Ethiopian News and Opinion Forum


Re: BREAKING NEWS! Ethiopian Troops Conducted Military Operation Deep Inside Ar-Tera

Postby Bwendimu » 01 Jun 2012, 22:28


The only problem with Ethiopian army is the leaders who refused to sign the document before them and release the fund and say "go". Once that is signed the end shall come to that region proglem.



Re: BREAKING NEWS! Ethiopian Troops Conducted Military Operation Deep Inside Ar-Tera

Postby Gurezza » 01 Jun 2012, 23:49


Bedatamu,
How soon did you forget? :lol: The all super power signed and agreed for you eko, including sanctioning. The only missing point is, courage from the CHIGARAM ZERE. You are scared to do it, don't you? :lol: we will make you lick Alshebab behind and ask for help, the way you did it last time the degree soldiers. :lol:



Re: BREAKING NEWS! Ethiopian Troops Conducted Military Operation Deep Inside Ar-Tera

Postby PissingBy » 02 Jun 2012, 21:47


የኢትዮጵያ ሠራዊት በኤርትራ ጦር ላይ ጥቃት ፈጸመ

Sunday, 03 June 2012 00:00
By a Staff Reporter

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፈው ሳምንት ኤርትራ የነፃነት ቀኗን ስታከብር በነበረበት ዕለት፣ ባድመ በሚገኘው የኤርትራ ጦር ላይ ጥቃት ማድረሱን ወታደራዊ ምንጮች ገለጹ፡፡ ጥቃቱ በትግራይ አካባቢ በቅርቡ በኤርትራ ጦር ታፍነው ለተወሰዱ ኢትዮጵያውያን አጸፋዊ ምላሽ ነው ተብሏል፡፡

ማንነታቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ የመከላከያ ሠራዊት ምንጮች እንደገለጹት፣ ግንቦት 16 ቀን 2004 ዓ.ም. የኤርትራን ድንበር ጥሶ የገባው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባድመ አካባቢ በሰፈረው በአንድ ብርጌድ የኤርትራ ጦር ላይ ድንገተኛ ጥቃት ሰንዝሮ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡

በጥቃቱ በርካታ የኤርትራ ወታደሮች የመቁሰልና የሞት አደጋ የደረሰባቸው መሆኑን፣ እስከ ሻለቃ ማዕረግ ያላቸው በርካታ የኤርትራ ጦር አመራሮችም እጃቸውን የሰጡ መሆናቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከወራት በፊት በተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፣ የኤርትራ መንግሥት ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚፈጽመው የሽብር ጥቃት ተመጣጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በያዝነው ዓመት ጥር ወር ላይ አፋር ክልል ውስጥ የተገደሉትና ታፍነው የተወሰዱትን የአውሮፓውያን ቱሪስቶች ሴራ ያቀነባበረው የኤርትራ መንግሥት ነው ብሎ ያመነው የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የመከላከያ ሠራዊቱ የኤርትራን ድንበር ጥሶ በመግባት ሽብርተኞች የሚንቀሳቀሱባቸው ናቸው ባላቸው ሦስት የጦር ካምፖች ላይ ጥቃት ፈጽሟል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንን ጥቃት ካካሄደ በኋላም ግን ትግራይ አካባቢ በማዕድን ፍለጋ ላይ የተሰማሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በየጊዜው በኤርትራ ጦር እየታፈኑ እንደሚወሰዱ በተቃዋሚዎችም ሆነ በመንግሥት በኩል ሲገለጽ ቆይቷል፡፡

የመከላከያ ምንጮች እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ ጦር ሰሞኑን በኤርትራ ላይ የወሰደው ወታደራዊ ጥቃት የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ አካባቢ ለሚፈጽሙት አፈና አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የወሰደውን ዕርምጃ በማስመልከት ከኤርትራ በኩል የተገለጸ ነገር የለም፡፡

Previous Page


Return to News & Opinion

Who is online

Registered users: Abdelaziz, Anti-Slavery, Bing [Bot], Bwendimu, elias, Google [Bot], Google Adsense [Bot], Google Desktop, Google Feedfetcher, Harboy II, Individual, MINILIK SALSAWI, molover