Skip to content

Ethiopia

አሜሪካ ከጀግኖች አፍሪካውያን ጎን ትቆማለች ?

ከፕሮፌሰር  ዓለማየሁ  ገብረማርያም
ትርጉም  ከነጻነት ለሃገሬ


magl3

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

ታሪክ ከጀግኖች አፍሪካውያን  ጋር ከወገነ፤  አሜሪካስ  ለምን  አትወግንም ?

ፕሬዜዳንት ኦባማ አክራ፤ ጋናን በ2009 ሲጎበኙ ሁለት አስቸኳይና አስፈላጊ መልዕክቶችን አስተላልፈው ነበር፡፡ ‹‹ታሪክ ከጀግኖች አፍሪካውያን ጋር ወግኗል›› ሲሉ: ለአፍሪካ መሪዎችና ገዢዎች ደግሞ ጠበቅ ያለ መልክት ኣስተላፈው ነበር፡፡

………እንዳትሳሳቱ፡ ታሪክ ወገናዊነቱ ከጀግኖቹ አፍሪካውያን ጋር እንጂ በሥላጣን ላይ እራሳቸውን እንዳነገሱ ለማቆየት መፈንቅለ መንግሥት ከሚያካሂዱ ጋር አለያም ሕገ መንግሥታቸውን እንዳሻቸው ከሚለዋውጡት ጋር አይደለም፡፡ አፍሪካ የሚያስፈልጓት ጡንቻቸው የፈረጠሙ መሪዎች ሳይሆን የዳበሩ ተቋሞች እንጂ … የሕዝቦቻቸውን ፈቃድ ከማያከብሩት እጅጉን በበለጠ  ሕዝባቸውን የሚያከብሩ መንግሥታት የከፍተኛ ሃብታም፤ በጣም የተረጋጉ እና የበለጠ የተዋጣላቸው ይሆናሉ… የልማት መሰረቱ  መልካም አስተዳደር ነው፡፡ በበርካታ ቦታዎች እጅጉን ለረዘመ ብዙ ጊዜ ጎድሎ የነበረው ቅመም ይህ ነው፡፡ ይህ ነው የአፍሪካን እምቅ ችሎታ ሊያወጣው የሚችለው፡፡ ይህም ሃላፊነት በአፍሪካውያን ብቻ ነው ግቡን ሊመታ የሚችለው፡:

ለአፍሪካውያን ህዝቦች የላኩት መልእክት አነሳሽ ተስፋ ሰጪ፤አደፋፋሪ ነበር፡፡

መሪዎቻችሁን በተጠያቂነት ለመያዝና ለሕዝቡ አስፈላጊውን ግልጋሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለመገንባት ስልጣኑ አላችሁ፡፡ በመንደራችሁ አገልግሎት መስጠት ትችላላችሁ፤ አቅማችሁንና እውቀታችሁን አዲስ ሃብት መፍጠሪያ፤ ከሌላው ዓለም ጋር መገናኛም ልታደርጉት ትችላላችሁ:: ከመሰረቱ አንስታችሁ የእርስ በርስ ግጭትን፤ በሽታን በማጥፋት  ለውጥ ማምጣት ችላላችሁ፡፡ ያንን ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ አዎን ይቻላል! ምክንያቱም በዚህ ሰአት ታሪክ በመገስገስ ላይ ነውና፡፡

ፕሬዜዳንት ኦባማ በተጨማሪም የተከበረና የረጋ ቃል ለአፍሪካ ህዝቦች ገቡ፡

አሜሪካ በማንም ሕዝብ ላይ ምንኛውንም አይነት የመንግስት ስርአት ለመጫን ፍላጎት የላትም፡፡… ማድረግ የምንፈልገው፤ ትኩረታችንን በመልካም አስተዳደር ላይ፤ የስልጣንጣን  መባለግን በሚቆጣጠር  እና ተቃዋሚ ሃይላት ድምጻቸው እንዲሰማ በሚያደርግ፤ የሕግ የበላይነት ለሚያስከብር፤ የፍትሕ ስርአቱን አስተዳደር በእኩል መብት በሚያካፍል፤ የሕዝባዊ ማሕበራት ተሳትፎን በሚያረጋግጥ ፓርላማ ላይ፤ ወጣቱ ትውልድ በስፋት የሚሳተፍበትን በሙስና ላይ ግልጽ አቋም የሚይዝ፤ ከሕጉ ጋር የተያያዘ ቁጥጥር፤ አግልግሎቶችን በማፋጠን፤ ሃላፊነት ለሚሰማቸው ግለሰቦችና ተቋማት፤ ተጠያቂነትንና ግልጽነትን ለሚያረጋግጡ ሁሉ ድጋፋችንን መጨመር ነው እቅዳችን፡፡

አሁን ግልጽ በሆነው የፕሬዜዳንት ኦባማ ሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸው ላለፉት ጥቂት ዓመታት ያስተላለፍናቸውን አንዳንድ አስቸጋሪ ጥያቄዎችን ማንሳት ይኖርብናል፡፡ ከ2009 ይልቅ በ2012 በአፍሪካ የበዙ ባለ ጡንቻ መሪዎች አሉ? በየጎዳናውና በየወህኒ ቤቱ ጠንካራ የአፍሪካ ልጆች በ2009 ከነበረው በ2012  ያሉት ኣይበልጡም?  አፍሪካ በ2009 ከነበሯት ደካማ ተቋማት አሁን ያሉት ይበዛሉ? በ2009 ከነበሩት የሕዝባቸውን ፍቃድና ፍላጎት የሚያሟላ የአፍሪካ መሪዎች የበለጡ አሁን አሉ? በአፍሪካ በ2009 ከነበረው የእርስ በርስ ግጭት አሁን ያለው ያንሳል? አሁን አፍሪካ መልካም አስተዳደር አላት? በርካታ የተቃዋሚዎች ድምጽ ይሰማል?  ሕዝባዊ ተሳትፎስ በርክቷል? የወጣቱስ ተሳትፎ በ2009 ከነበረው አሁን ተሸሏል? የታሪክስ ሂደት ወደ ዴሞክራሲ፤ወደ ነጻነት፤ ሰብአዊ ምብት፤በመራመድ ላይ ነው? ወይስ አፍሪካ የኋሊት ፈላጭ ቆራጭነት ወደ ነገሰበት የጭለማው ዘመን፤ ወደ ማን አለብኝነትና የጭቆና አገዛዝ፤ አምባገነናዊ አስተዳደር እየተጓዘች ነው?

አሜሪካ ዛሬ ከጠንካራ አፍሪካውያን ጋር በጥንካሬ ቆማለች ወይስ ከነዚያ አምባገነን ገዢዎች ጋር ተቃቅፋ ኣልጋ ላይ ተጋድማለች?

ፕሬዜዳንት ኦባማ  ሲያነሳሱዋቸው የነበሩት  የአፍሪካ ጀግና ልጆችስ የት ገቡ?

እንደ አሜሪካው ስቴት ዲፓርትመንት የሰብአዊ መብት ትግበራ የ2011 (ሜይ 2012) ዘገባ እነዚያ ፕሬዜዳንት ኦባማ ያሏቸው በርካታ ‹‹ጠንካራ አፍሪካውያን›› አሁን በወህኒ ቤት፤ በመከራ መቀበል፤ በስቃይ በመገረፍ፤ በመለጎም፤ በሽሽት ላይ፤ በሞት በመቀጠፍ፤ አለያም በስጋት ማቅ ተሸፍነው፤ ወከባውን በመሸሽ፤ በዘፈቀደ በየቦታው መያዝን፤ ከፍርድ በፊት በወህኒ መማቀቅን፤ስቃይን፤ ዱላን፤ ኢሰብአዊ  መከራን፤ለሕይወት አስጊ የሆነውን እስራት፤ በንግግ ር ነጻነት መገደብን፤ የፕሬስ ነጻነትን ማጣት፤ ሕገ ወጥ ብርበራን፤ ይህና ሌሎችም መሰል ስቃዮች ናቸው የአፍሪካውያን የእለት ተእለት ሕይወት፡፡ የአፍሪካ ማሕበረሰብና ተቋማት በምግባረ ብልሹ ባለስልጣናት፤ በሙስና፤ ግልጽነት በመጥፋቱ፤በማያስፈልግና ወደኋላ ጎታች፤በሆነ ቢሮክራሲ ማነቆ ተይዘው፤ ማንኛውም ጉዳይ በገዢዎቹ መዋቅር ውስጥ ባሉትና ትዕዛዝ ተቀብለው በሚተነፍሱ፤ በፖለቲካ ቁጥጥር ስር በሆኑ የፍትህ መዋቅሮች፤የተባሉትን ብቻ እሺ በሚሉና በራሳቸው ህሊና በማይገዙና በማይመሩ የፓርላማ አባላት ተከበው በጭለማ ውስጥ በመዳከር ላይ ናቸው፡፡  የአፍሪካውያን ማሕበረሰብ በሚያለያይ በሽታ ተከትበው፤በዘር፤ በነገድ፤ በጎሳ፤ በመንደር፤በጾታ፤ በቋንቋ፤በሃይማኖት፤በባህል፤በወረዳ ተለያይተው ነው ያሉት፡፡

የሰብአዊ መብትን ከሚደፍሩ ሃገራት ሁሉ ድፍረቱ በእጅጉ የበዛባት ሃገር ኢትዮጵያ ነች፡፡ በሜይ 2010 ገዢው ፓርቲ በፓርላማ ካሉት 547 ወንበሮች 545ቱን (99.6%) መቀመጫዎችን ‹‹አሸነፈ››:: በዚያ የምርጫ ወቅት የሁዋይት ሀውስ መግለጫ ያሳየው ጉዳዩ ‹‹አሳሳቢ››  የሚል ነበር:-

ፍትሃዊና ነጻ ምርጫን ለማካሄድ ሁኔታው ከምርጫው ቀናት አስቀድሞም የተመቻቸና ትክክል አልነበረም፡፡ በቅርብ ዓመታት የኢትዮጵያ ገዢ መንግስት የፖለቲካወን ምህዳር በማጥበብ የተቃዋሚዎችን አካሄድም ለመስንከል በማስፈራራትና በማዋከብ፤የራሱን ሜዳ እያሰፋ በማመቻቸት የሲቪክ ማሕበረሰቡን በማግለል፤የነጻ መገናኛ ብዙሃንንም ተግባራቸውንና ክዋኔያቸውን በመቀነጣጠስና በማገድ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ደግሞ ሃሳብን በነጻ የመግለጽን ሂደት በእጅጉ የሚገድቡ ሲሆኑ ገዢው መንግስት እራሱ ከተቀበለውና ከፈረመው የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች ጋር ጨርሶ የሚጻረርና ተለዋዋጭ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብት ሁኔታ ‹‹ያሳስባል›› ከሚል በጨዋነት ከተሰነዘረው  የበለጠ ግንዛቤ የሚያስፈልገው ነው፡፡ድርጊቱ ቁጣን ሊያጭር ከድርገቱ ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ና ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች ጋር የሚዛመድ እንዲሆን ግፊት ያስፈልገዋል፡፡  በቅርቡ በወጣው ኢትዮጵያን የሚመለከተው የዩ ኤስ ስቴት ዲፓርትመንት የሰብአዊ መብት ዘገባ (ሜይ 2012) ‹‹ ከ100 የሚበልጡ የፖለቲካ ሰዎች፤ጋዜጠኞች፤እና የድረገጽ ተሳታፊዎች (በዓለም አቀፍ በተወገዘው የጸረሽብርተኝነት ሕግ) መንግስት የፕሬስን ነጻነት ገደበ፤የመያዝና የመጠቃት ፍርሃት ጋዜጠኞች እራሳቸውን እንዲቆጣጠሩ አስገድዷቸዋል፡፡ የእርዳታና የሰብአዊ ግልጋሎት ሰጪዎች  (CSO law)  አሁንም የጠነከረ እገዳ በማድረግ የማሕበረሰቡና የእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች እንቅስቃሴዎች ከመዳከም ወደ መቆም እየተጓዙ ነው፡፡በጣም አሳሳቢ የሚባሉት የሰብአዊ መብት ችግሮች፤ ድብደባን በደህንነት ሰዎች መሰቃየትን፤ወህኒ ማጎርን፤በጣም የተበላሸ የወህኒ ሁኔታን፤ የሴቶችን ሕብረተሰባዊ  ልዩነትን፤…… በጁንና ሴፕቴምበር (2011) የተካሄደው ሁለተኛው ዙር አፈናና እስር፤በርካታ ስመጥር ጋዜጠኞችን፤የፖለቲካ ተቃዋሚ አባላትን፤ንቁ የፖለቲካ ተሳታፊዎችን፤አንዱዓለም አራጌን የአንድነትለፍትሕና ለዴሞክራሲና የመድረክን ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ጭምር፤ታዋቂውን የድረገጽ ጸሃፊና ተሟጋች እስክንድር ነጋ፤ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ አባልን ናትናኤል መኮንንን ያካተተ ነው;;›››››››››

ካረን ጄ ሃንራሃን የዴሞክራሲ ቢሮ፤ የሰብአዊ መብትና የሌበር ዲፒዩቲ ምክትል  ጸሃፊ ለብሔራዊ አንዳውመንት በኦክቶበር 2012 ባደረጉት ንግግር

….በኢትዮጵያ ግብግብ ገጥሞናል፡፡ መሰረታዊው ጥየቄም ገዢው መንግስት በፖለቲካና ማሕበረሰቡ ተቋማት ላይ ጫናውን ሲያበዛና ገደቡ ልክ ሲያጣ፤ዴሞክራሲንና የሰብአዊ መብትን በአግባቡ ማራመድ የሚቻለው እንዴት ተብሎ ነው፡፡ ይህም በሲቪል ማሕበረሱ ላይ የሚደረግ ጫና፤የሜዲያዎች ነጻነት ማጣት፤በጸረ ሽብርተኝነት አዋጅ ሰበብ ጋዜጠኞችን የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት አፈናና ማሳደድ፤ለአእስር መዳርግ የሚያካትት ነው፡፡ ወደፊት መራመዱ ለመንግስትም ቢሆን የተቃዋሚዎችንና የሲቪል ሕበረሰቡን እድገት የሚያስከትል ይሆናል፡፡ኢትዮጵያዊያን ዜጎች መብቶቻቸውን ሙሉ በሙሉ ለመጠቀም ማስቻል ብቻ ሳይሆን የአሜሪካንና የኢትዮጵያ መንግስታት ሁለቱም የመረጋጋትና የልማት እድገትና ዋስትና ያገኛሉ፡፡

የአሜሪካን መሪዎች ምናልባትም ቀደም ሲሉ በቦታው ከነበሩትና ከፈላጭ ቆራጭና አምባገነኖች ተመሳሳይ ጥሪ የአሁኖቹ የአሜሪካ መሪዎች ሊማሩ ይችሉ ይሆናል፡፡ አንድ ወቅት ላይ ፕሬዜዳንት ትሩማን እንዳሉት፡‹‹ የተቃዋሚውን የመናገር ነጻነት ለማፈን የቆረጠ መንግስት የጉዞው አቅጣጫ አንድ ብቻ ነው፤ተደራራቢ ወደ ሆነና ለሁሉም ዜጎች የሽብርና ሁሉም በፍርሃት የሚኖርበት አካባቢ እንዲሆን በማድረግ አምቆ የመግዛት ስርአት፤›› ይህ ነው በኢትዮጵያ ያለው የማያከራክርና የማይካድ ሕይወትና ‹‹ጥሪ›› ‹‹አሳሳቢ›› የሚሉ ባዶ ቃላት አንዳችም ፋይዳ ሊናራቸው ሁኔታዎችን ሊቀይሩና የዜጎችን ሕይወት ሊለውጡ አይችሉም!

ዛሬ በአፍሪካ ያለው ያሜሪካ መምሪያ ብዙ ጉድለቶች ኣሉት

በዩ ኤስ ዲፓርትመንት ኦፍ ስቴት የአፍሪካ ጉዳዮች ሃላፊ የሆኑት ጆኒ ካርሰን አባባል  በአፍሪካ ውስጥ ሊያገለግሉ የሚችሉ ‹‹አምስት የአሜሪካንን ፍላጎት የሚያሟሉ ምሶዎች አሉ›› ይህም የሚያካትተው፤ (1) ዴሞክራሲውን የሚያግዙ እና የዴሞክራሲ መዋቅሮችን፤ ነጻ፤ ፍትሃዊና ግልጽ ምርጫዎችን የሚያጠናክሩ፤ (2) የአፍሪካን እድገት ልማት የሚያግዝ፤ (3) ግጭቶችን መከላከል፤ ማቅለል እና ውሳኔዎችን ማስፈጸም (4)ፕሬዜዳንታዊ ጅማሮዎችን እንደ ዓለም አቀፍ የጤና ጅማሮዎችን መደገፍ፤የወደፊቱን መመገብ፤ዓለም አቀፍ የዓየር ንብረትን ጅማሮዎችን መደገፍ (5) ከአፍሪካ ሃገርና ሕዝብ ጋር በሽግግር ሂደቶች ላይ እንደ አደንዛዥ እጽ ቁጥጥርን፤ ሕግ ወጥ የገንዘብ ዝውውርን፤ የሰዎች ሽያጭን›› ያካትታል:: እንደ ካርሰን አባባል ‹‹በአሁኑ ወቅት›› የዩ ኤስ ፖሊሲ በአፍሪካ በኮት ዲ ቩዋር በጊኒ፤በናይጄር፤መንግስታዊ ሰላማዊ ሽግግሮችን ረድቷል፡፡በናይጄርያ የተሳካ ምርጫ እንዲካሄድ አድርጓል፤የደቡብ ሱዳንን ነጻነት አረጋግጧል፡፡ በዴሞክራቲክ ኮንጎም የጾታንና የወሲባዊን ሁከቶችን ለማቆም በንቃት በመንቀሳቀስ ላይና በመካከለኛው አፍሪካ በመላው በመንቀሳቀስ ላይ ያለውን የሎርድ ሬዚስታነስ ሠራዊት ለማክሸፍም በጽናት በመንቀሳቀስ ላይ ነው፡፡ የወደፊቱን መመገብ የሚለው የዩ ኤስ ዓለም አቀፋዊ የምግብ ዋስትና ጅማሮ 12 የአፍሪካ ሃገራትን ያካትታል፡፡

የዩ ኤስ ዲፓርትመንት ኦፍ ስቴት የሰብአዊ መብት ዘገባ (ሜይ 2012)  የሂላሪ ክሊንተን ገለጻ፡ “እንደሃገር አስተዳደሪነቴ በዓለም ዙርያ ባደረግሁት ጉዞ የሰብአዊ መብትን ለማስከበርና የፍትሕና ስርአት ለማስከበር ሲሉ የራሳቸውን ሕይወት ለአደጋ ያጋለጡ በርካታ ሰዎች አጋጥመውኛል፤ በትልቁም ይሁን መጠኑ ባነሰ መልክ መንግስቶቻቸውን ተጠያቂ እንዲሆንና ለዓለም አቀፉ ሰብአዊ መብት ድንጋጌ ተገዢነት ይሞግታሉ፤ ቆራጥነታቸውና ድፍረታቸው ለሰላማዊ  መሻሻል አነሳሥ ነው፡፡ይህ ዘገባ ድፍረትና ጥንካሬያቸውን በሚገባ ዕውቅና በመስጠት እንደማሳሰቢያነትም ያገለግላል፡ ዩናይትድ ስቴትስ ሰብአዊ ክብርን ለማራመድ ከሚጥሩ ጋር አብሮ በመቆም በጥረታቸውም ላይ የዓለም ትኩረትና ድጋፍ ብርሃን እንዲያበራ ከማድረግ አንቆጠብም፡፡”

እነዚህ መጠነኛ ክንዋኔዎች ፕሬዜዳንት ኦባማ ከሰነዘሩዋቸው እነዚያ ግዙፍ፤ ተስፋ ሰጪ ቃላቶች ጋርና አስተዳደራቸው መልካም አስተዳደርንና ሰብአዊ መብትን በማስከበሩ ረገድ በአፍሪካ የተደረገው  ሲመዘን እጅጉን ተራርቀውና በማይመጣጠን ደረጃ ኣንሰው ይገኛሉ፡፡ አሁን ጊዜው ያለፈውን በማንሳት መወነጃጀያ፤ ጥርስ ማፋጪያ፤ ሆድ ማከኪያ፤ እና ጣት መቀሳሰርያ ግዜ አይደለም፡፡ ወደ ፕሬዜዳንታችን የትግል ጥሪ በመመልከትና ትኩረታችንን በማገናኘት ‹‹ወደፊት እንቀጥል›› በማለት የሞረሽ ጥሪ ማድረግ ነው የሚገባን፡፡

አሜሪካኖች በአብዛኛው የሚታወቁበት በቀጥታ አነጋገራቸው አካፋን አካፋ በማለታቸው ነው፡፡ እኔ ዘወትር በተራ አሜሪካውያንና በጥቂት ታላላቅ መሪዎቻቸው የማደንቅላቸው ባሕሪያቸው ነው፡፡የሚሉትን ያደርጋሉ የሚያደርጉትን ይላሉ፡፡ ‹‹ቀጥተኛ ተናጋሪው›› የሚባሉት ፕሬዜዳንት ሃሪ ኤስ ትሩማን ‹‹ለማንም መከራና ስቃይ አልመኝም፡፡ እውነቱን በምናገርበት ጊዜ እነሱ ግን መከራ ነው ይላሉ::›› ስለዚህም እኔም ትንሽ ቀጥተኛ ንግግር አደርገ ለሁ፡፡ ስለ ሰብአዊ መብት ጉራና እወጃ በቂ ያህል ሰምተናል፡፡ የአፍሪካን የሰብአዊ መብት ችግር ስለ መቅረፍ፤ በአፍሪካ መልካም አስተዳደርን ስለመገንባት ‹‹ስለ ግጥሚያው ጥሪ ወይም ስለፍላጎት ቅስቀሳው›› ‹‹ችግሮች‹› ‹‹አከራካሪ ጉዳይነት›› ስለሁሉም ርዕሶች በሚገባ እናውቃለን፡፡ በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊያንም አሜሪካ መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና ዴሞክራሲና ሰብአዊ መብትን ለማረጋገጥ ስላደረገውና ሳያደርገው በቸልታ ስለታለፈው፤ በቂ ጉርምርምታም፤ መነጫነጭ፤እንዲሁም ምሬት በበቂ አድምጠናል፡፡ ከእንግዲ ምንም የጎንዮሽ ንግግር አያስፈልግም ግልጡን በቀጥታ እና ቀጥተኛ የሆነ ድርጊት ማሳየት ብቻ ነው፡፡ በፕሬዜዳንት ኦባማ ሁለተኛ የስልጣን ዘመን፤በአፍሪካ መልካም አስተዳደርንና ሰብአዊ መብትን በሚገባ ተግባራዊ ለማድረግ ሁለት ምርጫዎች ብቻ ናቸው ያሉት፤ በቃን ብሎ በቁርጥ ‹‹ብድግ‹‹ : አለያም  እጅን  ኣጣጥፎ ኣፍን ለጉሞ ጭጭ በማለት ነው:: በሌላ አነጋገር: አሜሪካ ቆርጦ ከጠንካራዎቹ አፍሪካውያን ጋር በመቆም ትልቅነቱን ያስመሰክራል::  ካልሆነ ደግሞ ተሸመድምዶ በመድከም በ ምጽዋት፤በዓለም ባንክ፤ በአይ ኤም ኤፍ ገንዘብና ብድር በአፈሙዝ ሃይል ሥላጣን ይዘው ከሚገዙት ከጨካኞቹ ፈላጭ ቆራጭ የአፍሪካ መሪዎች ጋር ተቃቅፎ በውርደት መጋደም ነው፡፡

ጀግኖች  ኢትዮጵያውያን  መርጃው መንገድ፡ የት  ይጀመር?

በርካታ ልምድ ያካበቱት ኢትዮጵያዊያን ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ኤች አር 2003ን  (“Ethiopia Democracy and Accountability Act of 2007”) በሚገባ ያስታውሱታል፡፡ያ የሕግ ረቂቅ በኣመሪካን ምክር  ቤት ቀርቦ ነበር፡፡ (H.R. 4423 “Ethiopia Consolidation Act of 2005”) በቅድሚያ በኮንግሬስማን በኒው ጀርሲው ክሪስ ስሚዝ የአፍሪካን የውጭ ጉዳይ ንዑስ ኮሚቴ በሚመሩበት ጊዜ የቀረበ ነው፡፡(ረቂቁ ቆየት ብሎ  በውጭ ጉዳይ ኮሚቴ H.R. 4423 and H.R. 5680 ብሎ ተሰይሞ ነበር፡፡) በ2007 የኒው ጀርሲው ኮንግሬስማን ዶናልድ ፔይን የኮሚቴው ሰብሳቢ ሲሆኑ ጉዳዩን ተረክበው  የ85 የኮንግሬስ አባላትን ድጋፍ ለማግኘት ችለዋል፡፡ ረቂቁ በ2007 የቤቱን ድጋፍ ቢያገኝም ወደ ሴኔት ቀርቦ ድምጽ ሊያገኝ አድል ኣልነበረዉም፡፡ በረቂቁ ሕግ ውስጥ በርካታ ለመልካም አስተዳደር፤ ለተጠያቂነት፤ ስለሰብአዊ መብት መከበረና መረጋገጥ፤ ስለዴሞክራሲ፤ ስለፍትህ መከበርና ስለ ሕግ የበላይነት ስለነጣ የፍትህ ስርአት፤ ስለፍትህ ባለሙያዎች ስልጠና፤ስለምርጫ ቦርድ ነጻና ገለልተኛ መሆንና ሌሎችንም አስፈላጊ የሆኑ ሕዝባዊና ሃገራዊ ጉዳዮችን ያቀፈ ነበር፡፡

የኢትጵያን ‹‹ማግኒቲስኪ  ሕግ”  

ፕሬዜዳንት ኦባማ በ2009 በአክራ ባደረጉት ንግግር አፍሪካውያን ‹‹በሽታንና አለመግባባትን ሊያሸንፉ፤ከመሰረቱ ጀምሮ ወደ ላይ ለውጥ ማምጣት ይችላሉ፡፡ ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ ምክንያቱም በዚህ ሰአት ታሪክ እየገሰገሰ ነው›› አዎን ትችላላችሁ ብለው ለኣፍሪካኖች ተናግረው ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ሕግ በአሜሪካ ኮንግሬስ ማለፍ የሚገባው አሁን ነው፡፡በሁለቱም ወገኖች የፓርቲ አሰላለፍ በኩል ስምምነቱ አለና፡፡ በዴሞክራቶችም ሆነ በሪፓብሊካንስ የሰብአዊ መብት ጉዳይ ቅድሚያ የአየተሰተጠው ነዉ፡፡ የማግኒቲስኪ ሕግ ተብሎ ኣዲስ የዎጣው አመላከችና  ፈር ቀዳጅ የሆነ የሰብአዊ መብትን መደፈር የሚያስከብር ድንጋጌ ነው፡፡ይህን ሕግ በቅድሚያ ያነሱትና ያቀረቡት እንዲሁም በተዘዋዋሪ መልክ ድጋፋቸውንና በመጨረሻም ድምጻቸውን በመስጠት ያሳለፉት ሊመሰገኑ የሚገባቸው ናቸው፡፡ (* የለነገሩ ኦባማ አስተዳደር የንግዱን ሕግና የሰብአዊ መብቱን ድንጋጌ ማቀላቀል አያስፈልግም  የሚል አቋም ቢይዝም በመጨረሻው ላይ ግን ተስማምቷል::)

“የማግኒቲስኪ ሕግ”  በጣም ከፍተኛ የሆነ የሪፓብሊካኖች ድጋፍ ነበረው፡፡ የሪፓብሊካኑ አሪዞና ሴኔተር ጆን ማኬይን ‹‹ ስለማግኔቲስኪ ግፍና በደል ለመናገር፤ እንዲሁም ሌሎችም አሁን በሕይወት ያሉና በሩስያ ወህኒ ቤቶች አለ አግባብ በመሰቃየት ላይ ስላሉት መታገልና ለነጻነታቸው መቆም  አሜሪካ የሞራል ግዴታ አለበት››  በማለት አሳስበዋል፡፡ ‹‹ለቭላድሚር ፑቲንና ለሩስያ የሰርቆት መንግስት እንዲህ አይነቱ ኢሰብአዊ ድርጊትና የዜጎች በተለያየ መልኩ መብቶች መገፈፍና ለእስር መዳረግ፤ በወህኒ ስቃይ ማየትን እኛ አሜሪካውያን ልንቀበለው የሚገባን አለመሆኑን የምናሳውቅበት ነው፡፡ ይህ ሕግ ደግሞ ጸረ ሩስያ አይደለም፡፡ይልቅስ ሩስያን ደጋፊ ሕግ ነው:: እኔ ስለነሱ ግፍ ስተፈጸመባቸው እጨነቃለሁ፤በጸሎቴም አስባቸዋለሁ፡፡›› የአሪዞናው ሴኔተር ጆን ማኬን፤ ይህ ሕግ በሁሉም ሃገራት ላይ ተፈጻሚ ሊሆን ይገባል፡፡ የዴሞክራቲኩ ኒው ሃምፕሻየር ሴኔተር ጂያን ሻሂን አሜሪካ በሁሉም ቦታዎች ስለሰብአዊ  መብት ትኩረት ያደርጋል፤ ‹‹ስለ ሃገራቸው የሙስና ዝቅጠት ደፍረው ከሚናገሩት ጋር አብረን እንቆማለን፤ ይህ ሕግ በዓለም ላይ ላሉት ማግኒቲሰኪዎች ሁሉ ነው፡፡›› ሕጉ በዓለም አቀፍ ሁሉ እንደ ምሳሌ የሚወሰድ ነውና በየትም ቦታ እንደሚከበር እምነት አለኝ፡፡ ሁዋይት ሀውስም በዚህ ጉዳይ ላይ መግለጫ አውጥቶ ፕሬዜዳንቱ እንደሚፈርሙት ጠቁሟል፡፡  ‹‹አስተዳደሩ በሩስያ የዴሞክራሲ እውነታና የህግን የበላይነት ለማረጋገጥ ከሚሹና በዓለም አቀፍ ደረጃም እውን እንዲሆን ከሚጥሩ ከኮንግሬስና ከአጋሮቻችን ጋር መስራቱን ይቀጥላል›› ብለዋል ኦባማ::

ማግኒትኪ የሩስያ መሪዎች ሙስና ያጋለጠ ወጣት ጠበቃ ነበር፥ በዚህ ምክኒያት ባለስጣኖችጭ ኣስረው ኣሰቃይተው በስር ገደሉት:: የየሩስያ ፕሬዜዳንቱ ነጻ ካውንስል ለሲቪል ማሕበረሰብ ልማትና ሰብአዊ መብት ዋስትና በደረሰበት ማጣራት መሰረት፤ የማግኒቲስኪ ተይዞ መታሰር ከሕግ ውጪ የተፈጸመ መሆኑን አረጋግጧል፡፡  የፍርድ ቤቱ ሂደትም ማግኒቲስኪ በሩስያ ፌዴሬሽን ፍትህ በፍርድ ቤቱ፤ በአቃቤ ሕጉ፤ እንደተነፈገውና ምርመራ የተካሄደበትም በስርቆት በወነጀላቸውና ማንነታቸውን ይፋ ባወጣባቸው ግለሰቦች ነበር፡፡ በእስር ላይ በነበረበት ጊዜም አስፈላጊ የሆነውን የህክምና እርዳታ እንዳያገኝ ሆኖ በ8 የወህኒ ቤቱ ጠባቂዎች በመጨረሻው የሕይወቱ ሰአት በግፍ እንደተደበደበ ተገሎኣል፡፡ ድርጊቱንም ባለስላጣናቱ ከመካዳቸውም ባሻገር አንዳቸውም በድርጊታቸው የተነሳ ለጥያቄ እንኳን ወደ ፍርድ ቤት አልቀረቡም፡፡

ፍትሕን ተነፍገው በወህኒ በመሰቃየት ላይ ያሉ በርካታ ‹‹ኢትዮጵያዊያን ማግቲሰኪዎች›› አሉ፡፡ በ2005 በተካሄደው ምርጫ ወቅት ባዶ እጃቸውን ዴሞክራሲንና ሰብአዊ መብትን ለማስከበር ገዢው መንግስት እራሱ ያጸደቀውን ሕገ መንግስት እንዲከበር ለመጠየቅ ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉትን ንጹሃን 200 ዜጎች በፖሊስና በደህንነት አባላት ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በተሰጠ ቀጥታ ትዕዛዝ በጥይት ተደብድበው መሞታቸውና ከ800 የማያንሱት በጠና መቁሰላቸው ተረጋግጦ እያለ፤ ይ ህንንም  በቀጥታና በተዘዋዋሪ የፈጸሙት ይከበርልኝ የዜግነት ክብሬ አይደፈር በማለቱ የተፈጸመበት የሰብአዊ መብት መገርሰስ ዓልም ሊፋረደው የሚገባ እንጂ በሕግ ማውጣትና በማስፈራራት ብቻ ሊታለፍ የሚገባው ሊሆን አይገባም፡፡ የነዚህና የሌሎችም በግፍ የተገደሉና ለመከራ የተዳረጉ ኢትዮጵያዊያን ድምጽ ከያሉበት ከፍ ብሎ ይጣራልና ሰሚ ሊያጣ አይገባውም፡፡

በዩ ኤስ ኮንግሬስ ለውጥ ማየት ታላቅ ደስታ ነው፡፡ በሰብአዊ መብትና በመልካም አስተዳደር አዲስ አስተሳሰብና አመለካከት ያለ ይመስላል:: እነዚህ ሁነቶችም የዓለም አቀፉ ድንጋጌዎችና የሰለጠነ ሕብረተሰብ አንድ አካል ናቸው፡፡ ለምንግስት ብቻ ሊተው የሚገባም አይደለም››:: ሰብአዊ መብት የሁሉም ሰብአዊ ፍጡር የጋራ ጉዳይ ነው፡፡ለሩስያው ጀግና  ሰርጂ ማግኒቲስኪ ጥሩ የሆነው  ህግ ለኢትዮጵያዊያኖቹ ጀግኖች ለ 16 ዓመቱ መለስካቸው አላምነውም ፤ ለ22 ዓመቱ ሃድራ ኦስማንም፤፤ለ50 ዓመቷ እቴነሽ ይማምም፤ለ23 ዓመቱም ቴዎድሮስ ግደይ፤ ለ24 ዓመቱም ጋሻው ሙሉጌታ፤ለ21 ዓመቱም ሌቺሳ ፋታሳም…..  በግፍ የተገደሉ ሰማታት ተገቢ ነው፡፡

ፕሬዜዳንት ኦባማ በ2009 በአክራ ‹‹አሜሪካ ራዕዩን (መልካም አስተዳደርና ሰብአዊ መብት መከበርን) በቃላት ብቻ ሳይሆን የአፍሪካን አቅም ሊያጠናክር በሚገባ መልኩ የማሻሻልና ቅድሚያ የመስጠት ሃላፊነት አለበት፡፡ በሞስኮ የዓለምአቀፋዊ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች ሊከበሩ የሚገባበት ማስገደጃዎች ሊኖሩ እንደሚገባና እነዚህ ድንጋጌዎች መፋለስም እንደሌለባቸው በማሳሰብ ንግግር አድረጌያለሁ፡፡›› ብለው ነበር፡፡ ታሪክ በሂደት ላይ ነው! ‹‹የኢትዮጵየዊያን ማግኒቲስኪ ሕግ›› ሊኖረን ተገቢ ነው፡፡ይህም ከወዳጆቻችንና አጋሮችቻን በምናገኘው ትንሽ ድጋፍ እውን ይሆናል!

በትክክለኛው የአፍሪካ የሰብአዊ መብት ጎን መቆም ማለት በትክክለኛው የታሪክ ጎን መቆም ማለት ነው፡፡

ፕሮፌስር ዓለማየሁ ገብረማርያም በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሳን በርናርዲኆ የፖሊቲካ ሳይንስ መምሀርና የህግ ጠበቃ ናችው።

*የተቶረገመው ጽሁፍ (translated from):

http://open.salon.com/blog/almariam/2012/12/15/will_the_us_stand_by_the_side_of_brave_africans

(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::) ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን  ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24

 

16 European Parliament members sent a letter to PM Hailemairma Desalegn asking him to free Eskinder Nega

Today, 16 members of the European Parliament issued a public letter to Ethiopian Prime Minster Hailemariam Desalegn expressing their grave concern regarding the continued detention of imprisoned journalist and blogger Eskinder Nega.

Arrested in 2011 and detained without access to an attorney for nearly two months, Mr. Nega was sentenced to 18 years in prison under the country’s broad 2009 Anti-Terrorism Proclamation on July 13, 2012. Mr. Nega’s arrest and prosecution came after he wrote online articles and spoke publicly about the possibility of an Arab Spring-like movement taking place in Ethiopia. After his sentencing, the government initiated proceedings to seize his assets, including the home still used by his wife and young son. An appeal hearing in the case is scheduled for Wednesday, December 19th.

The letter, notes that the Ethiopian government has an obligation to uphold the right to free expression and reminds the newly appointed Prime Minister that he has “the unique opportunity to lead Ethiopia forward on human rights and bring the country fully within the community of nations.” The letter closes by urging the Prime Minister to take all measures within his power “to facilitate the immediate and unconditional release of Mr. Nega.”

“This is an important recognition by members of the European Parliament from across the political spectrum that the right to free expression is universal and must be respected by the Ethiopian government,” said Freedom Now Executive Director Maran Turner. “Mr. Nega has been wrongfully detained in Ethiopia in violation of his right to freedom of expression, and he must be released.”

The text of the letter is copied below and a full PDF of the letter can be found at the below link. Freedom Now, a legal advocacy organization that represents prisoners of conscience around the world, serves as international pro bono counsel to Mr. Nega.

Source: Freedom Now

###

Dear Prime Minister Desalegn,

We write to express our grave concern regarding the continued detention of independent Ethiopian journalist and blogger Eskinder Nega and urge you to facilitate his immediate release.

Mr. Nega, a longtime publisher and journalist, was arrested in 2011 and charged under the country’s 2009 Anti-Terror Proclamation after he wrote and spoke publicly about the Arab-Spring movements then unfolding across the Middle East and North Africa. Although clearly sympathetic, Mr. Nega consistently emphasized that any similar movements in Ethiopia must remain peaceful. Despite this, the government of your predecessor Prime Minister Meles Zenawi arrested Mr. Nega, held him without access to family for nearly one month and without access to an attorney for nearly two months, and ultimately sentenced him to 18 years in prison. Even now, reports indicate that proceedings are underway to seize Mr. Nega’s home, where his wife and young son continue to live.

Unfortunately, Mr. Nega is not alone—journalists Woubshet Taye and Reyot Alemu have also received long prison sentences on terror charges. In response to your government’s use of the 2009 Anti-Terror Proclamation against journalists and opposition leaders, the African Commission on Human and Peoples’ Rights, the United Nations High Commissioner for Human Rights, and five United Nations Special Rapporteurs—including the Special Rapporteur on counter-terrorism and human rights—have all expressed alarm at this worrying trend. As some have noted, the use of vague anti-terror legislation to silence legitimate expression threatens to seriously undermine the credibility of efforts to address real security threats to the region.

It is our understanding that appeal proceedings in Mr. Nega’s case are ongoing and we respect your need to allow the judicial process to continue. However, it is also your government’s obligation to respect the right to freedom of expression as established under customary international law and codified in Article 19 of the International Covenant on Civil and Political Rights, to which Ethiopia is a party.

You now have the unique opportunity to lead Ethiopia forward on human rights and bring the country fully within the community of nations. As such, we urge you to take all measures within your power to facilitate the immediate and unconditional release of Mr. Nega.

Sincerely,

Alexander Graf Lambsdorff
Ana Gomes
Charles Tannock
Eduard Kukan
Eija-Riitta Korhola
Emilio Menendez del Valle
Fiona Hall
Frank Engel
Kinga Gál
Laima Liucija Andrikienė
Maria Da Graça Carvalho
Mariya Gabriel

96 Ethiopians arrested in northern Tanzania

GLOBAL TIMES — Tanzanian authorities on Monday said that 96 Ethiopians who were found hiding in villages near Kenya boarder.

According to immigration officers, the Ethiopians were arrested on Sunday morning when they were found in a lorry in an area located between Ngeriani and Tingatinga villages in the district waiting to cross Tanzania to one of the southern African countries.

Arusha Regional Immigration Officer Daniel Namomba said the Ethiopians were expected to be taken to court on Monday after long interrogations with immigration officers at Namanga Immigration border post.

He said four Tanzanians, who facilitated the “dirty game,” were also arrested and taken to court to face charges leveled against them.

This occurred few days after 13 Ethiopians, en-route to South Africa, were arrested in Arusha while hiding in a house owned by a taxi driver.

Namomba explained the arrest of the aliens has been possible through collaboration with local Samaritans, immigration officers and wildlife rangers in the area.

He said the problem is getting more complicated as stowaways use illegal routes popularly known as “panya route” to get into Tanzania.

“These people were on transit to one of the southern African countries on the way to European countries and the United States,” he said.

The immigrants were found in a lorry with registration numbers T264 APV, owned by someone identified as Said Augustino Mrembe, a Kilimanjaro-based resident, he said, adding all of them were in good conditions.

The recent Southern African Development Community (SADC) report showed Tanzania is a gate way for illegal immigrants wishing to go to southern African countries especially South Africa.

ከዳር ቆሞ ለዉጥን መጠበቅ የህልም እንጀራ

ፍስሀ እሸቱ (ዶ/ር)

በሀገራችን ያለዉን ሁኔታ ስንመለከተዉ በጥቂት ቃላት ማጠቃለል የቻላል። ይህም ከድጡ ወደ ማጡ የሚለዉ በጥሩ ሁኔታ የሚገልጸዉ ይመስለኛል። አበዉ ጉልቻ ቢለዋወጥ እንደሚሉ አፈናዉ፤ ስለላዉ፤ እስሩ፤ ግድያዉ፤ ስደቱ፤ ዘረፋዉና፤ ማናለብኝነቱ ሳይቋረጥ ቀጥሏል። አዲሱ ጠቅላይ ሚንስትርና አጋሮቻቸዉም ደግመዉ ደጋግመዉ አስረግጠዉ እንደተናገሩት ለዉጥ የሚባል ነገር እንደማይታሰብና የነበረዉ ሁኔታ ባለበት እንደሚቀጥል ነዉ። ከዚህ አንጻር የለዉጥ የተስፋ ጭላንጭል እንደሌለ በወሬ ብቻ ሳይሆን በተግባራቸዉም አሳይተዉናል። ምንም መራር ቢሆንም እዉነታዉ ግን ስርአቱ መሪዉን ቢያጣ እንኳን፤ በአላማ፤ በአቅም፤ በድርጅትና፤ በስነልቦና፤ ፍጹም የበላይነቱን ተጎናጽፎ ይገኛል።
አበዉ እንደሚሉት አቅሙን የማያዉቅ ሞቱን አፋጠነ እንደሚሉት በተቃዋሚዉ ባንጻሩ የሚታዉ ደሞ፡
1ኛ. እኛ ከወኔ ወኔ የለን፤ መስእዋትነት ለመክፈል ዝግጁነት የለንም
2ኛ. ከአንድነት አንድነት የለን
3ኛ. ከአቅም አቅም የለን
4ኛ. ነጻነትን በምጽዋት ለማግኘት እንፈልጋለን (በዉጭ ሃይሎች)፤ ሌሎች በታገሉትና መስእዋትነት በከፈሉት ተጠቃሚ መሆን እንፈልጋለን
5ኛ. የስርአቱ አራማጆች ወድቆ መነሳትን ሲችሉበት እኛ ግን የወደቅንበት ቀርተናል፤ ከዚህ በፊት በደረሱብን ሽንፈቶች ለምሳሌ በቅንጅት ሽንፈት ተስፋ ቆርጠን ተበታትነናል
6ኛ. ጠላታችን ማን እንደሆነ ማወቅ ተስኖናል፤ ከስርአቱ ይልቅ እርስ በራሳችን ጦር መማዘዙን መርጠናል
7ኛ. በጭንቅላታችን ሳይሆን በስሜታዊነት የምንመራ ሆነናል፤ በአላማ ሳይሆን በጥላቻ ምንመራ ሆነናል
8ኛ. የረዥም ግዜ ዉጤት ሳይሆን አጭር ዉጤት እንፈልጋለን፤ በዚህም ምክንያት ቶሎ ተስፋ እንቆርጣለን
9ኛ. ሁሉም ፈላስፋ፤ አዋቂ፤ መፍትሄ ሰጪ ሆኖ፤ መደማመጥ ጠፍቷል፤ ሁሉም አዋቂ፤ ተናጋሪ፤ ሆኖ የሚታገለዉ ግን ጥቂት ሆኗል – ወሬ ወሬ ወሬ -ሀሜት ሀሜት ሀሜት – ኩነና ኩነና ኩነና – ተናጋኔ ተናጋሪ ተናጋሪ – አድራጊ ጠፋ (የኢንተርኔት፡ ፓልቶክና ሬድዮ፤ ስብሰባ ታጋዮች ሆነናል)
10ኛ. በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አብዛኛዉ ህብረተሰብ ያለዉን ስርአት በአያገባኝም ወይም በፍራቻ ወይንም በጥቅም ተቀብሎ አሜን ብሌ መገዛቱን መርጧል
11ኛ. ከዚህ በፊት በነበሩን ችግሮቻችን ተተብትበን ወደፊት መራመድ ተስኖናል
12ኛ. ሁሉም ጠያቂና ተሳዳቢ እንጂ ደጋፊ፡ አይዞኝ ባይ፤ አብሮ ታጋይ ጠፍቷል
13ኛ. ይሀ ሁሉ በእንዲህ እያለ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ፤ ከዚህ በፊት ያልነበረ
አዲሱ ፈሊጥ ደሞ አዲሱን ጠቅላይ ሚንነስትር ጊዜ እንስጠዉ የሚለዉ ሆኗል፤ አይ መዘናጋት፤ ራስን ማታለል፤ ሰዉየዉ እንደሆነ ለዉጥ እንደማይኖር እቅጩን ነግረዉናል።
14ኛ. የመቃወም ትርጉሙ ግራ ገብቶናል መቃወም ማለት ሁሉንም የምንቃወምበት በተለይም አዲስ ሀሳብ አዲስ ራእይ የተለየ አካሄድ ይዘዉ ትግሉን የተቀላቀሉትን እንደጠላት ተረባርበን መማዉገዝና፤ እንደ እባብ ጭንቅላታቸዉን ቀጥቅጠን ያለ የሌለ ሀይላቸንን በመጠቀም አንገታቸዉን እናሰደፋለን፡ ሀሳባቸዉን እንዲሞክሩ እንኳን እድሉን አንሰጣቸዉም። በዚህም ድልን ተግናጽፈን ተደስተን እርስ በእርስ እየተጠፋፋን እንገኛለን።
በኛ ካምፕ
ወይ አንታገል
ወይ አናዋጣ
ወይ ዝም አንል
ወይ አንረዳዳ
ነገሩ ሁሉ ግራ ሚያጋባ ዘመን ላይ እንገኛለን።
ሰላማዊ ሰልፍ ለመዉጣት ልመና
ስብሰባ ለመገኘት ልመና
ለክብር፤ ለህሊና፤ ለነጻነት ለመታገል ለምኑኝ ሚባልበት ዘመን ላይ እንገኛለን።
ባንጻሩ ዘመን ተለዉጦ ስለ እዉነት መቆም፤ ለክብር፤ ለህሊና፤ ለነጻነት ለሀገር መታገል ሚያሳፍርበት፤ ስለነጻነት መናገር ጀግና ወንድ፤ የሀገር ልጅ፤ ሀገር ወዳድ ማስባሉ ቀርቶ፤ እንደ ቁምጥና ሚያሳፍርበትና አንገት የሚያስደፋበት፤ ስለ ክብርም መናገር የሚያስኮንንበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡
ዛሬ ያልታደለችዉ ሀገራችን ኢትዮጵያ ልጆችዎ በሁለት ተከፍለዋል
1. በአንድ ወገን ያለዉ ስርአት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ እንዲቀጥል አስተዋጽኦ እያደረጉ ያሉ አብላጫዎቹ (99.999%) ሲሆኑ
በዚህ ምድብ፡
1. የስርአቱ ዋና አራማጆች
2. ስርአቱን በመደገፍ በቆራጥነት የቆሙለት
3. ከማያዉቁት መላክ የሚያዉቁት ሴይጣን ይሻላል ብለዉ በፍራቻና አንገት በመድፋት የተቀመጡ፤
4. ስለ ኢትዮጵያ አያገባንም ከራሳችንና ጥቅማችን በላይ ነፋስ ብለዉ ክብራቸዉን፤ ስብእናቸዉንና፤ ህሊናቸዉን ዘግተዉ ምን ያገባናል ብለዉ የተቀመጡ
5. ሌሎቹ ደግሞ መታገል እየፈለጉ ግን በፍራቻና ከዚህ በፊት በደረሰባቸዉ መከራ እምነት በማጣት ትግሉን እርግፍ አድርገዉ ተስፋ ቆርተዉ የተቀመጡ
6. ባፋቸዉ ተቃዎሚ ነን የሚሉ ነገር ግን ለዘመናት ምንም ለትግሉ ስተዋጽኦ ሳያደርጉ ለመታገል የመጣዉን ሁሉ ነገር ግን በነሱ አመለካከት የማያምነዉን፤ ለነሱ ያላጎበደደዉን፤ ሁሉ በመቃወም የትግሉን ጎራ በማዳከም የስርአቱን እድሜ እያራዘሙ ያሉ የሚገኙበት ሲሆን
2. በሌላ ጎራ ደሞ ቁጥራቸዉ እጅግ አናሳ ቢሆንም ስርአቱን ሌት ተቀን በመታገል በሀገር ቤትና በዉጭ በአላማ ጽናት፤ በወኔ በመታገልና መስእዋትነት እየከፈሉ ያሉ የቁርጥ ቀን ወገኖች ሲሆኑ ዛሬ ቁጥራቸዉ አናሳ ቢሆንም ዉለዉ አድረዉ ግን ማሸነፋቸዉ አይቀሬ ነዉ። ምክንያቱም እዉነት ከነሱ ጋር ናትና። እነዚህም ዛሬ በየጫካዉ ለኛ ነጻነት እየተዋጉ፤ ለኛ ክብር ወህኒ ቤቶች ተወርዉረዉ የሚገኙ፡ ለኛ ክብር ባሉበት ቦታ ሁሉ ለሃገራቸዉ እየታገሉ ያሉትን ጀግና ዜጎች ሁሉ ያካትታል።
እነዚህ ዜጎች ሀገራቸዉን በቁርጥ ቀን ያልከዱ፤ ለእዉነት በመቆማቸዉ ህሊናቸዉን የማይቆረቁራቸዉ፤ ነገ ስማቸዉና ታሪካቸዉ ዘላለማዊ የሆነ፡ ነገ የልጅ ለጆቻችን የሚዘክሩላቸዉ ብርቅዬ ወገኖቻችን ናቸዉ።
ለሀገር የሚያኮራ ስራ ሰርቶ ስምና ዝና አትርፎ ከማለፍ በላይ ምን የሚያስደስት ነገር ይኖራል። ኖሮ ኖሮ በልቶ፤ ተኝቶ፤ ማለፍማ እንኳን ሰዉ ተብዬዉ እንስሳም ያደርገዉ
የለም። ዋናዉ ጥያቄ ግን እያንዳንዳችን የትኛዉ ምድብ ዉስጥ ነን የሚለዉ ሲሆን የህሊናዉን ሙግት ለናነተዉ እተዎለሁኝ።
ከላይ ያለዉን ተጨባጭ ሁኔታ በዝርዝር ካስቀመጥኩኝ ለዉጥ ከልባችን የምንፈልግ ከሆነ መፍትሄዉ ምንድን ነዉ ወደሚለዉ ሁላችንም ወደ ምንጠይቀዉ ጥያቄ እመጣለሁኝ።
1. ለዉጥ ከልባችን እንፈልጋለን ወይ? ? ? የሚለዉ ጥያቄ በእያንዳንዳችን እዉነትኛ ህሊና መልስ ማግኘት አለበት? በእዉነት ለዉጥ እንፈልጋለን ወይ? ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም እንደሚባለዉ – ለዉጥን ከልቡ በጽናት የሚፈልግ ፍላጎቱን ለሟሟላት የማይፈነቅለዉ ድንጋይ ስለማይኖር ዉጤት ማግኘቱ አይቀሬ ነዉ
2. የትግሉን ክብደትና ጥልቀት ማወቅ ይጠበቅብናል በዚያዉም ልክ የአቅማችንን መጠን ማወቅ አለብን – ንቀታችንና ጥላቻችን የትም አላደረሰንም
3. ዉጤት የምንፈልግና አቅማችንን የምናዉቅ ከሆነ ከሆነ ለዉጤቱ የሚፈለግብንን ሁሉ ሳናመነታ ኢንቨስት ማድረግ አለብን፤ ጊዜ፤ገንዘብ፤ጉልበት፤እዉቀት፤ሞራል ወዘተ – ነጻነት በምጽዋት አይመጣም – መሄድ የሚገባንን መንገድ ሁሉ መሄድ ይጠበቅብናል
4. ትግሉ የማንም እንዳልሆነ መገንዘብ ይጠበቅብናል (የእያንዳንዳችን ሃላፊነት ነዉ – ምክንያት ድርደራ የትም አላደረሰንም – ስለትግሉ አዲሱ ፈሊጥ
– እኔ ፖለቲካ ዉስጥ የለሁበትም – ጀግንነት ሆኗል
– የምናምናቸዉ ሰዎች የሉም – እገሌ ማነዉ እሱ
– ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች አይረቡም
– ዉጭ ያለዉ ሐይል ምንም አያደርግም
– ሀገር ቤት ያለዉ ካልተነሳ የትም አንደርስም

ሁሉም ጣቱን ሲጠቋቆም – ትግሉ ግን እያንዳንዳችን ትከሻ ልይ መሆኑን ዘንግተናል። ስለዚህ
– መሪዎቹንና ድርጅቶቹን ካላመናችሁ ግቡና አስተካክሉ
– ወይንም የራሳችሁን ጠንካራ የተሻለ መንገድ አምጡ- ብቻ በዚህም በዚያም ትግሉን ተቀላቀሉ – አማራጩ ሽንፈትን በጸጋ ተቀብለን – አቅማችንን አዉቀን እየታገሉ ያሉትን ትተን አርፈን መቀመጥ ይኖርብናል – እባካችሁ ባንደግፋቸዉ አናዳክማቸዉ
5. የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ሁኔታ የዶሮና የእንቁላል ሆኗል። ህዝቡ ፖለቲካ ድርጅቶች ካልተጠናከሩ ዉጤት ካላሳዩን አንደግፍም ብሎ አኩርፎ ተቀምጧል። እነሱ ደሞ ሊጠናከሩ የሚችሉት ህዝቡ ሲደግፋቸዉ ነዉ። ግራ የሚያጋባ ሁኔታ። ይህ ካልተቀየረና ህዝቡ በተሳትፎ ካላጠናከራቸዉ የትም አይደረስም።
6. ሌላዉ ሁሉም ፖለቲካ ድርጅቶች አንድ ይሁኑ የሚለዉ ለሀያ አመት የተሞከረዉ ፈሊጥ መቼም አይሰራም – አግባብነት የለዉም – ልዩነት የጥንካሬ መሰረት ነዉ – ዋናዉ ቁም ነገር እርስ በእርስ በመጨራረስ የስርአቱን እድሜ አለማራዘም ነዉ። ስርአቱ እጁን አጣምሮ ደስ ሲለዉም የቤት ስራ እየሰጠን የእርስ በእርስ ሽኩቻ ድራማችንን እያየ ይገናል – መፍትሄዉ ቢቻል ተባብረን ካልተቻለም እርስ በእርስ ሽኩቻችንን አቁመን፤ የተሻሉ ናቸዉ የምንላቸዉን በሙሉ ሀይላችን መደገፍ የትግል አቅማቸዉን ማሳደግ ይኖርብናል – በዚያዉም ልክ ማናቸዉንም ተቃዋሚ ሀይሎችን የሚቃወምን ሁሉ ባለ በሌለ ሃይላችን በጋራ ማዉገዝና መዋጋት ይኖርብናል
7. ትግሉ ጊዜ የሚጠይቅ መሆኑን መረዳት በሂደትም መዉደቅና መነሳት መኖሩን መገንዘብ የኖርብናል፤ (ቅንጅት ቅንጅተ እያልን መቀመጡ የት አደረሰን)? አየር ባየር ዉጤት ፈላጊነት የትም አላደረሰንም፤ ዋናዉ ቁምነገር የፈጀዉን ጊዜ ይፍጅ ካላማችን ንቅንቀቀቅ ማለት የለብንም – የኩርፍያ ትግል የትም አላደረሰንም – ያላማ ጽናት ከሌለን አርፈን እንቀመጥ

በዚህ ጉዳይ ብዙ መናገር ለማጠቃለል ያክል ወደድንም ጠላንም
ዉጤት ያለ አዉነተኛ ፍላጎት
ዉጤት ያለ አቅም
ዉጤት ያለ መስእዋትነት
ዉጤት ያለ ጊዜ
በፍጹም አይገኝም፤
ፍላጎት አቅምና መስእዋትነት ሳይከፍሉ ዉጤትን መጠበቅ የዋህነት ነዉ። ይህንንም የያዝነዉን ፈሊጥና ባህል እንካልቀየርን ድረስ ስርአቱም በአሸናፊነቱ መቀጠሉ አይቀሬ ነዉ። የብዙዎቻችን ችግር የትግሉ ድል መፍትሄ በእጅችን ላይ መሆኑን መቀበል አለመፈለጋችን ወይም አለማወቃችን ነዉ። የወደቅነዉ መፍትሄ ከሌላ ቦታ መፈለጋችን ነዉ። ይህ እስካልተወጠ ድረስ ስርአቱ ለዘመናት መግዛቱን እንደማያቆም በእርግጠንነት ላረጋግጥላችሁ። ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልግ ዛሬ ነገ እያለ በቀጠሮ ሳይሆን ከልቡ ለዉጥን የሚፈልግ ከሆነ ዛሬ ካሁኗ ደቂቃ ጀምሮ ለራሱ ለህሊናዉ ለሀገሩ ለወገኑ ቃል መግባት ይኖርበታል። ስለሌላዉ ማሰባችንን ትተን ስለራሳችን እናስብ። በድርጅቶች ችግር አለ ብለን ካሰብን ገብተን እናሻሽላቸዉ፤ አሊያም የኛ አማራጭ የተሻለ ነዉ የምንል ከሆነ የተሻለ ድርጅት መስርተን ትግሉን እንቀላቀል። በዚህም በዚያም ገብተን እንታገል። የትም እንፍጨዉ ዉጤቱን እናምጣዉ።

እኔ ይህንን ስናገር የሽግግር ም/ቤቱ ግቡ ብዬ አይደለም፡ ለእናንተ ትግል ዉስጥ መግባት የድርጅቶች ጥንካሬ ቅድመ ሁኔታ አይደለም ወሳኙ። የራሳችሁ የህሊና ዉሳኔ ነዉ። ያንን የዉሳኔ ደረጃ ካለፋችሁና ለራሳችሁ ቃል ከገባችሁና ያለማወላወል ወደተግባር ከለወጣችሁ ሌላዉ ሁሉ ይስተካከላል። የተገላቢጦሹን ከፈለጋችሁ ግን ምን አለ በሉኝ ምንም ለዉጥ እንደማይመጣ በድጋሚ አረጋግጣለሁ።
ስለዚህ ብቸኛዉ ያለን የአካሄድ ቀመር በግልጽ እንዲህ ነዉ
1. እያንዳንድችን ዛሬ ትግሉን በቆራጥነት መቀላቀልና ሚከፈለዉን መስዋትነት ሁሉ መክፈል፤ በተጨማሪም ትግሉ የወሰደዉን ጊዜም ቢወስድ በቁርጠኝነት ለመታገል መዘጋጀት
2. በግል የትም ለመድረስ ስለማይቻል ያሉትን ድርጅቶች መርምሮ የተሻለ ነዉ የምንለዉን ዛሬዉኑ ተቀላቅሎ በሙሉ ሀይል መግባትና መታገል
ስለዚህ እመኑኝ የድሉ ቁልፍ እያንዳንዳችሁ ናችሁ። ሌላ ምንም አማራጭ የላችሁም።
ይህንን ለማድረግ ከፈቀድንና ለራሳችን በእዉነተኝነት ቃል ከገባን ምንገነባዉ አቅም የምንመኘዉን ዉጤት ይዞልን ይመጣል። ስለዚህ
የፍላጎት አቅም
የዉሳኔ አቅም
የሞራል አቅም
የአላማ ጽናት አቅም
የማቴርያል አቅም
የድርጅት አቅም
ለድላችን ወሳኝ መሆኑን ተረድተን ዛሬ ነግ ሳንል ትግሉን እንቀላቀል። በኛ በኩል እዉነቱን መራራም ቢሆን ተናግረናል፤ ለህሊናችን የሚቆጨን ነገር የለም፡ የህሊና ትግሉን ለናነት ትተናል።

እኛ በራሳችን በኩል የተሻለ ነዉ ያልነዉን አማራጭ አቅርበን ትግላችንን ተያይዘነዋል። በማናቸዉም መንገድ ለማንም ሳንል፤ ለእዉነት ብቻ ብለን፤ ለክብራችን ብለን፤ ለነጻነታችን ብለን፡ ትግሉ ጊዜ እንደማይሰጥ ተረድተን ቀጠሮ ሳንሰጥ የድሉን ጽዋ እስክንጎነጭ፤ ማንም ምንም የበል ምን፤ በቁርጠኝነት እየታገልን እንገኛለን። ልዩነቱ የህሊና እርካታ፤ የመንፈስ የማንነት ጽናትን ሰጥቶናል። ወርቅ በእሳት እንደሚፈተነዉ ችግርና መከራን ለመጋፈጥ ትግሉን በቆራጥነትና በኩራት እያከናወንን እንገኛለን። በስራችንም ኩሩ ኢትዮጵያዉያን እንደምንሆን አንጠራጠርም፤ ለእዉነት በመቆማችንና አምላክም ከቅኖች ጋር በመሆኑ አሸናፊዎች እንደምንሆን ሙሉ እምነት አለን። ከዚህ በላይ ታዲያ ምን የሚያስቀና ነገር ይኖራል።
ሀገራችን ክብራችን፤ የማንነታችን መለያ፤ የነጻነታችን ምልክት ናት። ማንም ይህንን ሊነጥቀን አይገባዉም፤ በትግላችንም የተነጠቅነዉን ማንነታችንን ያለጥርጥር እናስመልሳለን!!!
ድርጅታችንን በለመለከተ ግን አቋማችን ንጥር ያለና ግልጽ ነዉ
1. የማንም ኢትዮጵያዊ ክብርና፤ ነጻነት፤ በማናቸዉም ሁኔታ ሳይሸራረፍ መረጋገጥ ይኖርበታል እንላለን። አምላካችን የሰጠንን መብት ለማንም አሳልፈን አንሰጥም። ስርአቱ የሚሰራዉን ግፍ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እስካላቆመ ድረስ በፍጹም አለማመንታት መቀየር አለበት በሚለዉ አቋማችን ጸንተን ትግላችንን እንቀጥላለን – ይህም ስርአት ሁሉን ኢትዮጵያዊ አካላትን ባካተተ የሽግግር መንግስት እስኪተካ ትግላችንን በጽናት እንቀጥላለን
2. ህዝባዊ የለዉጥ እንቅስቃሴ በመፍጠር ስርአቱን በህዝባዊ ትግል ለመገርሰስና ትግሉን በድል ለማጠናቀቅ ህዝቡ ትግሉን እንዲቀላቀል ትግላችንን ሌት ተቀን እንቀጥላለን
3. ስርአቱም ሲገረሰስ የሚከሰቱ ችግሮችን ለመቅረፍ ቀድሞ መሰናዳት የተሻለና ብልህነትን የተላበሰ ማራጭ መሆኑን ስለምናምን የሽግግር ሂደቱ ምን መምሰል እንደሚኖርበት ቅድመ ዝግጅቶችን እንደርጋለን
4. ይንንኑም ለማከናወን የሚያስችል ድርጅታዊ አቅም እንገነባለን በዚህም አካሄድ ያለማወላወል እንቀጥላለን።
5. ከሌሎች ሁሉም አሁንም እደግመዋለሁ ከሁሉም የተቃዋሚ ሀይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን፤ ተቃዋሚ ሀይሎችም በጋራ እንዲሰሩ ማናቸዉንም ሁኔታዎች እናመቻቻለን
ስለዚህ የድርጅታች የነጠረና ግልጽ ያለ አማራጭን ያቀረበ ሲሆን፡ ይሻላል ብላችሁ ካመናችሁ ተቀላቀሉን። አለበለዚያ ሌላ የተሻለዉን ድርጅት ዛሬዉኑ ተቀላቀሉ። አንድ ነገር ላረጋግጥላችሁ ትግሉ ይቀጥላል። ተጠናክሮ ይቀጥላል። ባቡሩን በጊዜ ተቀላቅሎ የለዉጡን ሂደት ማፋጠኑ የናንተ ሀላፊነት ነዉ። በታሪክ ተጠያቂነት ምርጫዉን ለናንተ እተዋለሁ። የሚሻለዉን የጽናት መንገድም አምላክ ያሳያችሁ ዘንድ ሁሌም እጸልያለሁ።

ሀገራችንን ኢትዮጵያን አምላክ ይባርክ!!!

Will the U.S. Stand by the Side of Brave Africans?

maglIf History is on the Side of Brave Africans, Shouldn’t the U.S. be Too?

When President Obama visited Accra, Ghana in 2009, he delivered two distinct political messages within one overarching moral imperative: “History is on the side of brave Africans”. His message to African governments and leaders was emphatic:

…Make no mistake: history is on the side of these brave Africans, and not with those who use coups or change Constitutions to stay in power. Africa doesn’t need strongmen, it needs strong institutions… [G]overnments that respect the will of their own people are more prosperous, more stable, and more successful…

His message to the people of Africa was inspiring, upbeat and passionate:

…You have the power to hold your leaders accountable, and to build institutions that serve the people. You can conquer disease, end conflicts, and make change from the bottom up. You can do that. Yes you can. Because in this moment, history is on the move.

President Obama also made a solemn promise to Africans:

… What we will do is increase assistance for responsible individuals and institutions, with a focus on supporting good governance – on parliaments, which check abuses of power and ensure that opposition voices are heard; on the rule of law, which ensures the equal administration of justice; on civic participation, so that young people get involved; and on concrete solutions to corruption… to advance transparency and accountability.

Now, at the cusp of the beginning of President Obama’s second term, we have to ask some tough questions: Are there more African strongmen in 2012 than in 2009? Are there fewer brave Africans on the streets and more of them in jail in 2012 than in 2009? Does Africa today have more debilitated institutions than it had in 2009? Do more African governments respect the will of their people today than they did in 2009? Is there less conflict in Africa today than in 2009? Does Africa today have good governance and is the rule of law the rule in Africa? Are more opposition voices heard, more civic participation seen and more youth and women involved in the political process in Africa today than they did in 2009? Does the U.S. today “stand with all those who seek to advance human dignity”?  Is history in Africa today on the move forward to democracy, freedom and human rights, or is Africa marching backwards into the darkness of dictatorship and tyranny?

Is the U.S. today standing tall with the brave Africans or in bed with Africa’s strongmen?

Whatever Happened to the Brave Africans President Obama Spoke About in 2009? 

According to the U.S. Department of State’s Human Rights Practices Report for 2011 (May 2012), many of the “brave Africans” President Obama spoke about in 2009 are jailed, tortured, silenced, on the run, dead or just scared stiff under relentless official harassment and persecution. Arbitrary arrests, lengthy pretrial detentions, torture, and mistreatment of detainees by security forces, harsh and life-threatening prison conditions, illegal searches and seizures and infringements of citizens’ privacy rights, restrictions on freedom of speech and of the press and assembly in one form or another are the common facts of African daily life. African societies and institutions are decimated by official corruption and bloated bureaucracies. Justice is traded to the highest bidder in politically-controlled judiciaries; and rubberstamp parliaments crank out laws and proclamations like a Chinese toy factory.  African societies are plagued by discrimination on the basis of ethnicity, gender, language, religion, culture and region.

Among the most flagrant violators of human rights in Africa is the regime in Ethiopia. In May 2010, the ruling party in that country “won” 545 of 547 [99.6 %] seats in parliament. A White House Statement on that election turned a blind eye and  voiced muted “concern”:

An environment conducive to free and fair elections was not in place even before Election Day. In recent years, the Ethiopian government has taken steps to restrict political space for the opposition through intimidation and harassment, tighten its control over civil society, and curtail the activities of independent media. We are concerned that these actions have restricted freedom of expression and association…

In a speech given at the National Endowment for Democracy in October 2012, Karen J. Hanrahan, Deputy Assistant Secretary, Bureau of Democracy, Human Rights, and Labor  characterized the deplorable human rights situation in Ethiopia as merely a “challenge”:

… In Ethiopia, we are faced with a challenge. The principal question is how to work constructively with both the government and civil society to advance democracy and human rights when the government has limited political and civil space. This has included restrictions on civil society organizations, the curtailment of media freedom, and the conviction of journalists and members of the political opposition under the Anti-terrorism Proclamation. We’re particularly concerned about the Charities and Societies Proclamation and the Anti-terrorism Proclamation…

The “challenge” Hanrahan talks about includes the arrest of  “more than 100 opposition political figures, activists, journalists, and bloggers,” massive suppression of the independent press, virtual bans on civil society and nongovernmental organizations,beatings and torturing of detainees by security forces and poor prison conditions. It also includes the unlawful persecution and imprionsment of the 2012 PEN America Freedom to Write Award winner Eskinder Nega;  Reeyot Alemu, the 2012 winner of the International Women’s Media Fund’s Courage in Journalism Award; Woubshet Taye,  editor of a popular weekly, opposition party leaders Andualem Aragie and Natnael Mekonnen among many others. The evidence reported in the  latest U.S. State Department Human Rights Practices Report on Ethiopia (May 2012)  shows that describing the human rights situation in Ethiopia as a “challenge” and glossing it over with a polite expression of “concern” is tantamount to adding insult to injury.  The human rights situation in that country should provoke unmitigated moral outrage and immediate and direct action to uphold democratic principles and standards of universal human rights.

Perhaps current U.S. leaders could learn valuable lessons from their predecessors who faced similar “challenges” posed by tyrannies and dictatorships. President Truman once said, “Once a government is committed to the principle of silencing the voice of the opposition, it has only one way to go, and that is down the path of increasingly repressive measures, until it becomes a source of terror to all citizens and creates a country where everyone lives in fear.” Such is the indisputable fact of life in Ethiopia today and no amount of empty talk  about “concerns” and hollow promises about overcoming  “challenges”  will change the situation!

The U.S. Record in Africa Today Leaves Much to be Desired

According to Assistant Secretary Johnnie Carson who heads the U.S. Department of State’s Bureau of African Affairs, there are “five pillars that serve as the foundation of U.S. policy toward Africa.” These include “(1) support for democracy and the strengthening of democratic institutions including free, fair, and transparent elections; (2) support for African economic growth and development; (3) conflict prevention, mitigation, and resolution; (4) support for Presidential initiatives such as the Global Health Initiative, Feed the Future, and the Global Climate Change Initiative and (5) working with African nations on transnational issues such as drug smuggling, money laundering and trafficking in persons.” Carson reported that U.S. policy in Africa “in recent years”

has contributed to democratic transitions in Cote d’Ivoire, Guinea, and Niger; successful elections in Nigeria; and a referendum that led to the independence of South Sudan. The Bureau promotes African economic development through the annual Africa Growth and Opportunity Act (AGOA) Forums. It is actively striving to end sexual and gender-based violence in the Democratic Republic of the Congo (DRC) and eliminate the atrocities perpetrated by the Lord’s Resistance Army throughout Central Africa. Feed the Future, the U.S. Government’s global food security initiative, is focused on 12 African countries…

In her Preface to the U.S. Department of State’s Human Rights Practices Report for 2011 (May 2012), Secretary Hilary Clinton declared:

In my travels around the world as Secretary of State, I have met many individuals who put their lives on the line to advance the cause of human rights and justice. In ways small and large, they hold their governments accountable for upholding universal human rights… The United States stands with all those who seek to advance human dignity…

These quite modest accomplishments in Africa fall far short of President Obama’s lofty and eloquent words and majestic promises in Accra and his Administration’s actions to support good governance and promote human rights in Africa. Shakespeare said, “Action is eloquence.” Though there is always a gap between political rhetoric and political action, one should not confuse the eloquence of words with the eloquence of action. But this is not the time to look back and engage in recriminations, teeth-gnashing, belly-aching and finger pointing. We shall march to our President’s battle cry and “Keep Moving Forward”.

Time to Put Up or Shut Up?

Americans are generally known for straight talk, cutting down to the chase or cutting out the bull. It is one of the great qualities I have always appreciated in ordinary Americans and some of their great leaders. They say what they mean and mean what they say. It was “plain talkin’” President Harry S. Truman who said, “I never did give anybody hell. I just told the truth and they thought it was hell.”  So, I will do a little bit of straight talking. We have heard enough of human rights pontifications and declarations. We know all about the “challenges”, “problems”, “difficulties” and “issues” in improving human rights and good governance in Ethiopia and the rest of Africa.  We have also heard enough grousing, whining and complaining in Diaspora Ethiopian communities, particularly in the U.S., about what the U.S. has done, not done or could have done to to promote good governance, democracy and human rights in Ethiopia. In President Obama’s second term, there are only two choices: Put up or Shut Up! Put another way, the U.S. can step up and stand tall with the brave Africans or roll over in bed with the shameless and cowardly dictators who cling to power through handouts, World Bank and IMF loans and the barrel of the gun.

How to Help the Brave Ethiopians: Where to Start?

Many veteran Ethiopian human rights advocates will no doubt remember H.R. 2003 (“Ethiopia Democracy and Accountability Act of 2007”; originally introduced as H.R. 4423 “Ethiopia Consolidation Act of 2005” by Congressman Chris Smith of New Jersey when he chaired the Subcommittee on Africa and later renumbered as H.R. 4423 and H.R. 5680 in the House Committee on Foreign Affairs). Congress Donald Payne of New Jersey took the lead on H.R. 2003 when he became chairman of the Africa Subcommittee in 2007 and obtained the co-sponsorship of  some 85 members of Congress. That bill passed the House in October 2007. Its key provisions focused on a number of issues central to good governance and protection of human rights in Ethiopia, including the release and/or speedy trial of all political prisoners in the country,  prosecution of persons who have committed gross human rights violations, financial support to strengthen human rights and civil society groups and establishment of an independent judiciary, support for independent media operations, training assistance to strengthen legislative bodies, electoral commission and civil society groups, among others. Unfortunately, the bill never made it for a floor vote in the Senate.

Recently, the U.S. Congress passed and the President signed an important piece of legislation last week known as the “Sergei Magnitsky Law” (Senate Bill 1039  sponsored by democratic Senator Ben Cardin of Maryland, a long-time civil rights and civil liberties advocate and co-sponsored by 33 other Senators; and  H.R. 4405 in the House sponsored by the well-known human rights advocate and democratic Congressman Jim McGovern of Massachusetts and co-sponsored by 15 other members). This law is designed to “impose sanctions on persons responsible for the detention, abuse, or death of Sergei Magnitsky, for the conspiracy to defraud the Russian Federation of taxes on corporate profits through fraudulent transactions and lawsuits and for other gross violations of human rights in the Russian Federation.” The “Magnitsky” language was incorporated in a larger legislation (‘‘Russia and Moldova Jackson-Vanik Repeal and Sergei Magnitsky Rule of Law Accountability Act of 2012’’).

Sergei Magnitsky was a brave and principled 37-year-old Russian lawyer who exposed massive government corruption involving money-laundering by Russian officials. He died in prison in 2009. Russian President Dimitry Medvedev, citing the  conclusions of the independent Presidential Council for the Development of Civil Society and Human Rights, reported that Magnitsky was illegally arrested, detained and denied justice by the very courts and prosecutors of the Russian Federation he was investigating and accusing.  While in detention Magnitsky was denied necessary medical care and died from beatings he received by prison guards. Despite overwhelming evidence of official criminality in the Magnitsky case, no officials have yet to be brought to justice.

The key provisions of the Magnitsky Law requires the State Department to maintain a list of human rights abusers in Russia, freeze their assets and deny them U.S. visas.

Section 404 of the law (“Identification of Persons Responsible for the Detention, Abuse and Death of Sergei Magnitsky and Other Gross Violators of Human Rights”) requires the President to submit to Congress within 120 days “a list” of names of persons likely to have been involved directly or indirectly in “the detention, abuse, or death of Sergei Magnitsky” and other individuals “responsible for extrajudicial killings, torture, or other gross violations of internationally recognized human rights committed against individuals seeking to expose illegal activity carried out by officials of the Government of the Russian Federation.”

Section 406 requires the President to use his legal authority to “freeze and prohibit all transactions in all property and interests in property of a person who is on the list required by section 404(a) if such property and interests in property are in the United States, come within the United States, or are or come within the possession or control of  a United States person.” The law further imposes penalties on any “person that violates or conspires to violate” the law to the same extent as a person that commits an unlawful act.

Helping Ethiopia’s “Magnitskys”

In his 2009 Accra speech, President Obama told Africans that the U.S. will “increase assistance for responsible individuals and institutions, with a focus on supporting good governance… to advance transparency and accountability.” He also said that it is possible to “make change from the bottom up because in this moment, history is on the move.” Well, the moment of history to get Ethiopian human rights legislation passed through the U.S. Congress is now! There is a perfect alignment of the bipartisan legislative stars. Human rights as a policy issue is taking front and center among both Democrats and Republicans. The Magnitsky Law was a significant legislative victory not only for the memory of the brave Sergei Magnitsky but for all brave victims of official human rights abuses everywhere. Senator Cardin toiled for years to get the bill through Congress and managed to do so with the support of senior republicans. (Truth be told, the Obama administration did not support linking the human rights legislation to a trade bill, but in the end had to give in.)

The bipartisan support for human rights as evidenced in the Magnitsky Law is refreshing, invigorating, inspiring and long overdue. Republican Arizona Senator John McCain said the United States had a moral obligation to speak out for Magnitsky, as well as others who are still alive and languishing unjustly in Russian prisons: “We are sending a signal to Vladimir Putin and the Russian kleptocracy that these kind of abuses of human rights will not be tolerated without us responding in some appropriate fashion. I believe that this legislation is not anti Russia. I believe it’s pro Russia…. I continue to worry about them and I pray for them.” Republican Arizona Senator Jon Kyl said the bill should have applied to all countries. Democratic New Hampshire Senator  Jeanne Shaheen said that the United States intends to pay attention to human rights everywhere. “We will stand up for those who dare to speak out against corruption. This bill is for all the Magnitskys around the world.” Senator Ben Cardin said he would push to make it universal in scope so it could be used to punish other human rights violators around the world. “Now we start a new chapter in human rights. The legislation sets a precedent for international conduct that we expect will be honored globally.” Even the White House issued a Statement indicating that the President will support legislation that will “promote the rule of law and respect for human rights around the world”.

There are thousands of “Ethiopian Magnitskys” who have been denied justice, languishing in prison and forgotten. For starters, there has been no accountability for the post-2005 election massacres in which, according to an official Ethiopian Inquiry Commission, some 200 unarmed demonstrators were gunned down and another 800 wounded by security and police officials of the regime. There is a certified list of at least 237 individuals known to be involved or strongly suspected of direct involvement in these crimes against humanity.  It is mandatory that these officials be brought to trial without delay.

It is great to see a sea change in the U.S. Congress on the issue of human rights. There seems to be a new attitude and renewed commitment to human rights and good governance and a recognition that human rights are an integral part of international law and civilized humanity. President Ronald Reagan said, “Freedom is one of the deepest and noblest aspirations of the human spirit.” President Jimmy Carter said, “America did not invent human rights. Human rights invented America.” In Ethiopia and many parts of Africa, the noblest aspirations of the human spirit go unfulfilled. And just like human rights invented America, I believe it is time for human rights to reinvent Ethiopia and the rest of Africa.

As far as I am concerned, what is good enough for the brave Sergei Magnitsky of Russia is good enough for the brave Melesachew D. Alemnew, age 16, Hadra S. Osman, age 22, Etenesh Yimam, age 50, Teodros Gidey Hailu, age 23, Gashaw T. Mulugeta, age 24, Lechisa K. Fatasa, age 21…. of Ethiopia! History is on the move. Now Ethiopian Americans, let’s get a move on! Yes, We Can have an “Ethiopian Magnitsky Law”! With a little help from our friends!

Standing tall with the “brave Africans” is standing up on the right side of history. 

Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.

Previous commentaries by the author are available at:

http://open.salon.com/blog/almariam/

www.huffingtonpost.com/alemayehu-g-mariam/ 

Amharic translations of recent commentaries by the author may be found at:

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24