የአንድነት ፓርቲ ስራ አስፈጻሚዎች የፊርማ ማሰባሰቡን ሂደት ይመራሉ

በተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የመስራቾች ፊርማ ማሰባሰብ በነገው እለት ይጀመራል፡፡

ወደተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በሚደረገው በዚህ የመስራች አባላት ፊርማ የማሰባሰብ ሂደት ወ/ሪት ብርቱካን፤ አቶ ሙሉነህ፤ መቶ አለቃ አለማሁ የኔነህ (አስተባባሪው)፤አቶ መሃመድ አሊ እና ሌሎች የስራ አስፈጻሚ አባላት ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን በዛሬው እለት ርቼ አከባቢ ባለው የፓርቲው ጽ/ቤት በተደረገው ማብራርያና የቅድመ ዝግጅት ውይይት በሂደቱ የሚሳተፉት አባላት ማንኛውንም መስዋእትነት ለመጋፈጥ መዘጋጀታቸውን አረጋግጠዋል፡፡

የምርጫ ቦርድ የድጋፍ ደብዳቤ ለመጻፍ የተለያዩ ሰበቦችን ሲያስቀምጥ ከቆየ በኋላ እምቢታውን መግለጹ ይታወሳል፡፡