Skip to content

አዲስ ፓርቲ የማቋቋም ማመልከቻ ለምርጫ ቦርድ ቀረበ

የቅንጅት የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በአዲስ ፓርቲ ለመንቀሳቀስ የሚያስችለውን የፊርማ ማሰባሰቢያ ፈቃድ ለማግኘት በዛሬው እለት ለምርጫ ቦርድ ማመልከቻ አቀረበ፡፡

አመራሩ ባለፈው ሳምንት የላእላይ ም/ቤቱን 33 አባላት በማወያየት አዲስ ፓርቲ የመመስረት ሃላፊነቱን እንደተረከበ የሚታወስ ሲሆን በጉዳዩ ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ያሉ ወኪሎቹን የማነጋገሩን ሂደት በም/ሊቀመንበር ብርቱካን ሚደቅሳ አማካይነት በዚህ ሳምንት መጀመርያ ላይ በአዋሳ ከተማ በማድረግ ውጤታማ ውይይት አካሂዷል፡፡

ምርጫ ቦርድ የቀረበውን ማመልከቻ ከመረመረ በኋላ በነገው እለት የፊርማ ማሰባሰቢያ ፈቃዱን ለመስጠት ቀጠሮ እንደሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

Leave a Reply