እስረኞችን ለማስፈታት የቅንጅት ስራ አስፈጻሚ ከአገር ሽማግሌዎች ጋር እየሰራ ነው

ምርጫ 97ትን ተከትሎ በተፈጠረው ቀውስ ለእስር የተዳረጉ የቅንጅት ደጋፊዎችንና አባላትን ለማስፈታት የቅንጅት ስራ አስፈጻሚ አባላትና የአገር ሽማግሌዎች በጥምር በመስራት ላይ መሆናቸውን አንድ የስራ አስፈጻሚ አባል ለዜና አገልግሎቱ ገለጹ፡፡

ህዝባዊውን ፓርቲ ህጋዊ ከማድረጉ እንቅስቃሴ ጎን ለጎን እየተካሄደ ባለው እስረኞችን የማስፈታት እንቅስቃሴ በትናንትናው እለት 24 ያህል ፍርድ የተሰጠባቸው እስረኞችን የምህረት ሰነድ ያስፈረሙ ሲሆን በዛሬው እለት በተካሄደ የስራ አስፈጻሚው ስብሰባ ደግሞ ጉዳያቸው በፍርድ እየታየ ያሉት ሌሎች እስረኞችም የምህረቱ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ጥረት ለማድረግ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የስራ አስፈጻሚ ቡድን በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅ ከሚመራው የአገር የሽማግሌዎች ቡድን ጋር በመተባበር እስረኞቹን አስመልክቶ ለህዝቡ የገባውን ቃል ለመፈጸም ያለመታከት እንደሚሰራ የአመራር አባሉ ጨምረው ገልጸዋል፡፡