Preparations from regime change in Ethiopia underway

Conditions in Ethiopia are more ripe for regime change than in any other country in the world. These are some of the facts:

1. The dictator, Meles Zenawi, has been in power for 20 years. He is the most despised politician in Ethiopian history.

2. The economy is in shambles with over 40 percent unemployment.

3. Millions of Ethiopians go hungry.

4. The regime is extremely incompetent, corrupt and brutal.

5. In the 2005 elections, Ethiopians voted by an overwhelming margin against the regime. Their vote however was stolen, and when the people protested, Meles unleashed a campaign of terror against them.

The 2005 Ethiopian uprising failed primarily due to the opposition party’s timidity, luck of creativity and absence of leadership. The people of Ethiopia were ready to remove the regime through the ballot box, and when Meles refused accept rejection, they revolted. Unfortunately, the opposition leaders blinked and exposed the people to horrific attacks that have left them traumatized to this day.

Tthe people of Ethiopia need not depend on one leadership. Like Egypt and Tunisia, the campaign to remove Ethiopia’s ethnic apartheid regime must be structurally decentralized while united in its common goal. At the right moment, the various political, civic, youth and other groups who are involved in the campaign will elect transitional leaders. Until then, every organization can play a valuable role in the campaign to free Ethiopia from the Meles regime.

The following set of recommendations [in Amharic] by Ginbot 7 is helpful and needs to be distributed widely by all Ethiopian media, civic and political groups who need to come up with their own ideas and suggestions as well.

Please help distribute the following message from Ginbot 7

ለስኬታማ ህዝባዊ አመጽ ልንጠቀምባቸው የሚገቡን ዘዴዎች

(Source: Ginbot7.org)

ቱኒዚያውያን ከአንድ ወራት በፊት ለሃያ ሶስት አመታት የገዛቸውን አምባገነን ካስፈረጠጡት በኋላ፣ የነጻነት መንፈስ እሳት በግብጽ ላይ ወርዶ ለአስርተ አመታት የቆየን ፍርሃት በልቶታል። ቀድሞ አንገታቸውን ዝቅ ያደረጉ ቀና ብለዋል። ትናንት ሲረገጡ እራሳቸውን ዝቅ አድርገው የተቀበሉ፤ ዛሬ በቀጥቃጦቻቸው ትክክል ቆመው እውነትን በድፍረት የሚናገሩ ሆነዋል።

ህዝባዊው ሞገድ ግብጽ አላቆመም። የመንም እየተናወጠች ነው። አልጄሪያ፣ ሞሮኮ፣ ዮርዳኖስ፣ እና ጎረቤታችን ሱዳንም እጣ ደርሷቸዋል። በሳውድ አረቢያ እና በጋቦንም መለስተኛ የተቃውሞ ሰልፎች ተስተውለዋል። የአልጄሪያ እና የሶሪያ የዴሞክራሲ ታጋዮች በሚቀጥለው ወር የተሟሟቀ ተቃውሞ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ እንደሚገኙም ተሰምቷል።

እንግዲህ ከዚህ ሁሉ በስተጀርባ፤ በተለይም ከስኬታማው የቱኒዚያ ንቅናቄ እና ግብጽን እያንቀጠቀጠ ካለው እንቅስቃሴ በስተጀርባ፤ የሚያስገርሙ የወጣቶች የፈጠራ ሃሳቦች እና ድርጅቶች ተስተውለዋል። ለረዥም አመታት፥ በርካቶች በነዚህ አገራት እንዲህ ያለ ህዝባዊ አመጽ መንግስት ሊጥል አይችልም፤ የመንግስታቱ አፈና ከባድ ነው ብለው ሲያጣጥሉ ቆይተዋል። ያም ደግሞ በተወሰነ ደረጃ እውነት ነው፤ ህዝቡ እነዚህን ሰልፎች ለማካሄድ ብዙ መስዋእትነት እየከፈለ ነው። ብዙ የፖለቲካ ተንታኞች፥ ይህ የሚካሄደው በአገራችን ቢሆን ኖሮ ከዚህ እጅጉን የከፋ እና በብዙ እጥፍ ያየለ መስዋእትነት እንደሚከፈል ይናገራሉ።

ይሁን እንጂ፥ በነዚህ በሰሜን አፍሪካ አገራት ከተከሰቱ ህዝባዊ አመጾች የምንማረው አንድ ቁምነገር አለ። ይህም ቁምነገር ለአገራችን ወጣቶችም ቢሆን አስተማሪ ነው። በአጭሩ ሲቀመጥ፥ “ለሁሉ ችግር መፍትሄ ያለው በገዛ እጃችን ውስጥ ነው።” የሚለው ነው። በአሁኑ ሰዓት፥ በኢትዮጵያ ውስጥ የአመጽ ሰልፍ የጠራ ቡድን የለም። ይሁን እንጂ፥ በሰሞኑ ክስተቶች በመገፋፋት፣ ብዙ ወጣቶች ተነሳሽነት እያሳዩ ይገኛሉ።

ስለዚህም የቱኒዚያ እና የግብጽ ወጣቶች፥ ከነፍሰ ገዳይ የመንግስት የደህንነት ሃይሎች እና ፖሊሶች ለማምለጥ እና ስኬታማ አመጽ ለማካሄድ ከተጠቀሙባቸው ዘዴዎች ውስጥ የተወሰኑትን፤ እንዲሁም ሌላ ቦታ የተገኙ ሃሳቦችን ሰብስበን ለማካፈል ወደናል። እንደሚከተለው እናቀርባቸዋለን።

  1. በቱኒዚያ እና በግብጽ ህዝባዊው አመጽ ያለ ከልካይ እንደ ጎርፍ እንዲፈስ ከረዱት ዘዴዎች አንዱ፥ ሰልፈኞቹ በፖሊስ ላይ ያሳዩት ብልጣብልጥነት/ወይም ወጣቶቻችን እንደሚሉት ሽወዳ ነው። የፖሊስ መኪና ሊገባባቸው በማይችሉ ትናንሽ የመንደር መንገዶች ላይ በየሰፈሩ መሰብሰብ እና ሰልፉን እና የአብሮነትን ስሜት ማሟሟቅ፤ የፖሊስ ወይም የደህንነት ሰራተኞች ቁጥር ከህዝብ ቁጥር ጋር ሲነጻጸር ሁልጊዜም ቢሆን ዝቅተኛ መሆኑን መረዳት፤ በተጨማሪም፥ ፖሊሶች ብቻቸውን ወዲያ ወዲህ ለማለት ስለሚፈሩ በቡድን መጓጓዛቸው ሽፋናቸውን እንደሚቀንስባቸው ማወቅ፤ እና የመሳሰሉት ተስተውለዋል።
  2. በቱኒዚያ፥ ሰልፎች የጀመሩት በትናንሽ ከተሞች ነው። ከዛ ቀስ እያሉ ወደ ዋና ከተማው መጡ። ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ፥ የአዲስ አበባ ህዝብ ብቻውን የተጨፈጨፈው ተቃውሞ የተጀመረው እዛ ስለሆነ እና አብዛኛው ፌዴራል ፖሊስ እና በአስር ሺሆች የሚቆጠሩ የጦሩ አባላት በመዲናይቱ ስለተሰባሰቡ ነው። ተቃውሞ የሚጀመረው በሺሆች በሚቆጠሩት የኢትዮጵያ መንደሮች ቢሆን ግን፥ አገዛዙ ያንን ለመቆጣጠር ሲል ፖሊሶቹን ወደየክፍላተ አገራቱ ይልካል። ያም ሃይሉን ይለጥጥበትና ይዳከማል። አዲስ አበባ ላይ ሃይሉ ከተዳከመ ደግሞ፥ በሚሊዮኖች የሚቆጠረው የከተማይቱ ህዝብ የተቀሩትን የፖሊስ እና የደህንነት ሰራተኞች ተቋቁሞ የአራት ኪሎን ቤተመንግስት እንደ ንብ የማይወርበት እና አምባገነኑን በቁጥጥር ስር የማያውልበት ምንም ምክንያት አይኖርም። አገዛዙ ይህንን ፈርቶ በገጠር የሚከሰቱ ተቃውሞዎችን ለመቆጣጠር የጦር ወይም የፌዴራል ፖሊስ ሃይሎችን ካልላከ ደግሞ፣ ያም ይጎዳዋል። ምክንያቱም፥ እያንዳንዱ የገጠር ነዋሪ እየተነሳ የወያኔ ካድሬዎችን፣ ሰላዮችን እና ሚሊሻዎችን በቁጥጥር ስር ሲያውል፤ ቀጥሎ ያለው መንደርም የልብ ልብ እያገኘ ያንኑ ያደርጋል፤ ያም እየተስፋፋ ይሄድና የአገዛዙን ውድቀት ያፋጥነዋል።
  3. ፖሊስን ማዳከም። ሰሞኑን በግብጽ፥ ወጣቶቹ ከፖሊስ ጋር የድመት እና የአይጥ ጫወታ ሲጫወቱ ነበር ይባላል። አንድ የፖሊሶች ቡድን መጥቶ አንድ የወጣቶች ስብስብ በስንት መከራ ሰብሮ እና ወጣቶቹን በተለያየ አቅጣጫ አሯሩጦ እፎይ ከማለቱ፤ በአስር አቅጣጫ የሮጡት ልጆች መንደራቸውን ከማንም በላይ ስለሚያውቁ እንደገና አንድ ቦታ ተሰብስበው ቁጭ ይላሉ። ፖሊስን የማዳከም ጥቅም እራሱን የሚገልጠው ህዝባዊ አመጹ ለቀናት ሲቀጥል ነው። የተዳከመ ፖሊስ ህዝቡን መጋፈጥ ይሳነውና ሰልፉ ከቁጥጥሩ ውጪ ይሆናል፤ የስፋም ይቆርጣል።
  4. የፈረቃ ሰልፍ። የግብጽ የሰልፍ አቀናባሪዎች፤ ህዝቡ በፈረቃ ሰልፍ እንዲወጣ መልክት አስተላለፉ። ማለትም፥ የመጀመሪያው ፈረቃ ለስምንት ሰአታት ሲሰለፍ፣ ሁለተኛው ለቀጣኡ ስምንት ሰዓታት፤ የተቀረው ደግሞ ለቀጣዩ። ህዝቡ ብዙ ሚሊዮን ከመሆኑ የተነሳ፣ እንደዚህ እየተፈራረቀ ሌሊቱን ሙሉ መንገድ ላይ ለመቅረት ይችላል። ፖሊሶች ግን በቁጥር ትንሽ ስለሆኑ፣ እንደዚህ በፈረቃ እንስራ ቢሉ ቁጥራቸው የባሰውኑ ያንሳል። ይህ ፖሊሶቹን ከማዳከሙ በተጨማሪ፤ ሌሊት ላይ በየቤቱ በመዞር የአመጹ መሪዎች ናቸው ብለው የሚጠረጥሯቸውን ዜጎች ለማሰር የሚያስፈልጋቸውን ፋታ አይሰጣቸውም።
  5. የታቀደ መበታተን እና ፖሊስን አሳስቶ ህዝቡ ወደሚፈልገው አቅጣጫ መምራት። በአንድ ወቅት በመራቤቴ አካባቢ፣ ህዝብ አምጿል የሚል ወሬ ተሰምቶ፣ ያንን በቁጥጥር ስር ለማዋል ወደ ከተማዋ የተላኩትን የደህንነት ሰራተኞች፣ ህዝቡ “ሽፍታ! ሽፍታ!” ብሎ እየጮኸ ወደ ጫካ መራቸው ይባላል። እዛ ምን እንደተደረጉ አይታወቅም። ነገር ግን ተመልሰው አልመጡም። ለማንኛውም፥ በተለያየ አቅጣጫ በመበተን እና ፖሊሶች ተከትለው እንዲመጡ በማድረግ፤ ህዝብ የቁጥር አብላጫ ያለው መስሎ ከተሰማው፤ በቁጥጥር ስር ሊያውላቸው ይችላል። ይህኛው ዘዴ፥ ፖሊስ እና ደህንነት ከማዳከም አኳያም ትልቅ ጥቅም አለው።
  6. ብቁ የሆነ የመረጃ መለዋወጫ እና ለህዝብ መልክት ማስተላለፊያ ማግኘቱም ለሰልፎቹ ስኬት ቁልፍ ነበር። ቱኒዚያ እና ግብጽ ከአገራችን ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ የሆነ የኢንተርነት አገልግሎት ሽፋን ያለባቸው አገራት በመሆናቸው ወጣቶች ለመገናኘት እና ሃሳብ ለመለዋወጥ ችግር አልነበረባቸውም። ይሁን እንጂ፥ መንግስታቶቻቸው አጣብቂኝ ውስጥ ሲገቡ ያም ተዘጋባቸው። ያ ግን ተቃውሟቸውን አላቆመውም። በሁለቱም አገራት፥ ደርግን የሚቃወሙ ወጣቶች በአገራችን ያደርጉ እንደነበረው፣ ወጣቶች በየግድግዳው ላይ መፈክሮችን በመጻፍ ህዝባቸውን ያበረታቱ እና አምባገነኖቹን ይቃወሙ ነበር።
  7. ሰሞኑን ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ፌስቡክ በተባለው የኢንተርነት መገናኛ መረብ ላይ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ሲካፈሉት አየሁ ብለው አንድ ግለሰብ የላኩልን ዘዴ ደግሞ በብር ላይ ተቃውሞን መጻፍ ነው። ይህ ሃሳብ ከዚህ ቀደም በሌሎች አገራት በስራ ላይ የዋለ ሲሆን፤ ብር እራሱን በራሱ ስለሚያጓጉዝ መልክቶች በፍጥነት እንዲዘዋወሩ ይረዳል።
  8. መልክቶችን የአገዛዙ ሰላዮች ሳያዩ ማዘዋወር በትኩረት ቢታሰብበት ከማንም በላይ ለኢትዮጵያውያን ይቀላል። ከጥቂት አስርተ አመታት በፊት አደን ማደን በህግ ክልክል ነው የተባሉ አባቶቻችን፤ ባጠመዱት ወጥመድ ሲሮጥ መጥቶ የገባላቸውን ድኩላ ደብቀው ወደቤት ለመውሰድ ችግር አልነበረባቸውም። በኬሻ ጠቅልለው አህያ ላይ ይጭኑትና፤ ከላዩ ከሰል ወይም እንጨት ይጭናሉ። ድኩላ ጭኖ ብዙ ኪሎሜትር ሳይነቃበት መሄድ የሚችል ኢትዮጵያዊ ታዲያ፣ ጥቂት መቶ በራሪ ወረቀቶችን ከአዲስ አበባ ደብረብርሃን፤ ወይም ወልቂጤ መውሰድ እያቅተውም።
  9. መረጃን የማከፋፈል ስራን የሚወስዱ ሰዎች ለህዝባዊ አመጽ ቁልፍ ከመሆናቸው የተነሳ፣ የአምባገነናዊ አገዛዞች የደህንነት መዋቅር ዋና ኢላማዎች ናቸው። ስለዚህም በጥንቃቄ መመላለስ አለባቸው። ለምሳሌ፥ በራሪ ወረቀቶችን እያባዙ ማከፋፈሉን በአንድ ማእከላዊ ስፍራ ከመስራት ይልቅ፤ ለተለያዩ እና ለማይተዋወቁ አካላት ማከፋፈሉ ይቀላል።
  10. እራስን መከላከል። አምባገነኖች ሲጠበቡ፤ ሰው ከቅጠል ለይተው አያዩም። አገርንም ከአንድ ብጣሽ ወረቀት አስበልጠው አያዩም። መጨፍጨፍ ያለባቸውን ይጨፈጭፋሉ፤ ማቃጠል ያለባቸውን ሁሉ ያቃጥላሉ። በአንድ አገር ለውጥ የማምጣት ተግባር፤ በተለይም አምባገነናዊ አገዛዝን የማስወገድ ስራ፤ መስዋእትነትን የሚያስከፍል ነው። ከቤትህ ስትወጣም ይህንን አውቀህ ነው። ይሁን እንጂ፥ እስከ ሞት የሚደርስ መስዋእትነት ለነጻነትህ እና ለአገርህ ለመክፈል ዝግጁ ብትሆንም፤ እሞታለሁ ብለህ ግን ከቤትህ አትውጣ። አላማህ ለመኖር፤ ድል ለማድረግ እና ነጻ አየር ለመተንፈስ ይሁን። ውድ የሆንክ የፈጣሪ ልጅ መሆንህን፤ አገርህም ከመኖርህ እንጂ ከመሞትህ እንደማታተርፍ አትርሳ። ስለዚህ እራስህን ከጥቃት መከላከልን ጠንቅቀህ አስበህበት ውጣ።
  11. የመለስ ዜናዊ አገዛዝ፥ ባለፉት አምስት አመታት ሰልፈኞችን መቆጣጠር በሚችልበት መንገድ ላይ ከምእራባውያን መንግስታት ስልጠና አግኝቷል። በርካቶች፥ አገዛዙ ገና ከጅማሬው ግብጽ እና ቱኒዚያ እንዳደረጉት አስለቃሽ ጭስ መርጨት ሳይሆን፣ ጥይት መተኮስ እንደሚጀምር ይገምታሉ። ያ እንዳለ ሆኖ፥ ለይስሙላ ያህል፤ ለፈረንጆቹ፥ “ይኸው የሰጣችሁኝን ጋስ ተጠቅሜበታለሁ” ለማለት፤ ወይም ከተኩሱም አቀላቅሎ አስለቃሽ ጭስ የሚረጭ ከሆነ፤ በኮምጣጤ እና በሎሚ ጭማቂ የተነከሩ ሻሾችን ይዞ ከቤት መውጣት እና ጋሱ መረጨት ሲጀምር ያንን ወደ አይን ማቅረብ ይረዳል ይባላል። ለማንኛውም፥ አፍና አፍንጫ ለመሸፈን፤ እንዲሁም በወገን ላይ አደጋ ቢደርስ ቁስል መሸፈኛ እንዲሆን፤ በተቻለ መጠን ነጠላ እና ሻሽ ይዞ ከቤት በውጣት ይጠቅማል።
  12. ምግብና ውሃ። ወያኔ ከዚህ ቀደም ከኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ጋር ጦርነት በሚያካሄድበት ወቅት፤ ወደ ኦጋዴን የሚወስዱ መንገዶችን በመዝጋት ህዝቡን በረሃብ የመጨረስ “ስልት” ተብዬ ጭካኔ ተጠቅሞ ነበር። አምባገነናዊ አገዛዞች አልገዛ ያላቸውን ህዝብ በማስራብ ይታወቃሉ። አገዛዙ አሁንም ተቃውሞ ቢነሳበት፤ ይህንን ስልት ሊጠቀም ይችላል። ይሁን እንጂ፥ ይህ ኢትዮጵያውያንን የሚያሰጋ ጉዳይ አይደለም። በአገራችን፥ እንኳን በመንደሮች እና በትናንንሽ ከተሞች ይቅርና፤ በመዲናይቱ ውስጥ እንኳ፣ ብዙው ሰው ትንሽም ትሁን ጓሮ እና ግቢ አለው። ይህ ማለት ደግሞ፥ ቲማቲም፣ ካሮት፣ ጎመን፣ ድንች እና የመሳሰሉትን በቀላሉ እና በአጭር ጊዜ ውስጥ ማብቀል ይችላል። እነዚህ አትክልት፤ ያለ እንጀራ በተለያየ መልክ ተዘጋጅተው ሊበሉ ይችላሉ። እንደ ስኳር እና የምግብ ዘይት የመሳሰሉትን ለተወሰነ ጊዜ ማጣት በሰውነት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት የለም። የመጠጥ ውሃ ችግርን ለመቀነስ፤ እያንዳንዱ መንደር በመተባበር የውሃ ጉድጓድ መቆፈር ይችላል። የጉድጓድ ዉሃ ብዙውን ጊዜ ለመጠጥነት ንጹህ ቢሆንም፤ በቀላሉ ማጽዳት፣ ወይም አፍልቶ እና አቀዝቅዞ መጠጣት ይችላል። እንግዲህ እነዚህ ከሁሉ አስቀድሞ ሊደረጉ የሚገባ ዝግጅቶች ናቸው።
  13. የአላማ ጥራት እና ጽናት። የምናምጽበትን ምክንያት ጠንቅቀን ማወቅ ከብዙ አደጋ ይጠብቀናል። በራሳችን እና በአገራችን ላይ ጊዜያዊም ሆኔ ዘላቂን ጉዳት ከማድረስ ያተርፈናል። ሰሞኑን በግብጽ፥ ተስፋ የቆረጠው መንግስት የደህንነት ሰራተኞቹ እና ከእስር የተለቀቁ ወንጀለኞች የህዝብ እና የአገር ንብረት እንዲዘርፉ መንገድ ላይ ለቋቸዋል። የዚህ ዘረፋ ሰለባ ከሆኑት ተቋማት እንዱም ከአለም ታሪካዊ ቅርሶች ውስጥ ሶስት አራተኛውን ይዟል የሚባለው የአገሪቱ ሙዚየም ነው። ይህ ሲሆን፤ ሰልፈኞቹ እጅ ለእጅ ተያይዘው በሙዚየሙ ፊት በመቆም ከዘራፊዎቹ ጋር ትልቅ ተጋድሎን በማድረግ የአገራቸውን ሃብት ተከላክለዋል። ይህ ሲሆን፥ ሰልፈኞቹ ዞር ብለው ከዘረፋው በመቀላቀል እራሳቸውን ሊጠቅሙ ይችሉ ነበር። ነገር ግን የወጡበት አላማ ያ እንዳልሆነ፤ ከምንም በላይ ደግሞ የአገርን ሃብት እና ቅርስ መጠበቅ የያንዳንዱ ዜጋ ሃላፊነት እንደሆነ ስለተረዱ በርትተው ቆሙ። የትግራዩ ገዢ ቡድን ባለስልጣናት፥ የኢትዮጵያን ታሪካዊ ቅርሶች ከአገር እያስወጡ እንደሚሸጡ ከዚህ ቀደም ተወርቷል። በቅርቡ በኢትዮጵያ ህዝባዊ አመጽ ቢከሰት፣ ይህንን አጋጣሚ ተጠቅመው የተለያዩ የህዝብ እና የመንግስት ተቋማትን ለማስዘረፍ እንደሚሞክሩ እና በሰልፈኞች ላይ እንደሚያላክኩ ይገመታል። ዝርፊያ በሌለበት ዝርፊያ ተፈጽሟል ብለው እንደሚከሱ ከምርጫ 97 ልምዳችን እናውቃለን። ታዲያ በእንዲህ አይነቱ ወቅት የአገርን ሃብት ሊጠብቅ የሚችለው ዜጋው ብቻ ነውና፤ ለዚህ እንዘጋጅ።
  14. የመለስ ዜናዊ አገዛዝ፥ ከዚህ ቀደም ጭንቀት ውስጥ ሲገባ የዘር እና የሃይማኖት ግጭት እንደሚያነሳሳ ከልምዳችን እናውቃለን። ወደፊትም ቢሆን አጣብቂኝ ውስጥ ሲገባ ያንን ለመቀስቀስ ተዘጋጅቶ እና፤ ያንን ስራ የሚሰሩለትን ሰዎች በዙሪያው ኮልኩሎ እንደሚቀመጥ ጠንቅቀን እናውቃለን። ባለፈው ሳምንት በግብጽ የሆነው ክስተት ከዚህ አኳያ ትልቅ ትምህርት ሊሆነን ይችላል። ሙስሊሞች ወደ ጁማአ ጸሎት ሲገቡ፤ ክርስቲያን ወንድሞቻቸው ውጪ ቆመው ጸሎተኞቹን እና መስጊዶችን እንደሚጠብቁ ቃል ገቡ። እኛም በኢትዮጵያችን እንደዚህ ያለ ፍቅርን እና መተሳሰብን ልናሳይ ይገባናል። ከሁሉ አስቀድመን፤ ባህላችን እና ሃይማኖቶቻችን ስለ ጉርብትና የሚያስተምሩንን አንርሳ። መለስ ዜናዊ የሲቪል ልብስ የለበሱ ቅጥረኞቹን አሰማርቶ በዚህና በዚያ ዘውጌ ማህበረሰብ ላይ፤ በዚህና በዚያ ሃይማኖት አባላይ ላይ ተነሳ እያለ በጆሮህ ቢያንሾካሹክ፤ ጥላቻን የሚያውጆ በራሪ ወረቀቶች በአገዛዙ ሰዎች ተዘጋጅተው ቢበተኑ፤ አንዱንም አትስማ። አንተ የወጣኸው ነጻነትን እና የተሻለ ኑሮን ፍለጋ እንጂ ወገኖችህን ልታጠቃ አይደለም። ስለዚህም፥ በአቋምህ ጽና።
  15. ሰልፈኞች፥ የህዝብ ንብረት እነሱን ለማፈኑ ስራ ጥቅም ላይ ሲውል ሲያዩ፤ ያንን ንብረት እንደ ጠላት ንብረት ያያሉ። ለምሳሌ በግብጽ በርካታ የፖሊስ መኪናዎች ተቃጥለዋል። ህዝቡ ይህን በማድረጉ ወንጀል አልፈጸመም፤ እራሱን የመከላከል መብት ስላለው። ይሁን እንጂ፥ ይህ አምባገነኖች የሚጠቀሙበት ተሽከርካሪ ወይም ህንጻ፤ ዞሮ ዞሮ የኛው ንብረት ነው። ሲቃጠል የሚከፍለው ህዝብ ነው እንጂ አምባገነኑ አይደለም። ታዲያ እንዴት አድርገን እራሳችንን እንከላከል? ላሰበበት ሁልጊዜም ቢሆን የተሻለ አማራጭ አይታጣም። ለምሳሌ፥ ሰሞኑን አንዳንድ ብልጥ የግብጽ ወጣቶች፤ የፖሊስ ተሽከርካሪዎችን በማቃጠል ፈንታ፤ ባትሪዎቻቸውን በማስወገድ እና ከፖሊሶቹ አይን በመሰወር መኪናዎቹ እንዳይንቀሳቀሱ አድርገዋል። ይህ አንድ ዘዴ ነው።
  16. ድፍረት። እንግዲህ አምባገነናዊ አገዛዞችን ለመገልበጥ፤ በመጀመሪያ ፍርሃትን ማሸነፍ ይገባል። በአመጽ ስራ የሚሳተፉ ሰዎች፤ ብዙ ጊዜ መጀመሪያ ላይ ፍርሃት እንደሚሰማቸው ይናገራሉ። ነገር ግን የመጀመሪያዋን እርምጃ ከወሰዱ በኋላ፤ ስጋታቸው እየሟሸሸ ይሄድና ጨርሶ ይጠፋል። ስለዚህ፥ ጀግና ሁሉ ከፍጥረቱ ጀምሮ ደፋር ነበር የሚል አመለካከት ከያዝን ተሳስተናል። ድፍረት የሚገኘው በሂደት ነው። እናም የመጀመሪያዋ እርምጃ ወሳኝ ነች።

እንግዲህ፥ እነዚህ የሃሳብ ስብስቦች ያቀረብነው፤ ለችግር ሁሉ መፍትሄ በገዛ እጃችን እንዳለና፤ ለሰው አእምሮ የማሰብ ችሎታ ማቆሚያ እንደሌለው ለማሳሰብ ያህል ነው።