Kangaroo court reduces Teddy Afro’s sentence to 2 years

ADDIS ABABA, ETHIOPIA – The Woyanne high kangaroo court today reduced Teddy Afro’s 6-year prison sentence to 2 years, allowing him to go free in 5 months from now.

Teddy has been held in prison for the past 11 months after being falsely accused of vehicular manslaughter.

In December 2008, a Woyanne party hack acting as judge sentenced him to 6 years in prison for killing a homeless man, Degu Yibelte, in Addis Ababa with his BMW in what the prosecutor alleged as a hit-and-run accident.

A hospital record that showed Degu’s death one day earlier than the day Teddy had a car accident was ignored by the dumb judge.

ቴዲ አፍሮ ከአምስት ወር በኋላ ይፈታል

(አውራምባ ታይምስ) – ዝነኛው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በመኪና ሰውን ገጭቶ በማምለጥ ወንጀል ክስ ተመስርቶበት በከፍተኛ ፍርድ ቤት የስድስት አመት እስራት እንደተፈረደበት ይታወቃል፡፡

ሆኖም ድምጻዊው ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው ይግባኝ መሰረት ውሳኔው ተሸሮ በሁለት አመት እስራት ብቻ እንዲቀጣ ተወስኖበታል፡፡

አውራምባ ያነጋገራቸው የህግ ባለሙዎች እንዳሉት ‹ያቀረበው የይግባኝ ሰነድ የቀረበበትን ክስ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ የሚያደርግ ነው ሆኖም የስርአቱ አገዛዞች ድምጻዊውን ነጻ ማድረግ ስላልፈለጉና ወንጀለኛ ነው እንዲባል ስለሚፈልጉ ነጻ ከማለት ይልቅ ሁለት አመት ብለው ፈርደውበታል› ብለዋል፡፡

ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የቃሊቲ ወህኒ ቤት ኃላፊዎች እንደገለጹልን በወህኒ ቤቱ አሰራር መሰረት አንድ ፍርደኛ ከተፈረበት ፍርድ 1/3ኛውን በአመክሮ ስለሚቀነስለት የሚታሰረው አንድ አመት ከአራት ወር ብቻ ይሆናል ብለዋል፡፡ በዚህም መሰረት እስካሁን ለአስራ አንድ ወራት ያህል በእስር ቤት የቆየው ቴዲ ከአምስት ወር በኋላ ነጻ ይወጣል ተብሎ ይገመታል፡፡

አመክሮ የሚከለከልበት የተለየ ምክንያት አለ ወይ ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የወህኒ ቤት ምንጮች እንደገለጹልን አንድ ታሳሪ የተለየ መጥፎ የዲስፕሊን ችግር ከሌለበት በስተቀር ወይም ለማምለጥ ሙከራ ካላደረገ በቀር የአመክሮ ተጠቃሚ ይሆናል ቴዲ ደግሞ በሁሉም ዘንድ እጅግ የሚወደድ ባህሪና ጨዋ ስነምግባር ያለው ሰው እንደመሆኑ ይህ አይነቱ ክልከላ እርሱን አይመለከትም ብለውናል፡፡

Related:

* Teddy Afro railroaded to prison for 6 years by kangaroo court

* High court reduces Teddy Afro’s sentence to 2 years

* Ethiopians react to Teddy Afro’s sentence

* There Is No Justice In Ethiopia – The Teddy Afro show trial

* Ethiopians in DC demand the release of Teddy Afro