

 

 

Hailemariam is doing just fine

By Elias Kifle

What type of government Ethiopia will have is NOT up to Hailemariam, Bereket and their EPRDF alone. The opposition can and should have a big role if we put our acts together.

For me and many in the opposition camp, the premiership of Hailemariam is a big, a real positive change for Ethiopia. For the first time in 21 years, Ethiopia is being led by a man who doesn’t hate the country and her people. Meles was a hardcore anti-Ethiopia and every day he was in power, the fabric of our country was being torn to pieces. Meles was the enemy of Ethiopia, not just our political opponent. Hailemariam, on the other hand, is not an enemy. He is our political opponent who will not loosen EPRDF’s grip on power, but has no interest in destroying Ethiopia. It is up to the opposition parties now to get organized, united and pressure him and the EPRDF to accept a multiparty system in Ethiopia. Without getting organized, to expect Hailemariam to say or do any thing we want is foolishness.

If we want Ethiopia to transition to multiparty democracy, there are many things we can do. One of them that I and many of my comrades are working on is the creation of a transitional government. Support us, or come up with different ideas of your own. If not, please stop whining. Stop talking about Hailemariam said this and didn’t say that. Instead, ask what you are doing to help bring real change in Ethiopia.

Hailemariam is doing just fine right now. I would not advise him to say any thing that would antagonize TPLF. His first priority should be to survive, not say some thing we may like. We have to understand under what kind of dangerous environment he is operating. Let’s quit bitching about Hailemariam, and instead let’s get ourselves organized and come up with a strong alternative to EPRDF.

I would like to hear your comments.